1 ዮሐንስ 5 – NASV & NSP

New Amharic Standard Version

1 ዮሐንስ 5:1-21

በእግዚአብሔር ልጅ ማመን

1ኢየሱስ እርሱ ክርስቶስ እንደ ሆነ የሚያምን ሁሉ ከእግዚአብሔር ተወልዷል፤ አባትንም የሚወድድ ሁሉ ልጁንም እንደዚሁ ይወድዳል። 2እግዚአብሔርን ስንወድድና ትእዛዞቹን ስንፈጽም የእግዚአብሔርን ልጆች እንደምንወድድ በዚህ እናውቃለን፤ 3እግዚአብሔርን መውደድ ትእዛዞቹን መፈጸም ነውና። ትእዛዞቹም ከባድ አይደሉም፤ 4ምክንያቱም ከእግዚአብሔር የተወለደ ሁሉ ዓለምን ያሸንፋል። ዓለምን የሚያሸንፈውም እምነታችን ነው። 5ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ ከሚያምን በስተቀር ዓለምን የሚያሸንፍ ማነው?

6በውሃና በደም የመጣው ይህ፣ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። እርሱ በውሃና በደም እንጂ በውሃ ብቻ አልመጣም። የሚመሰክረውም መንፈስ ነው፤ መንፈስ እውነት ነውና። 7ስለዚህ ሦስት ምስክሮች አሉት፤ 8እነርሱም5፥7-8 ጥንታዊ ባልሆነው በቩልጌት ቅጅ ላይ በሰማይ የሚመሰክሩት ሦስቱ ናቸው፤ እነርሱም አባት፣ ቃልና መንፈስ ቅዱስ ናቸው ይላል። 8 በምድር የሚመሰክሩት ሦስቱ ናቸው – ሆኖም ይህ ከ16ኛው ክፍለ ዘመን በፊት በነበሩት የግሪክ ቅጆች ውስጥ አይገኝም። መንፈሱ፣ ውሃውና ደሙ ናቸው፤ ሦስቱም ይስማማሉ። 9የሰውን ምስክርነት ከተቀበልን፣ የእግዚአብሔር ምስክርነት ከዚያም ይልቃል፤ ይህ ስለ ልጁ የሰጠው የእግዚአብሔር ምስክርነት ነውና። 10በእግዚአብሔር ልጅ የሚያምን ሁሉ በልቡ ምስክር አለው፤ ማንም እግዚአብሔርን የማያምን ሁሉ እግዚአብሔር ስለ ልጁ የሰጠውን ምስክርነት ስላላመነ ሐሰተኛ አድርጎታል። 11ምስክርነቱም ይህ ነው፤ እግዚአብሔር የዘላለምን ሕይወት ሰጠን፤ ይህም ሕይወት ያለው በልጁ ነው። 12ልጁ ያለው ሕይወት አለው፤ የእግዚአብሔር ልጅ የሌለው ሕይወት የለውም።

ማጠቃለያ ሐሳብ

13በእግዚአብሔር ልጅ ስም የምታምኑ እናንተ፣ የዘላለም ሕይወት እንዳላችሁ ታውቁ ዘንድ ይህን እጽፍላችኋለሁ፤ 14በእግዚአብሔር ፊት ለመቅረብ ያለን ድፍረት ይህ ነው፤ ማንኛውንም ነገር እንደ ፈቃዱ ብንለምን እርሱ ይሰማናል። 15የምንለምነውን ሁሉ እንደሚሰማን ካወቅን፣ የለመንነውንም ነገር እንደ ተቀበልን እናውቃለን።

16ማንም ሰው ወንድሙ ለሞት የማያበቃ ኀጢአት ሲያደርግ ቢያየው ይጸልይ፤ እግዚአብሔርም ለሞት የማያበቃ ኀጢአት ላደረጉት ሕይወትን ይሰጣል። ለሞት የሚያበቃም ኀጢአት አለ፤ ስለዚህኛው ግን ይጸልይ አልልም። 17ዐመፅ ሁሉ ኀጢአት ነው፤ ለሞት የማያበቃም ኀጢአት አለ። 18ከእግዚአብሔር የተወለደ ሁሉ ኀጢአት እንደማያደርግ፣ ነገር ግን የእግዚአብሔር ልጅ እንደሚጠብቀው፣ ክፉውም እንደማይነካው እናውቃለን። 19እኛ ከእግዚአብሔር እንደ ሆንን፣ መላው ዓለምም በክፉው ሥር እንደ ሆነ እናውቃለን።

20የእግዚአብሔር ልጅ እንደ መጣ፣ እውነተኛ የሆነውን እርሱን እንድናውቅ ማስተዋልን እንደ ሰጠን እናውቃለን፤ እኛም እውነተኛ በሆነው በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ አለን። እርሱ እውነተኛ አምላክና የዘላለም ሕይወት ነው።

21ልጆች ሆይ፤ ራሳችሁን ከጣዖቶች ጠብቁ።

New Serbian Translation

1. Јованова 5:1-21

Победоносна вера у Христа

1Свако ко верује да је Исус Христос, рођен је од Бога, и свако ко воли Оца, воли и оног који је рођен од њега. 2А да смо деца Божија, знамо по томе што волимо Бога и држимо се његових заповести. 3Љубав према Богу значи ово: држати његове заповести. Његове заповести нису тешке, 4јер сви који су рођени од Бога побеђују свет. А ово је средство наше победе: наша вера. 5Ко побеђује свет, ако не онај који верује да је Исус Син Божији?

6Он, Исус Христос, је онај који је дошао водом и крвљу. Не само водом, него водом и крвљу. А сам Дух сведочи о овоме, јер Дух је истина. 7Тако, имамо три сведока: 8Духа, воду и крв; а ово троје се слажу. 9Ако верујемо људском сведочанству, знајмо да је Божије сведочанство веће. Ово је Божије сведочанство којим је Бог потврдио свога Сина: 10ко верује у Сина Божијега има ово сведочанство у свом срцу, а ко не верује Богу, прави од њега лажљивца, јер није поверовао сведочанству којим је Бог потврдио свога Сина. 11Ово је сведочанство: Бог нам је дао живот вечни и овај живот је у његовом Сину. 12Ко има Сина има живот, а ко нема Сина Божијег, нема живота.

Вечни живот

13Ово сам написао вама који верујете у Сина Божијег, да знате да имате вечни живот. 14Ово је поуздање које имамо у њега: он нас слуша штогод да затражимо по његовој вољи. 15А ако знамо да нас слуша што год затражимо, онда знамо да већ имамо оно што смо тражили од њега.

Рођени од Бога не остаје у греху

16Ако неко види свога брата да чини грех који не води у смрт, нека моли за њега и Бог ће му дати живот. То је за оне који не чине смртни грех. Међутим, постоји грех који води у смрт. За такав грех не кажем да се моли. 17Свака је неправда грех, али постоји грех који не води у смрт.

18Знамо да свако ко је од Бога рођен не живи грешно, јер га онај који је рођен од Бога чува, и Зли га се не дотиче. 19Ми знамо да смо од Бога, а да је сав свет у власти Злога. 20Али знамо да је Син Божији дошао и дао нам разум да упознамо Истинитога. А ми смо у Истинитом – у његовом Сину Исусу Христу. Он је истински Бог и вечни живот.

21Дечице, чувајте се идола!