1 ዜና መዋዕል 6 – NASV & BPH

New Amharic Standard Version

1 ዜና መዋዕል 6:1-81

ሌዊ

1የሌዊ ወንዶች ልጆች፤

ጌድሶን፣ ቀዓት፣ ሜራሪ።

2የቀዓት ወንዶች ልጆች፤

እንበረም፣ ይስዓር፣ ኬብሮን፣ ዑዝኤል።

3የእንበረም ልጆች፤

አሮን፣ ሙሴ፣ ማርያም።

የአሮን ወንዶች ልጆች፤

ናዳብ፣ አብዩድ፣ አልዓዛር፣ ኢታምር።

4አልዓዛር ፊንሐስን ወለደ፤

ፊንሐስ አቢሱን ወለደ፤

5አቢሱ ቡቂን ወለደ፤

ቡቂ ኦዚን ወለደ፤

6ኦዚ ዘራእያን ወለደ፤

ዘራእያ መራዮትን ወለደ፤

7መራዮት አማርያን ወለደ፤

አማርያ አኪጦብን ወለደ፤

8አኪጦብ ሳዶቅን ወለደ፤

9ሳዶቅ አኪማአስን ወለደ፤

አኪማአስ ዓዛርያስን ወለደ፤

ዓዛርያስ ዮሐናንን ወለደ፤

10ዮሐናን ዓዛርያስን ወለደ፤ እርሱም ሰሎሞን በኢየሩሳሌም ባሠራው ቤተ መቅደስ በክህነት ያገለገለ ነበር፤

11ዓዛርያስ አማርያን ወለደ፤

አማርያም አኪጦብን ወለደ፤

12አኪጦብ ሳዶቅን ወለደ፤

ሳዶቅ ሰሎምን ወለደ፤

13ሰሎም ኬልቅያስን ወለደ፤

ኬልቅያስ ዓዛርያስን ወለደ፤

14ዓዛርያስ ሠራያን ወለደ፤

ሠራያ ኢዮሴዴቅን ወለደ።

15እግዚአብሔር የይሁዳና የኢየሩሳሌም ሕዝብ በናቡከደነፆር እጅ ተማርከው እንዲወሰዱ ባደረገ ጊዜ ኢዮሴዴቅም አብሮ ተማርኮ ሄደ።

16የሌዊ ወንዶች ልጆች፤

ጌድሶን፣ ቀዓት፣ ሜራሪ።

17የጌድሶን ወንዶች ልጆች፤

ሎቤኒ፣ ሰሜኢ።

18የቀሃት ወንዶች ልጆች፤

እንበረም፣ ይስዓር፣ ኬብሮን፣ ዑዝኤል።

19የሜራሪ ወንዶች ልጆች፤

ሞሖሊ፣ ሙሲ።

በየአባቶቻቸው ቤተ ሰብ የተቈጠሩት የሌዊ ጐሣዎች የሚከተሉት ናቸው፤

20ከጌርሶን፤

ልጁ ሎቤኒ፣ ልጁ ኢኤት፣

ልጁ ዛማት፣ 21ልጁ ዮአክ፣

ልጁ አዶ፣ ልጁ ዛራ፣ ልጁ ያትራይ።

22የቀዓት ዘሮች፤

ልጁ አሚናዳብ፣ ልጁ ቆሬ፣

ልጁ አሴር፣ 23ልጁ ሕልቃና፣

ልጁ አቢሳፍ፣ ልጁ አሴር፣

24ልጁ ኢኢት፣ ልጁ ኡርኤል፣

ልጁ ዖዝያ፣ ልጁ ሳውል።

25የሕልቃና ዘሮች፤

አማሢ፣ አኪሞት።

26ልጁ ሕልቃና፣6፥26 አንዳንድ የዕብራይስጥ ቅጆች፣ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕምና የሱርስቱ ቅጅ ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ አብዛኞቹ የዕብራይስጥ ቅጆች ግን፣ ኪሞትና 26 ሕልቃና፤ የሕልቃና ወንዶች ልጆች፤ ልጁ ሱፊ፣

ልጁ ናሐት፣ 27ልጁ ኤልያብ፣

ልጁ ይሮሐም፣ ልጁ ሕልቃና፣

ልጁ ሳሙኤል6፥27 አንዳንድ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞች (እንዲሁም 1ሳሙ 1፥1920 እና 1ዜና 6፥3334 ይመ) ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ ዕብራይስጡ ግን፣ ልጁ ሳሙኤል የሚለውን ሐረግ አይጨምርም

28የሳሙኤል ወንዶች ልጆች፤

የበኵር ልጁ ኢዮኤል6፥28 አንዳንድ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞችና ሱርስቱ (እንዲሁም 1ሳሙ 8፥2 እና 1ዜና 6፥33 ይመ) ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ ዕብራይስጡ ግን፣ ኢዩኤል የሚለውን ስም አይጨምርም።

ሁለተኛው ልጁ አብያ።

29የሜራሪ ዘሮች፤

ሞሖሊ፣ ልጁ ሎቤኒ፣

ልጁ ሰሜኢ፣ ልጁ ዖዛ፣

30ልጁ ሳምዓ፣ ልጁ ሐግያ፣

ልጁ ዓሣያ።

የቤተ መቅደሱ መዘምራን

6፥54-80 ተጓ ምብ – ኢያ 21፥4-39

31ታቦቱ ከገባ በኋላ፣ ዳዊት የመዘምራን አለቃ አድርጎ በእግዚአብሔር ቤት የሾማቸው ሰዎች እነዚህ ናቸው፤ 32እነርሱም ሰሎሞን የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ በኢየሩሳሌም እስኪሠራ ድረስ፣ በማደሪያው፣ ይኸውም በመገናኛው ድንኳን ፊት ሆነው እየዘመሩ ያገለግሉ ነበር፤ አገልግሎታቸውንም የሚያከናውኑት በወጣላቸው ደንብ መሠረት ነው።

33ከወንዶች ልጆቻቸው ጋር ሆነው ያገለገሉ ሰዎች እነዚህ ናቸው፤

ከቀዓታውያን ልጆች፤ ዘማሪው ኤማን፣ የኢዮኤል ልጅ፣ የሳሙኤል ልጅ፣

34የሕልቃና ልጅ፣ የይሮሐም ልጅ፣

የኤሊኤል ልጅ፣ የቶዋ ልጅ፣

35የሱፍ ልጅ፣ የሕልቃና ልጅ፣

የመሐት ልጅ፣ የአማሢ ልጅ፣

36የሕልቃና ልጅ፣ የኢዮኤል ልጅ፣

የዓዛርያስ ልጅ፣ የሶፎንያስ ልጅ፣

37የታሐት ልጅ፣ የአሴር ልጅ፣

የአብያሳፍ ልጅ፣ የቆሬ ልጅ፣

38የይስዓር ልጅ፣ የቀዓት ልጅ፣

የሌዊ ልጅ፣ የእስራኤል ልጅ።

39እንዲሁም የሔማን ወንድም አሳፍ በስተ ቀኙ ሆኖ ያገለግል ነበር፤

አሳፍ የበራክያ ልጅ፣ የሳምዓ ልጅ፣

40የሚካኤል ልጅ፣ የበዓሤያ ልጅ፣

የመልክያ ልጅ፣ 41የኤትኒ ልጅ፣

የዛራ ልጅ፣ የዓዳያ ልጅ፣

42የኤታን ልጅ፣ የዛማት ልጅ፣

የሰሜኢ ልጅ፣ 43የኢኤት ልጅ፣

የጌድሶን ልጅ፣ የሌዊ ልጅ፤

44በስተ ግራቸው በኩል አብረዋቸው ያሉት የሜራሪ ልጆች፤

የቂሳ ልጅ ኤታን፣ የአብዲ ልጅ፣

የማሎክ ልጅ፣ 45የሐሸብያ ልጅ፣

የአሜስያስ ልጅ፣ የኬልቅያስ ልጅ፣

46የአማሲ ልጅ፣ የባኒ ልጅ፣

የሴሜር ልጅ፣ 47የሞሖሊ ልጅ፣

የሙሲ ልጅ የሜራሪ ልጅ፣

የሌዊ ልጅ።

48ሌዋውያን ወንድሞቻቸው ግን የእግዚአብሔርን ቤት የማደሪያ ድንኳን ተግባር እንዲያከናውኑ ተመድበው ነበር። 49የእግዚአብሔር ባሪያ ሙሴ ባዘዘው መሠረት፣ ስለ እስራኤል ማስተስረያ በቅድስተ ቅዱሳኑ ውስጥ የሚከናወነውን ተግባር ሁሉ፣ በመሠዊያው ላይ የሚቃጠል መሥዋዕትና በዕጣኑ መሠዊያ ላይ የሚቀርበውን መሥዋዕት የሚያቀርቡት ግን አሮንና ዘሮቹ ብቻ ነበሩ።

50የአሮን ዘሮች እነዚህ ነበሩ፤

ልጁ አልዓዛር፣ ልጁ ፊንሐስ፣

ልጁ አቢሱ 51ልጁ ቡቂ፣

ልጁ ኦዚ፣ ልጁ ዘራእያ፣

52ልጁ መራዮት፣ ልጁ አማርያ፣

ልጁ አኪጦብ፣ 53ልጁ ሳዶቅ፣

ልጁ አኪማአስ።

54መኖሪያዎቻቸው እንዲሆኑ የተመደቡላቸው ቦታዎች እነዚህ ናቸው፦ የመጀመሪያው ዕጣ የእነርሱ ስለሆነ፣ ከቀዓት ጐሣ ለሆኑት ለአሮን ዘሮች የተመደቡላቸው መኖሪያዎች እነዚህ ነበሩ።

55ለእነርሱም በይሁዳ ምድር የምትገኘው ኬብሮንና በዙሪያዋ ያለው የግጦሽ ቦታ ተሰጠ፤ 56በኬብሮን ዙሪያ የሚገኙት የዕርሻ ቦታዎችና መንደሮች ግን ለዮፎኒ ልጅ ለካሌብ ተሰጡ። 57ለአሮን ዘሮች የመማፀኛ ከተሞች የሆኑትን ኬብሮንን፣ ልብናን፣ የቲርን፣ ኤሽትሞዓን፣ 58ሖሎንን፣ ዳቤርን፣ 59ዓሳንን፣ ዮታን6፥59 የሱርስቱ ቅጅ (እንዲሁም የሰብዓ ሊቃናትና ኢያ 21፥16) ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ ዕብራይስጡ ግን፣ ዮታን የሚለውን ስም አይጨምርም።፣ ቤትሳሚስን ከነመሰማሪያዎቻቸው ሰጡ።

60ከብንያም ነገድ ድርሻ ላይ ገባዖንን፣6፥60 ኢያ 21፥17 ከዚህ ጋር ይስማማል፤ ዕብራይስጡ ግን ገባዖን የሚለውን ስም አይጨምርም። ጌባን፣ ጋሌማን፣ ዓናቶትን ከነመሰማሪያዎቻቸው ሰጡ።

ለቀዓት ዘሮች የተከፋፈሉት እነዚህ ከተሞች በአጠቃላይ ዐሥራ ሦስት ናቸው።

61ለቀሩት የቀዓት ዘሮች ደግሞ ከምናሴ ነገድ እኩሌታ ድርሻ ዐሥር ከተሞች ተሰጧቸው።

62ለጌድሶን ነገድ በየጐሣቸው ከይሳኮር፣ ከአሴር፣ ከንፍታሌምና በባሳን ከሚገኘው ከምናሴ ነገድ ድርሻ ላይ ዐሥራ ሦስት ከተሞች ተመደቡላቸው።

63ለሜራሪ ዘሮች በየጐሣቸው ከሮቤል፣ ከጋድና ከዛብሎን ድርሻ ላይ ዐሥራ ሁለት ከተሞች ተመደቡላቸው።

64እስራኤላውያንም ከተሞቹን በዚሁ ሁኔታ መድበው ከነመሰማሪያዎቻቸው ለሌዋውያኑ ሰጧቸው።

65ቀደም ብለው የተጠቀሱትንም ከተሞች ከይሁዳ፣ ከስምዖንና ከብንያም ነገድ ላይ ወስደው መደቡላቸው።

66ለአንዳንድ የቀዓት ጐሣዎችም ከኤፍሬም ነገድ ድርሻ ላይ የሚኖሩበት ቦታ ተሰጣቸው።

67በኰረብታማው በኤፍሬም ምድር የሚገኙትን የመማፀኛ ከተሞች ሴኬምን፣ ጌዝርን፣ 68ዮቅምዓምን፣ ቤትሖሮን፣ 69ኤሎንንና ጋትሪሞን ከነመሰማሪያዎቻቸው ሰጧቸው።

70እንዲሁም እስራኤላውያን ከምናሴ ነገድ እኩሌታ ድርሻ ላይ ዓኔርና ቢልዓም የተባሉትን ከተሞች ከነመሰማሪያዎቻቸው ወስደው ለቀሩት የቀዓት ጐሣዎች ሰጧቸው።

71ጌድሶናውያን ከዚህ የሚከተሉትን ከተሞች ወሰዱ፤

ከምናሴ ነገድ እኩሌታ፣ በባሳን የሚገኘውን ጎላንና አስታሮትን ከነመሰማሪያዎቻቸው ወሰዱ፤

72ከይሳኮርም ነገድ፣ ቃዴስን፣ ዳብራትን 73ራሞትንና ዓኔምናን ከነመሰማሪያዎቻቸው ወሰዱ፤

74ከአሴር ነገድ መዓሳልን፣ ዓብዶን፣ 75ሑቆቅንና፣ ረአብን ከነመሰማሪያዎቻቸው ወሰዱ፤

76ከንፍታሌም ነገድ በገሊላ የሚገኘውን ቃዴስን፣ ሐሞንንና፣ ቂርያታይምን ከነመሰማሪያዎቻቸው ወሰዱ።

77ከሌዋውያን የቀሩት የሜራሪ ጐሣዎች ደግሞ ከዚህ የሚከተለውን ወሰዱ፤

ከዛብሎን ነገድ ዮቅኒዓምን፣ ቀርታህን፣6፥77 የሰብዓ ሊቃናት ትርጕምንና ኢያ 21፥34 ይመ፤ ዕብራይስጡ ግን፣ ዮቅኒዓምን፣ ቀርታህን የሚለውን አይጨምርም። ሬሞንና፣ ታቦርን ከነመሰማሪያዎቻቸው ወሰዱ።

78ከዮርዳኖስ ወንዝ ማዶ ከኢያሪኮ በስተ ምሥራቅ ከሚገኘው ከሮቤል ነገድ፣

በምድረ በዳ የሚገኘውን ቦሶርን፣ ያሳን፣ 79ቅዴሞትንና ሜፍዓትን ከነመሰማሪያዎቻቸው ወሰዱ፤

80ከጋድ ነገድ በገለዓድ የምትገኘውን ሬማትን፣ መሃናይምን፣ 81ሐሴቦንና ኢያዜርን ከነመሰማሪያዎቻቸው ወሰዱ።

Bibelen på hverdagsdansk

1. Krønikebog 6:1-66

Øvrige berømte efterkommere af Levi

1Som allerede nævnt havde Levi sønnerne Gershon, Kehat og Merari. 2Gershon havde to sønner: Libni og Shimi. 3Kehat havde som nævnt fire sønner: Amram, Jitzhar, Hebron og Uzziel. 4Merari havde to sønner: Mahli og Mushi.

5Blandt Gershons efterkommere var der følgende slægtsoverhoveder: Libni, Jahat, Zimma, 6Joa, Iddo, Zerach og Jeateraj.

7Blandt Kehats efterkommere var der følgende slægtsoverhoveder: Amminadab,6,7 Sandsynligvis skulle der have stået Jitzhar, jf. 2.Mos. 6,21-24 og 4.Mos. 16,1. Kora, Assir, 8Elkana, Ebjasaf, Assir, 9Tahat, Uriel, Uzzija og Shaul.

10Blandt Elkanas efterkommere var der følgende: Amasaj, Ahimot, 11Elkana, Zofaj, Nahat, 12Eliab, Jeroham, Elkana og Samuel.

13Samuel fik to sønner: den første hed Joel og den anden Abija.

14Blandt Meraris efterkommere var der følgende slægtsoverhoveder: Mahli, Libni, Shimi, Uzza, 15Shima, Haggija og Asaja.

Tempelmusikerne af Levis stamme

16-17Kong David udvalgte en gruppe levitter til at stå for lovsangen og musikken i det telt, han havde rejst på Zions bjerg, og hvor han havde anbragt pagtens ark. De udførte deres tjeneste efter de retningslinier, David havde givet dem, indtil Salomon byggede templet.

18-23Tre ledere blev udvalgt til at stå for sangen og musikken sammen med deres sønner. Den øverste leder var Heman af Kehats slægt. Han kunne føre sin slægt tilbage til patriarken Jakob fra sin far, Joel, over Samuel, Elkana, Jeroham, Eliel, Toa, Zuf, Elkana, Mahat, Amasaj, Elkana, Joel, Azarja, Zefanja, Tahat, Assir, Ebjasaf, Kora, Jitzhar, Kehat, Levi til Jakob.

24-28Den næstøverste leder var Asaf af Gershons slægt. Han kunne føre sin slægt tilbage til Levi fra sin far, Berekja, over Shima, Mikael, Ba’aseja, Malkija, Etni, Zerach, Adaja, Etan, Zimma, Shimi, Jahat, Gershon til Levi.

29-32Den tredje leder blev Etan af Meraris slægt. Han kunne føre sin slægt tilbage til Levi fra sin far, Kishi, over Abdi, Malluk, Hashabja, Amatzja, Hilkija, Amzi, Bani, Shemer, Mahli, Mushi, Merari til Levi.

33De øvrige levitter fik hver deres opgave i tjenesten ved Guds telt.

Præsternes opgave

34Det var kun Arons efterkommere, der fik lov at gøre tjeneste som præster. Det var deres opgave at brænde røgelse og ofre brændofre på alteret, og kun ypperstepræsten måtte træde frem for Gud inde i det allerhelligste rum og skaffe soning for folkets synder. Præsterne var ansvarlige for, at de regler og forskrifter, som Gud havde givet sin tjener Moses, blev overholdt til punkt og prikke.

35-38Præsteslægten fra Aron og fremover var som før nævnt: Eleazar, Pinehas, Abishua, Bukki, Uzzi, Zerahja, Merajot, Amarja, Ahitub, Zadok og Ahima’atz.

De byer, der blev givet til Arons slægt og de øvrige levitter

39En række byer og områder blev ved hjælp af de hellige lodder tildelt Arons præsteslægt, som var en del af Kehat-slægten. 40-44Først fik de Hebron i Judas stammeområde med tilhørende græsmarker—de øvrige marker og omliggende landsbyer tilhørte Kaleb, Jefunnes søn. Hebron var en af tilflugtsbyerne. Dernæst fik de i Judas område tildelt Libna, Jattir, Eshtemoa, Hilen,6,40-44 Det samme som „Holon”, jf. Jos. 21,15. Debir, Ashan, Jutta6,40-44 Indføjet fra Jos. 21,16, som har en mere nøjagtig liste. og Bet-Shemesh—alle med tilhørende græsmarker. 45Fra Benjamins stammeområde fik Arons slægt tildelt byerne Gibeon,6,45 Ordet „Gibeon” er faldet ud af teksten her, men indføjet fra Jos. 21,17. Der var altså ni byer fra Judas område og fire fra Benjamins, i alt 13 byer. Geba, Alemet og Anatot med tilhørende græsmarker. Det var i alt 13 byer. 46Derefter fik Kehats øvrige efterkommere ved lodtrækning tildelt ti byer fra Efraims og Dans område samt fra Manasses halve stamme vest for Jordan.6,46 Ordene „fra Efraims og Dans område” er faldet ud af teksten her, men hentet fra parallelstedet i Jos. 21,5. Der var to byer fra Manasse, fire fra Efraim og fire fra Dan, i alt 10, jf. de nærmere detaljer i vers 51-55 og Jos. 21,20-25.

47Gershons efterkommere fik slægt for slægt tildelt 13 byer i Issakars, Ashers og Naftalis område og i Bashan, hvor Manasses anden halve stamme boede.

48Meraris efterkommere fik slægt for slægt tildelt 12 byer i de områder, hvor Rubens, Gads og Zebulons stammer boede.

49Israelitterne tildelte altså ved lodtrækning levitterne en række byer med tilhørende græsmarker. 50Præsterne fik byer tildelt fra Judas, Simeons og Benjamins stammeområder.6,50 Levitterne fik ingen jord, fordi de ikke skulle dyrke jorden, men leve af gaver fra de øvrige stammer. Dog fik de nogle byer, for de skulle jo have et sted at bo og græsmarker til deres husdyr. Præsterne fik de byer, der lå nærmest ved helligdommen i Jerusalem.

51Kehats efterkommere fik som sagt tildelt en række byer fra Efraims stammeområde: 52Det var tilflugtsbyen Sikem i Efraims højland, samt Gezer, 53Jokmeam og Bet-Horon. 54De fik også Ajjalon og Gat-Rimmon6,54 En del af teksten er faldet ud, jf. Jos. 21,23-24.—alle byer kom med de tilhørende græsmarker. 55Manasses halve stamme mod vest afstod byerne Aner og Bileam med tilhørende græsmarker.

56Blandt de byer, Gershons efterkommere fik tildelt, var Golan og Ashtarot med tilhørende græsmarker fra Manasses halve stamme i Bashan øst for Jordan. 57-58Af Issakars stamme fik de Kedesh, Daberat, Jarmut og En-Gannim med tilhørende græsmarker. 59-60Af Ashers stamme fik de Mashal, Abdon, Hukok og Rehob med tilhørende græsmarker. 61Af Naftalis stamme fik de Kedesh i Galilæa, Hammot og Kirjatajim med tilhørende græsmarker.

62Meraris efterkommere fik tildelt Rimmon og Tabor med tilhørende græsmarker af Zebulons stamme. 63-64Fra Rubens stamme øst for Jordanfloden, over for Jeriko, fik de ørkenbyen Betzer samt Jatza, Kedemot og Mefa’at—alle med tilhørende græsmarker. 65-66Gads stamme gav dem Ramot i Gilead, Mahanajim, Heshbon og Jazer—alle med tilhørende græsmarker.