1 ዜና መዋዕል 6 – NASV & HTB

New Amharic Standard Version

1 ዜና መዋዕል 6:1-81

ሌዊ

1የሌዊ ወንዶች ልጆች፤

ጌድሶን፣ ቀዓት፣ ሜራሪ።

2የቀዓት ወንዶች ልጆች፤

እንበረም፣ ይስዓር፣ ኬብሮን፣ ዑዝኤል።

3የእንበረም ልጆች፤

አሮን፣ ሙሴ፣ ማርያም።

የአሮን ወንዶች ልጆች፤

ናዳብ፣ አብዩድ፣ አልዓዛር፣ ኢታምር።

4አልዓዛር ፊንሐስን ወለደ፤

ፊንሐስ አቢሱን ወለደ፤

5አቢሱ ቡቂን ወለደ፤

ቡቂ ኦዚን ወለደ፤

6ኦዚ ዘራእያን ወለደ፤

ዘራእያ መራዮትን ወለደ፤

7መራዮት አማርያን ወለደ፤

አማርያ አኪጦብን ወለደ፤

8አኪጦብ ሳዶቅን ወለደ፤

9ሳዶቅ አኪማአስን ወለደ፤

አኪማአስ ዓዛርያስን ወለደ፤

ዓዛርያስ ዮሐናንን ወለደ፤

10ዮሐናን ዓዛርያስን ወለደ፤ እርሱም ሰሎሞን በኢየሩሳሌም ባሠራው ቤተ መቅደስ በክህነት ያገለገለ ነበር፤

11ዓዛርያስ አማርያን ወለደ፤

አማርያም አኪጦብን ወለደ፤

12አኪጦብ ሳዶቅን ወለደ፤

ሳዶቅ ሰሎምን ወለደ፤

13ሰሎም ኬልቅያስን ወለደ፤

ኬልቅያስ ዓዛርያስን ወለደ፤

14ዓዛርያስ ሠራያን ወለደ፤

ሠራያ ኢዮሴዴቅን ወለደ።

15እግዚአብሔር የይሁዳና የኢየሩሳሌም ሕዝብ በናቡከደነፆር እጅ ተማርከው እንዲወሰዱ ባደረገ ጊዜ ኢዮሴዴቅም አብሮ ተማርኮ ሄደ።

16የሌዊ ወንዶች ልጆች፤

ጌድሶን፣ ቀዓት፣ ሜራሪ።

17የጌድሶን ወንዶች ልጆች፤

ሎቤኒ፣ ሰሜኢ።

18የቀሃት ወንዶች ልጆች፤

እንበረም፣ ይስዓር፣ ኬብሮን፣ ዑዝኤል።

19የሜራሪ ወንዶች ልጆች፤

ሞሖሊ፣ ሙሲ።

በየአባቶቻቸው ቤተ ሰብ የተቈጠሩት የሌዊ ጐሣዎች የሚከተሉት ናቸው፤

20ከጌርሶን፤

ልጁ ሎቤኒ፣ ልጁ ኢኤት፣

ልጁ ዛማት፣ 21ልጁ ዮአክ፣

ልጁ አዶ፣ ልጁ ዛራ፣ ልጁ ያትራይ።

22የቀዓት ዘሮች፤

ልጁ አሚናዳብ፣ ልጁ ቆሬ፣

ልጁ አሴር፣ 23ልጁ ሕልቃና፣

ልጁ አቢሳፍ፣ ልጁ አሴር፣

24ልጁ ኢኢት፣ ልጁ ኡርኤል፣

ልጁ ዖዝያ፣ ልጁ ሳውል።

25የሕልቃና ዘሮች፤

አማሢ፣ አኪሞት።

26ልጁ ሕልቃና፣6፥26 አንዳንድ የዕብራይስጥ ቅጆች፣ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕምና የሱርስቱ ቅጅ ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ አብዛኞቹ የዕብራይስጥ ቅጆች ግን፣ ኪሞትና 26 ሕልቃና፤ የሕልቃና ወንዶች ልጆች፤ ልጁ ሱፊ፣

ልጁ ናሐት፣ 27ልጁ ኤልያብ፣

ልጁ ይሮሐም፣ ልጁ ሕልቃና፣

ልጁ ሳሙኤል6፥27 አንዳንድ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞች (እንዲሁም 1ሳሙ 1፥1920 እና 1ዜና 6፥3334 ይመ) ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ ዕብራይስጡ ግን፣ ልጁ ሳሙኤል የሚለውን ሐረግ አይጨምርም

28የሳሙኤል ወንዶች ልጆች፤

የበኵር ልጁ ኢዮኤል6፥28 አንዳንድ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞችና ሱርስቱ (እንዲሁም 1ሳሙ 8፥2 እና 1ዜና 6፥33 ይመ) ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ ዕብራይስጡ ግን፣ ኢዩኤል የሚለውን ስም አይጨምርም።

ሁለተኛው ልጁ አብያ።

29የሜራሪ ዘሮች፤

ሞሖሊ፣ ልጁ ሎቤኒ፣

ልጁ ሰሜኢ፣ ልጁ ዖዛ፣

30ልጁ ሳምዓ፣ ልጁ ሐግያ፣

ልጁ ዓሣያ።

የቤተ መቅደሱ መዘምራን

6፥54-80 ተጓ ምብ – ኢያ 21፥4-39

31ታቦቱ ከገባ በኋላ፣ ዳዊት የመዘምራን አለቃ አድርጎ በእግዚአብሔር ቤት የሾማቸው ሰዎች እነዚህ ናቸው፤ 32እነርሱም ሰሎሞን የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ በኢየሩሳሌም እስኪሠራ ድረስ፣ በማደሪያው፣ ይኸውም በመገናኛው ድንኳን ፊት ሆነው እየዘመሩ ያገለግሉ ነበር፤ አገልግሎታቸውንም የሚያከናውኑት በወጣላቸው ደንብ መሠረት ነው።

33ከወንዶች ልጆቻቸው ጋር ሆነው ያገለገሉ ሰዎች እነዚህ ናቸው፤

ከቀዓታውያን ልጆች፤ ዘማሪው ኤማን፣ የኢዮኤል ልጅ፣ የሳሙኤል ልጅ፣

34የሕልቃና ልጅ፣ የይሮሐም ልጅ፣

የኤሊኤል ልጅ፣ የቶዋ ልጅ፣

35የሱፍ ልጅ፣ የሕልቃና ልጅ፣

የመሐት ልጅ፣ የአማሢ ልጅ፣

36የሕልቃና ልጅ፣ የኢዮኤል ልጅ፣

የዓዛርያስ ልጅ፣ የሶፎንያስ ልጅ፣

37የታሐት ልጅ፣ የአሴር ልጅ፣

የአብያሳፍ ልጅ፣ የቆሬ ልጅ፣

38የይስዓር ልጅ፣ የቀዓት ልጅ፣

የሌዊ ልጅ፣ የእስራኤል ልጅ።

39እንዲሁም የሔማን ወንድም አሳፍ በስተ ቀኙ ሆኖ ያገለግል ነበር፤

አሳፍ የበራክያ ልጅ፣ የሳምዓ ልጅ፣

40የሚካኤል ልጅ፣ የበዓሤያ ልጅ፣

የመልክያ ልጅ፣ 41የኤትኒ ልጅ፣

የዛራ ልጅ፣ የዓዳያ ልጅ፣

42የኤታን ልጅ፣ የዛማት ልጅ፣

የሰሜኢ ልጅ፣ 43የኢኤት ልጅ፣

የጌድሶን ልጅ፣ የሌዊ ልጅ፤

44በስተ ግራቸው በኩል አብረዋቸው ያሉት የሜራሪ ልጆች፤

የቂሳ ልጅ ኤታን፣ የአብዲ ልጅ፣

የማሎክ ልጅ፣ 45የሐሸብያ ልጅ፣

የአሜስያስ ልጅ፣ የኬልቅያስ ልጅ፣

46የአማሲ ልጅ፣ የባኒ ልጅ፣

የሴሜር ልጅ፣ 47የሞሖሊ ልጅ፣

የሙሲ ልጅ የሜራሪ ልጅ፣

የሌዊ ልጅ።

48ሌዋውያን ወንድሞቻቸው ግን የእግዚአብሔርን ቤት የማደሪያ ድንኳን ተግባር እንዲያከናውኑ ተመድበው ነበር። 49የእግዚአብሔር ባሪያ ሙሴ ባዘዘው መሠረት፣ ስለ እስራኤል ማስተስረያ በቅድስተ ቅዱሳኑ ውስጥ የሚከናወነውን ተግባር ሁሉ፣ በመሠዊያው ላይ የሚቃጠል መሥዋዕትና በዕጣኑ መሠዊያ ላይ የሚቀርበውን መሥዋዕት የሚያቀርቡት ግን አሮንና ዘሮቹ ብቻ ነበሩ።

50የአሮን ዘሮች እነዚህ ነበሩ፤

ልጁ አልዓዛር፣ ልጁ ፊንሐስ፣

ልጁ አቢሱ 51ልጁ ቡቂ፣

ልጁ ኦዚ፣ ልጁ ዘራእያ፣

52ልጁ መራዮት፣ ልጁ አማርያ፣

ልጁ አኪጦብ፣ 53ልጁ ሳዶቅ፣

ልጁ አኪማአስ።

54መኖሪያዎቻቸው እንዲሆኑ የተመደቡላቸው ቦታዎች እነዚህ ናቸው፦ የመጀመሪያው ዕጣ የእነርሱ ስለሆነ፣ ከቀዓት ጐሣ ለሆኑት ለአሮን ዘሮች የተመደቡላቸው መኖሪያዎች እነዚህ ነበሩ።

55ለእነርሱም በይሁዳ ምድር የምትገኘው ኬብሮንና በዙሪያዋ ያለው የግጦሽ ቦታ ተሰጠ፤ 56በኬብሮን ዙሪያ የሚገኙት የዕርሻ ቦታዎችና መንደሮች ግን ለዮፎኒ ልጅ ለካሌብ ተሰጡ። 57ለአሮን ዘሮች የመማፀኛ ከተሞች የሆኑትን ኬብሮንን፣ ልብናን፣ የቲርን፣ ኤሽትሞዓን፣ 58ሖሎንን፣ ዳቤርን፣ 59ዓሳንን፣ ዮታን6፥59 የሱርስቱ ቅጅ (እንዲሁም የሰብዓ ሊቃናትና ኢያ 21፥16) ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ ዕብራይስጡ ግን፣ ዮታን የሚለውን ስም አይጨምርም።፣ ቤትሳሚስን ከነመሰማሪያዎቻቸው ሰጡ።

60ከብንያም ነገድ ድርሻ ላይ ገባዖንን፣6፥60 ኢያ 21፥17 ከዚህ ጋር ይስማማል፤ ዕብራይስጡ ግን ገባዖን የሚለውን ስም አይጨምርም። ጌባን፣ ጋሌማን፣ ዓናቶትን ከነመሰማሪያዎቻቸው ሰጡ።

ለቀዓት ዘሮች የተከፋፈሉት እነዚህ ከተሞች በአጠቃላይ ዐሥራ ሦስት ናቸው።

61ለቀሩት የቀዓት ዘሮች ደግሞ ከምናሴ ነገድ እኩሌታ ድርሻ ዐሥር ከተሞች ተሰጧቸው።

62ለጌድሶን ነገድ በየጐሣቸው ከይሳኮር፣ ከአሴር፣ ከንፍታሌምና በባሳን ከሚገኘው ከምናሴ ነገድ ድርሻ ላይ ዐሥራ ሦስት ከተሞች ተመደቡላቸው።

63ለሜራሪ ዘሮች በየጐሣቸው ከሮቤል፣ ከጋድና ከዛብሎን ድርሻ ላይ ዐሥራ ሁለት ከተሞች ተመደቡላቸው።

64እስራኤላውያንም ከተሞቹን በዚሁ ሁኔታ መድበው ከነመሰማሪያዎቻቸው ለሌዋውያኑ ሰጧቸው።

65ቀደም ብለው የተጠቀሱትንም ከተሞች ከይሁዳ፣ ከስምዖንና ከብንያም ነገድ ላይ ወስደው መደቡላቸው።

66ለአንዳንድ የቀዓት ጐሣዎችም ከኤፍሬም ነገድ ድርሻ ላይ የሚኖሩበት ቦታ ተሰጣቸው።

67በኰረብታማው በኤፍሬም ምድር የሚገኙትን የመማፀኛ ከተሞች ሴኬምን፣ ጌዝርን፣ 68ዮቅምዓምን፣ ቤትሖሮን፣ 69ኤሎንንና ጋትሪሞን ከነመሰማሪያዎቻቸው ሰጧቸው።

70እንዲሁም እስራኤላውያን ከምናሴ ነገድ እኩሌታ ድርሻ ላይ ዓኔርና ቢልዓም የተባሉትን ከተሞች ከነመሰማሪያዎቻቸው ወስደው ለቀሩት የቀዓት ጐሣዎች ሰጧቸው።

71ጌድሶናውያን ከዚህ የሚከተሉትን ከተሞች ወሰዱ፤

ከምናሴ ነገድ እኩሌታ፣ በባሳን የሚገኘውን ጎላንና አስታሮትን ከነመሰማሪያዎቻቸው ወሰዱ፤

72ከይሳኮርም ነገድ፣ ቃዴስን፣ ዳብራትን 73ራሞትንና ዓኔምናን ከነመሰማሪያዎቻቸው ወሰዱ፤

74ከአሴር ነገድ መዓሳልን፣ ዓብዶን፣ 75ሑቆቅንና፣ ረአብን ከነመሰማሪያዎቻቸው ወሰዱ፤

76ከንፍታሌም ነገድ በገሊላ የሚገኘውን ቃዴስን፣ ሐሞንንና፣ ቂርያታይምን ከነመሰማሪያዎቻቸው ወሰዱ።

77ከሌዋውያን የቀሩት የሜራሪ ጐሣዎች ደግሞ ከዚህ የሚከተለውን ወሰዱ፤

ከዛብሎን ነገድ ዮቅኒዓምን፣ ቀርታህን፣6፥77 የሰብዓ ሊቃናት ትርጕምንና ኢያ 21፥34 ይመ፤ ዕብራይስጡ ግን፣ ዮቅኒዓምን፣ ቀርታህን የሚለውን አይጨምርም። ሬሞንና፣ ታቦርን ከነመሰማሪያዎቻቸው ወሰዱ።

78ከዮርዳኖስ ወንዝ ማዶ ከኢያሪኮ በስተ ምሥራቅ ከሚገኘው ከሮቤል ነገድ፣

በምድረ በዳ የሚገኘውን ቦሶርን፣ ያሳን፣ 79ቅዴሞትንና ሜፍዓትን ከነመሰማሪያዎቻቸው ወሰዱ፤

80ከጋድ ነገድ በገለዓድ የምትገኘውን ሬማትን፣ መሃናይምን፣ 81ሐሴቦንና ኢያዜርን ከነመሰማሪያዎቻቸው ወሰዱ።

Het Boek

1 Kronieken 6:1-81

De nakomelingen van Levi

1Hier volgen de namen van de zonen van Levi: Gersom, Kehat en Merari. 2Kehats zonen waren Amram, Jishar, Hebron en Uzziël. 3Amrams kinderen waren Aäron, Mozes en Mirjam. Aärons zonen waren Nadab, Abihu, Eleazar en Itamar. 4-10De oudste zonen van de elkaar opvolgende generaties van Aäron waren: Eleazar, de vader van Pinechas, de vader van Abisua, de vader van Bukki, de vader van Uzzi, de vader van Zerahja, de vader van Merajoth, de vader van Amarja, de vader van Ahitub, de vader van Zadok, de vader van Ahimaäz, de vader van Azarja, de vader van Johanan, de vader van Azarja, die hogepriester was van de tempel in Jeruzalem, die door Salomo was gebouwd.

11-15Deze Azarja was de vader van Amarja, de vader van Ahitub, de vader van Zadok, de vader van Sallum, de vader van Hilkia, de vader van Azarja, de vader van Seraja, de vader van Jozadak.

Jozadak werd balling, toen de Here het volk van Juda en Jeruzalem gevangen liet nemen door Nebukadnezar.

16Zoals hierboven aangegeven, waren Gersom, Kehat en Merari de zonen van Levi. 17De zonen van Gersom waren Libni en Simi. 18De zonen van Kehat waren Amram, Jishar, Hebron en Uzziël.

19-21De zonen van Merari waren Machli en Musi. De families van de Levieten waren als volgt naar hun gezinshoofden verdeeld: in de familie van Gersom: Libni, Jahath, Zimma, Joah, Iddo, Zarah en Jeathrai. 22-24In de familie van Kehat: Amminadab, Korach, Assir, Elkana, Ebjasaf, Assir, Tachat, Uriël, Uzzia en Saul. 25-27Het gezin van Elkana was verder verdeeld in de volgende gezinnen van zijn zonen Amasai, Ahimoth, Elkana, Zofai, Nachat, Eliab, Jeroham en Elkana. 28De gezinnen van de familie van Samuël werden geleid door Samuëls zonen: Joël, de oudste, en Abia, de tweede zoon. 29-30 De gezinnen van de familie van Merari werden geleid door zijn zonen Machli, Libni, Simi, Uzza, Simea, Haggia en Asaja.

31Koning David wees deze mannen als koorleiders aan en liet koren vormen om God in de tabernakel te prijzen, nadat hij daar de ark een plaats had gegeven. 32Totdat Salomo de tempel in Jeruzalem had gebouwd, gingen zij daar door met het leiden van de samenzang.

33-38Hier volgen de namen van de nakomelingen van de koorleiders: de zanger Heman kwam uit de familie van Kehat en zijn geslachtsregister ging terug via de volgende personen: Joël, Samuël, Elkana, Jeroham, Eliël, Toah, Suf, Elkana, Mahath, Amassai, Elkana, Joël, Azarja, Zefanja, Tachat, Assir, Ebjasaf, Korach, Jishar, Kehat, Levi en Israël. 39-43Hemans helper was Asaf, wiens stamboom terugging via Berechja, Simea, Michaël, Baëseja, Malkia, Ethni, Zerach, Adaja, Ethan, Zimma, Simi, Jahath, Gersom en Levi. 44-47Hemans tweede helper was Ethan, een lid van de familie van Merari, die aan zijn linkerhand stond. Ethans stamboom liep terug via Kisi, Abdi, Malluch, Hasabja, Amazia, Hilkia, Amzi, Bani, Semer, Machli, Musi, Merari en Levi.

48Hun familieleden, alle andere Levieten, waren belast met allerlei andere taken in de tabernakel. 49Maar alleen Aäron en zijn nakomelingen waren priesters. Tot hun taken behoorde het offeren van brandoffers en reukwerk, alle werkzaamheden die te maken hadden met het binnenste heiligdom, het Heilige der Heiligen, voor de verzoening van Israël met de Here. Zij zorgden ervoor dat alle aanwijzingen die Gods dienaar Mozes had gegeven, werden opgevolgd.

50-53De nakomelingen van Aäron waren Eleazar, Pinechas, Abisua, Bukki, Uzzi, Zerahja, Merajoth, Amarja, Ahitub, Zadok en Ahimaäz. 54Door middel van het lot werden aan de nakomelingen van Aäron die deel uitmaakten van de familie van Kehat, 55de vrijstad Hebron in Juda met de weidegronden er omheen toegewezen. 56-57 Maar de velden en omringende dorpen werden aan Kaleb, de zoon van Jefunne, gegeven. 58-59 De nakomelingen van Aäron kregen ook de volgende steden met weidegronden er omheen: Libna, Jattir, Estemoa, Hilen, Debir, Asan en Bet-Semes. 60Dertien andere steden met het omringende grasland, inclusief Geba, Alemeth en Anathoth, werden door de stam van Benjamin aan de priesters toegewezen. 61Daarna werd er geloot om de verdeling van het land van de overgebleven nakomelingen van de familie van Kehat te regelen en zij kregen tien steden in het gebied van de stam van Manasse.

62De gezinnen van de familie van Gersom kregen door middel van het lot dertien steden in het gebied van Basan van de stammen Issachar, Aser, Naftali en Manasse. 63De gezinnen van de Merari-familie kregen op diezelfde manier twaalf steden van de stammen Ruben, Gad en Zebulon. 64-65 Ook de stammen Juda, Simeon en Benjamin stelden op deze manier door middel van het lot steden beschikbaar aan de Levieten. De namen van deze steden werden daarbij hardop genoemd.

66-69De stam van Efraïm gaf de volgende vrijsteden met het omringende grasland aan de overgebleven gezinnen van de Kehat-familie: Sichem, de vrijstad in het gebergte Efraïm, Gezer, Jokmeam, Bet-Horon, Ajalon en Gath-Rimmon. 70De volgende vrijsteden met het omringende grasland kwamen in handen van de gezinnen van de Kehatieten uit het bezit van de stam van Manasse: Aner en Bileam.

71De vrijsteden met het omringende grasland die de stam van Manasse aan de gezinnen van de Gersom-familie gaf, waren: de vrijstad Golan in Basan en Astharoth. 72De stam van Issachar gaf hun Kedes, Dobrath, 73Ramot en Anem, met uiteraard de omringende weidegronden. 74De stam van Aser gaf hun Masal, Abdon, 75Hukok en Rechob, weer met het omringende grasland. 76De stam van Naftali gaf hun Kedes in Galilea, Hammon en Kirjataïm met het bijbehorende grasland. 77Van de stam van Zebulon kregen zij de steden Rimmono en Tabor. 78-79 Aan de overkant van de Jordaan, tegenover Jericho, gaf de stam van Ruben hun Beser, een woestijnstad, Jahza, Kedemoth en Mefaäth, met de daarbij behorende weidegronden. 80De stam van Gad gaf hun ten slotte Ramot in Gilead, Machanaïm, 81Chesbon en Jazer. Ook hier kregen zij de erbij behorende weidegronden bij.