1 ዜና መዋዕል 3 – NASV & NIV

New Amharic Standard Version

1 ዜና መዋዕል 3:1-24

የዳዊት ወንዶች ልጆች

3፥1-4 ተጓ ምብ – 2ሳሙ 3፥2-5

3፥5-8 ተጓ ምብ – 2ሳሙ 5፥14-161ዜና 14፥4-7

1ዳዊት በኬብሮን ሳለ የወለዳቸው ወንዶች ልጆች እነዚህ ነበሩ፤

ከኢይዝራኤላዊቷ ከአኪናሆም የተወለደው የበኵር ልጁ አምኖን፣

ሁለተኛው፣ ከቀርሜሎሳዊቷ ከአቢግያ የተወለደው ዳንኤል፣

2ሦስተኛው ከጌሹር ንጉሥ ከተልማይ ልጅ ከመዓካ የተወለደው አቤሴሎም፣

አራተኛው የአጊት ልጅ አዶንያስ፣

3አምስተኛው የአቢጣል ልጅ ሰፋጥያስ፣

ስድስተኛው ከሚስቱ ከዔግላ የተወለደው ይትረኃም።

4እነዚህ ስድስቱ የተወለዱት ዳዊት በኬብሮን ሆኖ ሰባት ዓመት ተኩል በገዛበት ጊዜ ነበር።

ዳዊት በኢየሩሳሌም ሠላሳ ሦስት ዓመት ነገሠ፤ 5በዚያም የወለዳቸው ልጆች እነዚህ ነበሩ፤

ሳሙስ፣3፥5 ዕብራይስጡ፣ ሺማ ይላል፤ ሻሙአ ከሚለው ጋር አንድ ነው። ሶባብ፣ ናታን፣ ሰሎሞን፤ እነዚህ አራት ወንዶች ልጆች ከዓሚኤል ልጅ ከቤርሳቤህ የተወለዱ ናቸው።

6እንዲሁም ሌሎች ወንዶች ልጆች ነበሩት፤ ስማቸውም ኢያቤሐር፣ ኤሊሱዔ፣ ኤሊፋላት፣ 7ኖጋ፣ ናፌቅ፣ ያፍያ፣ 8ኤሊሳማ፣ ኤሊዳሄ፣ ኤሊፋላት ይባላል፤ በአጠቃላይ ዘጠኝ ነበሩ።

9ከቁባቶቹ ከወለዳቸው ወንዶች ልጆች ሌላ እነዚህ ሁሉ ልጆቹ ነበሩ፤ እነዚህም ትዕማር የምትባል እኅት ነበረቻቸው።

የይሁዳ ነገሥታት

10የሰሎሞን ልጅ ሮብዓም ነበረ፤

የሮብዓም ልጅ አቢያ፣

የአቢያ ልጅ አሳ፣

የአሳ ልጅ ኢዮሣፍጥ፣

11የኢዮሣፍጥ ልጅ ኢዮራም፣

የኢዮራም ልጅ አካዝያስ፣

የአካዝያስ ልጅ ኢዮአስ፣

12የኢዮአስ ልጅ አሜስያስ፣

የአሜስያስ ልጅ ዓዛርያስ፣

የዓዛርያስ ልጅ ኢዮአታም፣

13የኢዮአታም ልጅ አካዝ፣

የአካዝ ልጅ ሕዝቅያስ፣

የሕዝቅያስ ልጅ ምናሴ፣

14የምናሴ ልጅ አሞጽ፣

የአሞጽ ልጅ ኢዮስያስ።

15የኢዮስያስ ወንዶች ልጆች፤

በኵሩ ዮሐናን፣

ሁለተኛ ልጁ ኢዮአቄም፣

ሦስተኛ ልጁ ሴዴቅያስ፣

አራተኛ ልጁ ሰሎም።

16የኢዮአቄም ዘሮች፤

ልጁ ኢኮንያ፣

ልጁ ሴዴቅያስ።

ከምርኮ በኋላ የነበረው የነገሥታቱ የትውልድ ሐረግ

17የምርኮኛው የኢኮንያን ዘሮች፤

ልጁ ሰላትያል፣ 18መልኪራም፣ ፈዳያ፣ ሼናጻር፣ ይቃምያ፣ ሆሻማ፣ ነዳብያ።

19የፈዳያ ወንዶች ልጆች፤

ዘሩባቤል፣ ሰሜኢ።

የዘሩባቤል ወንዶች ልጆች፤

ሜሱላም፣ ሐናንያ፤ እኅታቸው ሰሎሚት ትባላለች። 20ሌሎችም አምስት ልጆች ነበሩ፤ እነርሱም ሐሹባ፣ ኦሄል፣ በራክያ፣ ሐሳድያ፣ ዮሻብሒሴድ።

21የሐናንያ ዘሮች፤

ፈላጥያ፣ የሻያ፤ እንዲሁም የረፋያ፣ የአርናን፣ የአብድዩና የሴኬንያ ወንዶች ልጆች።

22የሴኬንያ ዘሮች፤

ሸማያና ወንዶች ልጆቹ፤ ሐጡስ፣ ይግአል፣ ባሪያሕ፣ ነዓርያ፣ ሻፋጥ፤ በአጠቃላይ ስድስት ነበሩ።

23የነዓርያ ወንዶች ልጆች፤

ኤልዮዔናይ፣ ሕዝቅያስ፣ ዓዝሪቃም፤ በአጠቃላይ ሦስት ነበሩ።

24የኤልዩዔናይም ወንዶች ልጆች፤

ሆዳይዋ፣ ኤልያሴብ፣ ፌልያ፣ ዓቁብ፣ ዮሐናን፣ ደላያ፣ ዓናኒ፤ በአጠቃላይ ሰባት ናቸው።

New International Version

1 Chronicles 3:1-24

The Sons of David

1These were the sons of David born to him in Hebron:

The firstborn was Amnon the son of Ahinoam of Jezreel;

the second, Daniel the son of Abigail of Carmel;

2the third, Absalom the son of Maakah daughter of Talmai king of Geshur;

the fourth, Adonijah the son of Haggith;

3the fifth, Shephatiah the son of Abital;

and the sixth, Ithream, by his wife Eglah.

4These six were born to David in Hebron, where he reigned seven years and six months.

David reigned in Jerusalem thirty-three years, 5and these were the children born to him there:

Shammua,3:5 Hebrew Shimea, a variant of Shammua Shobab, Nathan and Solomon. These four were by Bathsheba3:5 One Hebrew manuscript and Vulgate (see also Septuagint and 2 Samuel 11:3); most Hebrew manuscripts Bathshua daughter of Ammiel. 6There were also Ibhar, Elishua,3:6 Two Hebrew manuscripts (see also 2 Samuel 5:15 and 1 Chron. 14:5); most Hebrew manuscripts Elishama Eliphelet, 7Nogah, Nepheg, Japhia, 8Elishama, Eliada and Eliphelet—nine in all. 9All these were the sons of David, besides his sons by his concubines. And Tamar was their sister.

The Kings of Judah

10Solomon’s son was Rehoboam,

Abijah his son,

Asa his son,

Jehoshaphat his son,

11Jehoram3:11 Hebrew Joram, a variant of Jehoram his son,

Ahaziah his son,

Joash his son,

12Amaziah his son,

Azariah his son,

Jotham his son,

13Ahaz his son,

Hezekiah his son,

Manasseh his son,

14Amon his son,

Josiah his son.

15The sons of Josiah:

Johanan the firstborn,

Jehoiakim the second son,

Zedekiah the third,

Shallum the fourth.

16The successors of Jehoiakim:

Jehoiachin3:16 Hebrew Jeconiah, a variant of Jehoiachin; also in verse 17 his son,

and Zedekiah.

The Royal Line After the Exile

17The descendants of Jehoiachin the captive:

Shealtiel his son, 18Malkiram, Pedaiah, Shenazzar, Jekamiah, Hoshama and Nedabiah.

19The sons of Pedaiah:

Zerubbabel and Shimei.

The sons of Zerubbabel:

Meshullam and Hananiah.

Shelomith was their sister.

20There were also five others:

Hashubah, Ohel, Berekiah, Hasadiah and Jushab-Hesed.

21The descendants of Hananiah:

Pelatiah and Jeshaiah, and the sons of Rephaiah, of Arnan, of Obadiah and of Shekaniah.

22The descendants of Shekaniah:

Shemaiah and his sons:

Hattush, Igal, Bariah, Neariah and Shaphat—six in all.

23The sons of Neariah:

Elioenai, Hizkiah and Azrikam—three in all.

24The sons of Elioenai:

Hodaviah, Eliashib, Pelaiah, Akkub, Johanan, Delaiah and Anani—seven in all.