1 ዜና መዋዕል 6 – NASV & OL

New Amharic Standard Version

1 ዜና መዋዕል 6:1-81

ሌዊ

1የሌዊ ወንዶች ልጆች፤

ጌድሶን፣ ቀዓት፣ ሜራሪ።

2የቀዓት ወንዶች ልጆች፤

እንበረም፣ ይስዓር፣ ኬብሮን፣ ዑዝኤል።

3የእንበረም ልጆች፤

አሮን፣ ሙሴ፣ ማርያም።

የአሮን ወንዶች ልጆች፤

ናዳብ፣ አብዩድ፣ አልዓዛር፣ ኢታምር።

4አልዓዛር ፊንሐስን ወለደ፤

ፊንሐስ አቢሱን ወለደ፤

5አቢሱ ቡቂን ወለደ፤

ቡቂ ኦዚን ወለደ፤

6ኦዚ ዘራእያን ወለደ፤

ዘራእያ መራዮትን ወለደ፤

7መራዮት አማርያን ወለደ፤

አማርያ አኪጦብን ወለደ፤

8አኪጦብ ሳዶቅን ወለደ፤

9ሳዶቅ አኪማአስን ወለደ፤

አኪማአስ ዓዛርያስን ወለደ፤

ዓዛርያስ ዮሐናንን ወለደ፤

10ዮሐናን ዓዛርያስን ወለደ፤ እርሱም ሰሎሞን በኢየሩሳሌም ባሠራው ቤተ መቅደስ በክህነት ያገለገለ ነበር፤

11ዓዛርያስ አማርያን ወለደ፤

አማርያም አኪጦብን ወለደ፤

12አኪጦብ ሳዶቅን ወለደ፤

ሳዶቅ ሰሎምን ወለደ፤

13ሰሎም ኬልቅያስን ወለደ፤

ኬልቅያስ ዓዛርያስን ወለደ፤

14ዓዛርያስ ሠራያን ወለደ፤

ሠራያ ኢዮሴዴቅን ወለደ።

15እግዚአብሔር የይሁዳና የኢየሩሳሌም ሕዝብ በናቡከደነፆር እጅ ተማርከው እንዲወሰዱ ባደረገ ጊዜ ኢዮሴዴቅም አብሮ ተማርኮ ሄደ።

16የሌዊ ወንዶች ልጆች፤

ጌድሶን፣ ቀዓት፣ ሜራሪ።

17የጌድሶን ወንዶች ልጆች፤

ሎቤኒ፣ ሰሜኢ።

18የቀሃት ወንዶች ልጆች፤

እንበረም፣ ይስዓር፣ ኬብሮን፣ ዑዝኤል።

19የሜራሪ ወንዶች ልጆች፤

ሞሖሊ፣ ሙሲ።

በየአባቶቻቸው ቤተ ሰብ የተቈጠሩት የሌዊ ጐሣዎች የሚከተሉት ናቸው፤

20ከጌርሶን፤

ልጁ ሎቤኒ፣ ልጁ ኢኤት፣

ልጁ ዛማት፣ 21ልጁ ዮአክ፣

ልጁ አዶ፣ ልጁ ዛራ፣ ልጁ ያትራይ።

22የቀዓት ዘሮች፤

ልጁ አሚናዳብ፣ ልጁ ቆሬ፣

ልጁ አሴር፣ 23ልጁ ሕልቃና፣

ልጁ አቢሳፍ፣ ልጁ አሴር፣

24ልጁ ኢኢት፣ ልጁ ኡርኤል፣

ልጁ ዖዝያ፣ ልጁ ሳውል።

25የሕልቃና ዘሮች፤

አማሢ፣ አኪሞት።

26ልጁ ሕልቃና፣6፥26 አንዳንድ የዕብራይስጥ ቅጆች፣ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕምና የሱርስቱ ቅጅ ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ አብዛኞቹ የዕብራይስጥ ቅጆች ግን፣ ኪሞትና 26 ሕልቃና፤ የሕልቃና ወንዶች ልጆች፤ ልጁ ሱፊ፣

ልጁ ናሐት፣ 27ልጁ ኤልያብ፣

ልጁ ይሮሐም፣ ልጁ ሕልቃና፣

ልጁ ሳሙኤል6፥27 አንዳንድ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞች (እንዲሁም 1ሳሙ 1፥1920 እና 1ዜና 6፥3334 ይመ) ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ ዕብራይስጡ ግን፣ ልጁ ሳሙኤል የሚለውን ሐረግ አይጨምርም

28የሳሙኤል ወንዶች ልጆች፤

የበኵር ልጁ ኢዮኤል6፥28 አንዳንድ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞችና ሱርስቱ (እንዲሁም 1ሳሙ 8፥2 እና 1ዜና 6፥33 ይመ) ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ ዕብራይስጡ ግን፣ ኢዩኤል የሚለውን ስም አይጨምርም።

ሁለተኛው ልጁ አብያ።

29የሜራሪ ዘሮች፤

ሞሖሊ፣ ልጁ ሎቤኒ፣

ልጁ ሰሜኢ፣ ልጁ ዖዛ፣

30ልጁ ሳምዓ፣ ልጁ ሐግያ፣

ልጁ ዓሣያ።

የቤተ መቅደሱ መዘምራን

6፥54-80 ተጓ ምብ – ኢያ 21፥4-39

31ታቦቱ ከገባ በኋላ፣ ዳዊት የመዘምራን አለቃ አድርጎ በእግዚአብሔር ቤት የሾማቸው ሰዎች እነዚህ ናቸው፤ 32እነርሱም ሰሎሞን የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ በኢየሩሳሌም እስኪሠራ ድረስ፣ በማደሪያው፣ ይኸውም በመገናኛው ድንኳን ፊት ሆነው እየዘመሩ ያገለግሉ ነበር፤ አገልግሎታቸውንም የሚያከናውኑት በወጣላቸው ደንብ መሠረት ነው።

33ከወንዶች ልጆቻቸው ጋር ሆነው ያገለገሉ ሰዎች እነዚህ ናቸው፤

ከቀዓታውያን ልጆች፤ ዘማሪው ኤማን፣ የኢዮኤል ልጅ፣ የሳሙኤል ልጅ፣

34የሕልቃና ልጅ፣ የይሮሐም ልጅ፣

የኤሊኤል ልጅ፣ የቶዋ ልጅ፣

35የሱፍ ልጅ፣ የሕልቃና ልጅ፣

የመሐት ልጅ፣ የአማሢ ልጅ፣

36የሕልቃና ልጅ፣ የኢዮኤል ልጅ፣

የዓዛርያስ ልጅ፣ የሶፎንያስ ልጅ፣

37የታሐት ልጅ፣ የአሴር ልጅ፣

የአብያሳፍ ልጅ፣ የቆሬ ልጅ፣

38የይስዓር ልጅ፣ የቀዓት ልጅ፣

የሌዊ ልጅ፣ የእስራኤል ልጅ።

39እንዲሁም የሔማን ወንድም አሳፍ በስተ ቀኙ ሆኖ ያገለግል ነበር፤

አሳፍ የበራክያ ልጅ፣ የሳምዓ ልጅ፣

40የሚካኤል ልጅ፣ የበዓሤያ ልጅ፣

የመልክያ ልጅ፣ 41የኤትኒ ልጅ፣

የዛራ ልጅ፣ የዓዳያ ልጅ፣

42የኤታን ልጅ፣ የዛማት ልጅ፣

የሰሜኢ ልጅ፣ 43የኢኤት ልጅ፣

የጌድሶን ልጅ፣ የሌዊ ልጅ፤

44በስተ ግራቸው በኩል አብረዋቸው ያሉት የሜራሪ ልጆች፤

የቂሳ ልጅ ኤታን፣ የአብዲ ልጅ፣

የማሎክ ልጅ፣ 45የሐሸብያ ልጅ፣

የአሜስያስ ልጅ፣ የኬልቅያስ ልጅ፣

46የአማሲ ልጅ፣ የባኒ ልጅ፣

የሴሜር ልጅ፣ 47የሞሖሊ ልጅ፣

የሙሲ ልጅ የሜራሪ ልጅ፣

የሌዊ ልጅ።

48ሌዋውያን ወንድሞቻቸው ግን የእግዚአብሔርን ቤት የማደሪያ ድንኳን ተግባር እንዲያከናውኑ ተመድበው ነበር። 49የእግዚአብሔር ባሪያ ሙሴ ባዘዘው መሠረት፣ ስለ እስራኤል ማስተስረያ በቅድስተ ቅዱሳኑ ውስጥ የሚከናወነውን ተግባር ሁሉ፣ በመሠዊያው ላይ የሚቃጠል መሥዋዕትና በዕጣኑ መሠዊያ ላይ የሚቀርበውን መሥዋዕት የሚያቀርቡት ግን አሮንና ዘሮቹ ብቻ ነበሩ።

50የአሮን ዘሮች እነዚህ ነበሩ፤

ልጁ አልዓዛር፣ ልጁ ፊንሐስ፣

ልጁ አቢሱ 51ልጁ ቡቂ፣

ልጁ ኦዚ፣ ልጁ ዘራእያ፣

52ልጁ መራዮት፣ ልጁ አማርያ፣

ልጁ አኪጦብ፣ 53ልጁ ሳዶቅ፣

ልጁ አኪማአስ።

54መኖሪያዎቻቸው እንዲሆኑ የተመደቡላቸው ቦታዎች እነዚህ ናቸው፦ የመጀመሪያው ዕጣ የእነርሱ ስለሆነ፣ ከቀዓት ጐሣ ለሆኑት ለአሮን ዘሮች የተመደቡላቸው መኖሪያዎች እነዚህ ነበሩ።

55ለእነርሱም በይሁዳ ምድር የምትገኘው ኬብሮንና በዙሪያዋ ያለው የግጦሽ ቦታ ተሰጠ፤ 56በኬብሮን ዙሪያ የሚገኙት የዕርሻ ቦታዎችና መንደሮች ግን ለዮፎኒ ልጅ ለካሌብ ተሰጡ። 57ለአሮን ዘሮች የመማፀኛ ከተሞች የሆኑትን ኬብሮንን፣ ልብናን፣ የቲርን፣ ኤሽትሞዓን፣ 58ሖሎንን፣ ዳቤርን፣ 59ዓሳንን፣ ዮታን6፥59 የሱርስቱ ቅጅ (እንዲሁም የሰብዓ ሊቃናትና ኢያ 21፥16) ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ ዕብራይስጡ ግን፣ ዮታን የሚለውን ስም አይጨምርም።፣ ቤትሳሚስን ከነመሰማሪያዎቻቸው ሰጡ።

60ከብንያም ነገድ ድርሻ ላይ ገባዖንን፣6፥60 ኢያ 21፥17 ከዚህ ጋር ይስማማል፤ ዕብራይስጡ ግን ገባዖን የሚለውን ስም አይጨምርም። ጌባን፣ ጋሌማን፣ ዓናቶትን ከነመሰማሪያዎቻቸው ሰጡ።

ለቀዓት ዘሮች የተከፋፈሉት እነዚህ ከተሞች በአጠቃላይ ዐሥራ ሦስት ናቸው።

61ለቀሩት የቀዓት ዘሮች ደግሞ ከምናሴ ነገድ እኩሌታ ድርሻ ዐሥር ከተሞች ተሰጧቸው።

62ለጌድሶን ነገድ በየጐሣቸው ከይሳኮር፣ ከአሴር፣ ከንፍታሌምና በባሳን ከሚገኘው ከምናሴ ነገድ ድርሻ ላይ ዐሥራ ሦስት ከተሞች ተመደቡላቸው።

63ለሜራሪ ዘሮች በየጐሣቸው ከሮቤል፣ ከጋድና ከዛብሎን ድርሻ ላይ ዐሥራ ሁለት ከተሞች ተመደቡላቸው።

64እስራኤላውያንም ከተሞቹን በዚሁ ሁኔታ መድበው ከነመሰማሪያዎቻቸው ለሌዋውያኑ ሰጧቸው።

65ቀደም ብለው የተጠቀሱትንም ከተሞች ከይሁዳ፣ ከስምዖንና ከብንያም ነገድ ላይ ወስደው መደቡላቸው።

66ለአንዳንድ የቀዓት ጐሣዎችም ከኤፍሬም ነገድ ድርሻ ላይ የሚኖሩበት ቦታ ተሰጣቸው።

67በኰረብታማው በኤፍሬም ምድር የሚገኙትን የመማፀኛ ከተሞች ሴኬምን፣ ጌዝርን፣ 68ዮቅምዓምን፣ ቤትሖሮን፣ 69ኤሎንንና ጋትሪሞን ከነመሰማሪያዎቻቸው ሰጧቸው።

70እንዲሁም እስራኤላውያን ከምናሴ ነገድ እኩሌታ ድርሻ ላይ ዓኔርና ቢልዓም የተባሉትን ከተሞች ከነመሰማሪያዎቻቸው ወስደው ለቀሩት የቀዓት ጐሣዎች ሰጧቸው።

71ጌድሶናውያን ከዚህ የሚከተሉትን ከተሞች ወሰዱ፤

ከምናሴ ነገድ እኩሌታ፣ በባሳን የሚገኘውን ጎላንና አስታሮትን ከነመሰማሪያዎቻቸው ወሰዱ፤

72ከይሳኮርም ነገድ፣ ቃዴስን፣ ዳብራትን 73ራሞትንና ዓኔምናን ከነመሰማሪያዎቻቸው ወሰዱ፤

74ከአሴር ነገድ መዓሳልን፣ ዓብዶን፣ 75ሑቆቅንና፣ ረአብን ከነመሰማሪያዎቻቸው ወሰዱ፤

76ከንፍታሌም ነገድ በገሊላ የሚገኘውን ቃዴስን፣ ሐሞንንና፣ ቂርያታይምን ከነመሰማሪያዎቻቸው ወሰዱ።

77ከሌዋውያን የቀሩት የሜራሪ ጐሣዎች ደግሞ ከዚህ የሚከተለውን ወሰዱ፤

ከዛብሎን ነገድ ዮቅኒዓምን፣ ቀርታህን፣6፥77 የሰብዓ ሊቃናት ትርጕምንና ኢያ 21፥34 ይመ፤ ዕብራይስጡ ግን፣ ዮቅኒዓምን፣ ቀርታህን የሚለውን አይጨምርም። ሬሞንና፣ ታቦርን ከነመሰማሪያዎቻቸው ወሰዱ።

78ከዮርዳኖስ ወንዝ ማዶ ከኢያሪኮ በስተ ምሥራቅ ከሚገኘው ከሮቤል ነገድ፣

በምድረ በዳ የሚገኘውን ቦሶርን፣ ያሳን፣ 79ቅዴሞትንና ሜፍዓትን ከነመሰማሪያዎቻቸው ወሰዱ፤

80ከጋድ ነገድ በገለዓድ የምትገኘውን ሬማትን፣ መሃናይምን፣ 81ሐሴቦንና ኢያዜርን ከነመሰማሪያዎቻቸው ወሰዱ።

O Livro

1 Crónicas 6:1-81

A descendência de Levi

(Êx 6.16-27; Nm 3.17-20)

1São estes os nomes dos filhos de Levi:

Gerson, Coate e Merari.

2Os filhos de Coate foram:

Amrão, Izar, Hebrom e Uziel.

3Os descendentes de Amrão incluíam:

Aarão, Moisés e Miriam.

Os filhos de Aarão foram:

Nadabe, Abiú, Eleazar e Itamar.

4Os filhos mais velhos das sucessivas gerações de Aarão foram:

Eleazar, pai de Fineias,

5pai de Abisua, pai de Buqui,

6pai de Uzi,

pai de Zeraías,

7pai de Meraiote,

pai de Amarias,

8pai de Aitube,

pai de Zadoque,

9pai de Aimaaz,

pai de Azarias,

pai de Joanã,

10pai de Azarias, o sumo sacerdote no templo de Salomão, em Jerusalém,

11pai de Amarias,

12pai de Aitube,

pai de Zadoque,

13pai de Salum,

pai de Hilquias,

14pai de Azarias,

pai de Seraías,

pai de Jeozadaque,

15o qual foi levado para o exílio, quando o Senhor mandou o povo de Judá e de Jerusalém para o cativeiro sob Nabucodonozor.

16Tal como se disse antes, os filhos de Levi foram:

Gerson, Coate e Merari.

17Os filhos de Gerson foram:

Libni e Simei.

18Os filhos de Coate foram:

Amrão, Izar, Hebrom e Uziel.

19Os filhos de Merari:

Mali e Musi.

Os subclãs dos levitas foram:

20No clã de Gerson:

Libni, Jaate, Zima,

21Joá, Ido, Zera e Jeaterai.

22No clã de Coate: Aminadabe, Coré, Assir,

23Elcana, Ebiasafe, Assir,

24Taate, Uriel, Uzias e Saul.

25O subclã de Elcana, os seus filhos: Amasai, Aimote,

26Elcana, Zofai, Naate,

27Eliabe, Jeroão, Elcana.

28As famílias do subclã de Samuel foram encabeçadas pelos filhos de Samuel: Joel, o mais velho, e Abias, o segundo.

29Os subclãs de Merari foram encabeçados pelos seus filhos:

Mali, Libni, Simei, Uzá,

30Simeia, Hagias e Asaías.

Os músicos do templo

31O rei David nomeou cantores e organizou coros para louvarem o Senhor no templo, depois de ali ter colocado a arca. 32Já antes de Salomão construir o templo do Senhor, estes homens exerciam as suas funções de cantores, diante da tenda do encontro, conforme as normas estabelecidas.

33Estes são os nomes dos antecessores dos líderes dos coros:

Hemã, o cantor, era do clã de Coate; a sua genealogia foi traçada em retrospetiva da seguinte forma:

Joel, Samuel,

34Elcana III, Jeroão, Eliel, Toá,

35Zufe, Elcana II, Maate, Amasai,

36Elcana I, Joel, Azarias, Sofonias,

37Taate, Assir, Ebiasafe, Coré,

38Izar, Coate, Levi e Israel.

39O assistente de Hemã era o seu colega Asafe, cuja genealogia retrospetiva foi traçada da seguinte maneira:

Berequias, Simeia,

40Micael, Baaseias, Malquias,

41Etni, Zera, Adaías,

42Etã, Zima, Simei,

43Jaate, Gerson e Levi.

44O segundo assistente de Hemã foi Etã, representante do clã de Merari, que se mantinha à sua esquerda. Os antepassados de Merari, retrospetivamente foram:

Quisi, Abdi, Maluque,

45Hasabias, Amazias, Hilquias,

46Amzi, Bani, Semer,

47Mali, Musi, Merari, Levi.

48Os seus parentes, todos os outros levitas, foram designados para várias tarefas no tabernáculo. 49Só Aarão e os seus descendentes foram sacerdotes. As suas responsabilidades incluíam os sacrifícios de holocaustos e de incenso, assim como os deveres respeitantes ao interior do santuário, o santo dos santos, o lugar santíssimo, e as tarefas relacionadas com o dia anual de resgate de Israel. Deviam zelar para que todos os detalhes ordenados por Moisés, o servo de Deus, fossem observados.

50Os descendentes de Aarão foram:

Eleazar, Fineias, Abisua,

51Buqui, Uzi, Zeraías,

52Meraiote, Amarias, Aitube,

53Zadoque e Aimaaz.

As cidades dos levitas

(Js 21.4-39)

54Segue-se o relato das cidades e terras atribuídas por sorteio aos descendentes de Aarão, todos membros do clã de Coate:

55Hebrom com os pastos em volta de Judá. 56(Ainda que os campos e os subúrbios tivessem sido dados a Calebe, filho de Jefoné). 57Também as seguintes cidades de refúgio com os pastos em redor: Libna, Jatir, Estemoa, 58Hilem, Debir, 59Asã e Bete-Semes.

60Treze outras povoações, incluindo os arredores de pastagens, entre as quais Geba, Alemete e Anatote, foram dadas aos sacerdotes pela tribo de Benjamim.

61Foram atribuídas por sorteio as terras para serem doadas aos descendentes de Coate que restaram, e receberam dez povoações no território da meia tribo de Manassés.

62Os subclãs de Gerson receberam treze cidades na área de Basã, da parte das tribos de Issacar, de Aser, de Naftali e de Manassés.

63Os subclãs de Merari receberam por sorteio doze cidades, da parte das tribos de Rúben, de Gad e de Zebulão.

64Mais povoações e pastagens em redor foram dadas aos levitas 65(que lhes puseram novos nomes) da parte das tribos de Judá, de Simeão e de Benjamim.

66A tribo de Efraim deu estas cidades de refúgio, com as suas pastagens, ao subclã de Coate:

67Siquem, nas colinas de Efraim, Gezer, 68Jocmeão, Bete-Horom, 69Aijalom e Gate-Rimom.

70As seguintes cidades de refúgio com as suas pastagens foram dadas aos subclãs dos coatitas pela meia tribo de Manassés: Aner e Balaão.

71Foram as seguintes cidades de refúgio, com as suas pastagens, dadas ao clã de Gerson pela meia tribo de Manassés:

Golã em Basã e Astarote.

72A tribo de Issacar deu-lhes Quedes, Daberate, 73Ramote e Anem, mais as pastagens em redor de cada uma.

74A tribo de Aser deu-lhes Abdom, Masal, 75Hucoque e Reobe, com as respetivas pastagens.

76A tribo de Naftali deu-lhes Quedes na Galileia, Hamom e Quiriataim, com as suas pastagens.

77A tribo de Zebulão deu Rimono e Tabor ao clã de Merari, como cidades de refúgio.

78Do outro lado do rio Jordão, em frente a Jericó, a tribo de Rúben deu-lhes Bezer, uma povoação do deserto de Jaaz, 79Quedemote e Mefaate, mais as pastagens ao redor de cada uma.

80A tribo de Gad deu-lhes Ramote em Gileade, Maanaim, 81Hesbom e Jazer, com as respetivas zonas de pastagens em redor.