1 ዜና መዋዕል 4 – NASV & OL

New Amharic Standard Version

1 ዜና መዋዕል 4:1-43

ሌሎቹ የይሁዳ ጐሣዎች

1የይሁዳ ዘሮች፤

ፋሬስ፣ ኤስሮም፣ ከርሚ፣ ሆር፣ ሦባል።

2የሦባል ልጅ ራያ ኢኤትን ወለደ፤ ኢኤት ደግሞ አሑማይንና ላሃድን ወለደ፤ እነዚህም የጾርዓውያን ጐሣዎች ናቸው።

3የኤጣም ወንዶች ልጆች4፥3 አንዳንድ የሰብዓ ሊቃናት ቅጆች (እንዲሁም ቩልጌት ይመ) ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ ዕብራይስጡ ግን፣ አባት ይላል እነዚህ ናቸው፤

ኢይዝራኤል፣ ይሽማ፣ ይደባሽ። እኅታቸው ሃጽሌልፎኒ ትባላለች። 4ፋኑኤል ጌዶርን ወለደ፤ ኤጽር ደግሞ ሑሻምን ወለደ4፥4 ቃል በቃል ሲተረጐም አባት ሆነ ማለት ነው፤ ይህም ምናልባት፣ አባት ማለት፣ የጐሣው፣ እንዝላት፣ እንጅላት ወይም፣ መሠረት መሆኑን የሚያመለክት ነው። እነዚህ የኤፍራታ የበኵር ልጅና የቤተ ልሔም አባት የሆነው የሆር ዘሮች ናቸው።

5የቴቁሔ አባት አሽሑር፣ ሔላና ነዕራ የተባሉ ሁለት ሚስቶች ነበሩት።

6ነዕራም አሑዛምን፣ ኦፌርን፣ ቴምኒን፣ አሐሽታሪን ወለደችለት፤ የነዕራ ዘሮች እነዚህ ነበሩ።

7የሔላ ወንዶች ልጆች፤

ዴሬት፣ ይጽሐር፣ ኤትናን ናቸው። 8የቆጽ ወንዶች ልጆች ዓኑብ፣ ጾቤባና፣ የሃሩም ልጅ የአሐርሔል ጐሳዎች ናቸው።

9ያቤጽ ከወንድሞቹ ይልቅ የተከበረ ሰው ነበረ፤ እናቱም “በጣር የወለድሁት” ስትል ስሙን ያቤጽ አለችው። 10ያቤጽም፣ “አቤቱ፤ እንድትባርከኝ፣ ግዛቴንም እንድታሰፋልኝ እለምንሃለሁ፤ እጅህ ከእኔ ጋር ትሁን፤ ከሥቃይና ከጕዳትም ጠብቀኝ” በማለት ወደ እስራኤል አምላክ ጮኸ። እግዚአብሔርም የለመነውን ሰጠው።

11የሹሐ ወንድም ክሉብ ምሒርን ወለደ፤ ምሒርም ኤሽቶን ወለደ። 12ኤሽቶን ቤትራፋንና ፋሴሐን ወለደ፤ የዒር ናሐሽን ከተሞች የቈረቈረ እርሱ ነው4፥12 ወይም፣ የዒር ናሐሽ አባት ነው። እነዚህ የሬካ ሰዎች ናቸው።

13የቄኔዝ ወንዶች ልጆች፤

ጎቶንያል፣ ሠራያ።

የጎቶንያል ወንዶች ልጆች፤

ሐታት፣ መዖኖታይ4፥13 አንዳንድ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞችና የቩልጌት ቅጅ ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ ዕብራይስጡ ግን፣ መዖኖታይ የሚለውን አይጨምርም።14መዖኖታይ ደግሞ ዖፍራን ወለደ።

ሠራያ የኢዮአብ አባት ሲሆን፣ ኢዮአብ ጌሐራሺምን4፥14 ጌሐራሺም ማለት የእደ ጥበብ ሸለቆ ማለት ነው። ወለደ፤ የጥበበ እድ ባለሙያዎች ስለ ነበሩ ይህ ስም ተሰጣቸው።

15የዮፎኔ ልጅ የካሌብ ወንዶች ልጆች፤

ዒሩ፣ ኤላ፣ ነዓም።

የኤላ ልጅ፤

ቄኔዝ።

16የይሃሌልኤል ወንዶች ልጆች፤

ዚፍ፣ ዚፋ፣ ቲርያ፣ አሣርኤል።

17የዕዝራ ወንዶች ልጆች፤

ዬቴር፣ ሜሬድ፣ ዔፌር፣ ያሎን።

ከሜሬድ ሚስቶች አንዲቱ ማርያምን፣ ሸማይንና የኤሽትምዓን አባት ይሽባን ወለደች። 18አይሁዳዊት ሚስቱም የጌዶርን አባት ዮሬድን፣ የሦኮን አባት ሔቤርን፣ የዛኖዋን አባት ይቁቲኤልን ወለደች፤ እነዚህም ሜሬድ ያገባት የፈርዖን ልጅ የቢትያ ልጆች ናቸው።

19የሆዲያ ሚስት የነሐም እኅት ወንዶች ልጆች፤

የገርሚው የቅዒላ አባት፣ ማዕካታዊው ኤሽትሞዓ።

20የሺሞን ወንዶች ልጆች፤

አምኖን፣ ሪና፣ ቤንሐናን፣ ቲሎን። የይሺዒ ዘሮች፤ ዞሔትና ቤንዞሔት።

21የይሁዳ ልጅ የሴሎም ወንዶች ልጆች፤

የሌካ አባት ዔር፣ የመሪሳና በቤት አሽቤዓ የበፍታ ጨርቅ ሠሪ የሆኑት ጐሣዎች አባት ለዓዳ፣

22ዮቂም፣ የኮዜባ ሰዎች፣ ኢዮአስ፣ ሞዓብን የገዛ ሣራፍና ያሹቢሌሔም። ታሪካቸውም ጥንታዊነት ያለው ነው። 23ሰዎቹ በነጣዒምና በጋዴራ የሚቀመጡ ሸክላ ሠሪዎች ነበሩ፤ በዚያም በመቀመጥ ለንጉሡ ሸክላ ይሠሩ ነበር።

ስምዖን

4፥28-33 ተጓ ምብ – ኢያ 19፥2-10

24የስምዖን ዘሮች፤

ነሙኤል፣ ያሚን፣ ያሪን፣ ዛራ፣ ሳኡል፤

25ሰሎም የሳኡል ልጅ ነው፤ መብሳም የሰሎም ልጅ ነው፤

ማስማዕ ደግሞ የመብሳም ልጅ ነው።

26የማስማዕ ዘሮች፤

ልጁ ሃሙኤል፣ ልጁ ዘኩር፣ ልጁ ሰሜኢ።

27ሰሜኢ ዐሥራ ስድስት ወንዶችና ስድስት ሴቶች ልጆች ነበሩት፤ ወንድሞቹ ግን ብዙ ልጆች አልነበሯቸውም፤ ስለዚህ ጐሣቸው በሙሉ እንደ ይሁዳ ሕዝብ ብዙ አልነበረም። 28የኖሩባቸውም ቦታዎች እነዚህ ናቸው፦ ቤርሳቤህ፣ ሞላዳ፣ ሐጻርሹዓል፣ 29ቢልሃ፣ ዔጼም፣ ቶላድ፣ 30ቤቱኤል፣ ሔርማ፣ ጺቅላግ፣ 31ቤትማርካቦት፣ ሐጸርሱሲም፣ ቤት ቢሪ፣ ሽዓራይም፤ እስከ ዳዊት ዘመነ መንግሥት ድረስ የኖሩት በእነዚህ ከተሞች ነው። 32በአካባቢያቸው የሚገኙት መንደሮች ደግሞ ኤጣም፣ ዐይን፣ ሬሞን፣ ቶኬን፣ ዓሻን የተባሉ አምስት ከተሞች ናቸው፤ 33በእነዚህም ከተሞች ዙሪያ እስከ ባኣል የሚዘልቁ መንደሮች ነበሩ፤ መኖሪያቸው በዚሁ ሲሆን፣ የትውልድ መዝገብም አላቸው።

34ሞሾባብ፣ የምሌክ፣

የአሜስያስ ልጅ ኢዮስያስ፣ 35ኢዮኤል፣

የዮሺብያ ልጅ፣ የሠራያ ልጅ፣ የዓሢኤል ልጅ ኢዩ

36እንዲሁም ኤልዩዔናይ፣ ያዕቆባ፣ የሾሐያ፣

ዓሣያ፣ ዓዲዔል፣ ዩሲምኤል፣ በናያስ፣

37የሺፊ ልጅ ዚዛ፣ የአሎን ልጅ፣ የይዳያ ልጅ፣ የሺምሪ ልጅ፣ የሸማያ ልጅ።

38እነዚህ ስማቸው ከላይ የተዘረዘረው ሰዎች የየጐሣቸው መሪዎች ነበሩ፤ የየቤተ ሰባቸውም ብዛት እጅግ በጣም እየጨመረ ሄደ፤ 39እነርሱም ለከብቶቻቸው ግጦሽ ፍለጋ ከሸለቆው በስተ ምሥራቅ እስካለው እስከ ጌዶር መግቢያ ድረስ ዘልቀው ሄዱ። 40በዚያም ለምለምና ያማረ የግጦሽ ቦታ አገኙ፤ ምድሪቱም ሰፊ፣ ሰላምና ጸጥታ የሰፈነባት ነበረች። በቀድሞ ዘመን በዚህ ምድር ይኖሩ የነበሩት አንዳንድ የካም ዘሮች ናቸው።

41እነዚህ ስማቸው ከላይ የተዘረዘረው ወደዚህ ቦታ የመጡት በይሁዳ ንጉሥ በሕዝቅያስ ዘመን ነበረ፤ እነርሱም በድንኳኖቻቸው ውስጥ በነበሩት በካም ወገኖችና በምዑናውያን ላይ አደጋ በመጣል ፈጽመው አጠፏቸው4፥41 የዕብራይስጡ ቃል አንድን ሰው ወይም ነገር ሙሉ በሙሉ በማጥፋት ለእግዚአብሔር መስጠትን ያመለክታል።፤ ይህም እስከ ዛሬ ድረስ በግልጽ ይታያል። ለመንጎቻቸው በቂ የግጦሽ ቦታ ስላገኙም፣ በዚያ መኖር ጀመሩ። 42ከእነዚሁ አምስት መቶ የሚሆኑ የስምዖን ወገኖች በይሽዒ ልጆች በፈላጥያ፣ በነዓርያ፣ በረፋያና በዑዝኤል ተመርተው የሴይርን ኰረብታማ አገር ወረሩ። 43አምልጠው የቀሩትን አማሌቃውያን ፈጅተው እስከ ዛሬ በዚያው ይኖራሉ።

O Livro

1 Crónicas 4:1-43

Outros descendentes de Judá

1Estes foram os filhos de Judá:

Perez, Hezrom, Carmi, Hur e Sobal.

2Sobal teve um filho, Reaías, que foi pai de Jaate, o antepassado de Aumai e de Laade. Estes são conhecidos como as famílias dos zorateus.

3Os descendentes de Etã foram:

Jezreel, Isma, Idbas e Hazelelponi, sua filha. 4Ainda Penuel, pai de Gedor, e Ezer, pai Husá, filhos de Hur, o filho mais velho de Efrata, que foi o pai de Belém.

5Acheúr, o pai de Tecoa, teve duas mulheres: Hela e Naará.

6Naará deu à luz Auzão, Hefer, Temeni e Haastari.

7Hela deu-lhe

Zerete, Izar e Etnã. 8Coz foi pai de Anube e de Zobeba; foi também o antepassado das famílias chamadas pelo nome de Aarel, filho de Harum.

9Jabez foi o mais ilustre de todos os seus irmãos. A sua mãe chamou-lhe Jabez, porque teve um parto muito difícil. 10Este invocou o Deus de Israel e orou desta maneira: “Peço-te que me concedas as tuas maravilhosas bênçãos e que me favoreças no meu trabalho! Sê comigo em tudo o que fizer. Guarda-me do mal e das desgraças!” Deus respondeu ao seu pedido.

11-12Os descendentes de Reca foram: Quelube, irmão de Suá, cujo filho foi Meir, o pai de Estom; Estom foi pai de Bete-Rafa, de Paseia e de Teina; Teina foi pai de Ir-Naás.

13Os filhos de Quenaz foram

Otniel e Seraías.

Otniel teve como filhos

Hatate e Menotai. 14Menotai foi pai de Ofra;

Seraías foi pai de Joabe, o antepassado dos habitantes do vale dos Artífices, assim chamado porque ali se concentrou um grande número de artesãos.

15Os filhos de Calebe, filho de Jefoné, foram:

Iru, Elá e Naã. Um dos filhos de Elá foi Quenaz.

16Foram filhos de Jealelel:

Zife, Zifa, Tiria e Asareel.

17-18Os filhos de Ezra foram os seguintes:

Jeter, Merede, Efer e Jalom.

Merede casou-se com Bitia, princesa egípcia, que foi mãe de Miriam, de Samai e de Isbá, antepassado de Estemoa.

A mulher de Estemoa foi uma judia, que se tornou a mãe de Jarede, Heber e Jecutiel, que foram respetivamente os antepassados dos gedoritas, dos socoitas e dos zanoaitas.

19Hodias teve por mulher a irmã de Naã.

Um dos seus filhos foi o pai de Queila, o garmita; e outro foi pai de Estemoa, o maacatita.

20Os filhos de Simão foram os seguintes:

Amnom, Rina, Bene-Hanã e Tilom.

Foram filhos de Isi:

Zoete e Bene-Zoete.

21Os filhos de Sela, filho de Judá, foram:

Er, pai de Leca, Lada, pai de Maressa, as famílias dos operários do linho que trabalhavam em Bete-Asbeia, e ainda:

22Joquim, mais as famílias Cozeba, Joás, Sarafe, o qual foi chefe em Moabe antes de voltar para Leem. Todos estes nomes foram obtidos através de registos muito antigos. 23Estas famílias ficaram conhecidas por serem oleiros que viviam em Netaim e Gedera; todos trabalhavam para o rei.

A descendência de Simeão

(Js 19.2-9)

24Os filhos de Simeão foram:

Nemuel, Jamim, Jaribe, Zera e Saul.

25O filho de Saul chamou-se Salum, o seu neto Mibsão e o seu bisneto Misma.

26Os filhos de Misma incluíam

Hamuel, pai de Zacur e avô de Simei.

27Simei teve dezasseis filhos e seis filhas; no entanto, nenhum dos seus irmãos teve grandes famílias; todos eles tiveram poucos filhos; menos do que era normal em Judá. 28Habitaram em Berseba, em Molada, em Hazar-Sual, 29em Bila, em Ezem, em Tolade, 30em Betuel, em Horma, em Ziclague, 31em Bete-Marcabote, em Hazar-Susim, em Bete-Biri e em Saaraim. Estas foram as povoações que estiveram sob o seu controlo até ao tempo de David. 32Os descendentes habitaram também perto ou nas seguintes localidades: Etã, Aim, Rimom, Toquem e Asã. 33Algumas não ficavam muito longe de Baal. Tudo isto está relatado nas suas genealogias.

34-39Estes são os nomes de alguns dos príncipes das prósperas famílias que peregrinaram até ao oriente do vale de Gedor, procurando melhores pastos para o seu gado:

Mesobabe, Jamleque,

Josa, filho de Amazias, Joel,

Jeú, filho de Jossibias,

Elioenai, Jaacobá, Jesoaías,

Asaías, Adiel, Jesimiel, Benaia,

Ziza, filho de Sifi, filho de Alom, filho de Jedaías, filho de Simri, filho de Semaías.

40Acharam boas pastagens, terra espaçosa e fértil. Mas aquela zona pertencia aos descendentes de Cam.

41Por isso, durante o reinado de Ezequias, rei de Judá, esses príncipes, atrás nomeados, invadiram a terra e destruíram as tendas e as habitações dos meunitas; mataram os habitantes da terra e ali se estabeleceram. 42Mais tarde, 500 destes invasores da tribo de Simeão foram para as montanhas de Seir. Os seus líderes eram Pelatias, Nearias, Refaías e Uziel, todos filhos de Isi. 43Destruíram os poucos amalequitas que ainda restavam e ficaram a viver ali.