1 ዜና መዋዕል 3 – NASV & NAV

New Amharic Standard Version

1 ዜና መዋዕል 3:1-24

የዳዊት ወንዶች ልጆች

3፥1-4 ተጓ ምብ – 2ሳሙ 3፥2-5

3፥5-8 ተጓ ምብ – 2ሳሙ 5፥14-161ዜና 14፥4-7

1ዳዊት በኬብሮን ሳለ የወለዳቸው ወንዶች ልጆች እነዚህ ነበሩ፤

ከኢይዝራኤላዊቷ ከአኪናሆም የተወለደው የበኵር ልጁ አምኖን፣

ሁለተኛው፣ ከቀርሜሎሳዊቷ ከአቢግያ የተወለደው ዳንኤል፣

2ሦስተኛው ከጌሹር ንጉሥ ከተልማይ ልጅ ከመዓካ የተወለደው አቤሴሎም፣

አራተኛው የአጊት ልጅ አዶንያስ፣

3አምስተኛው የአቢጣል ልጅ ሰፋጥያስ፣

ስድስተኛው ከሚስቱ ከዔግላ የተወለደው ይትረኃም።

4እነዚህ ስድስቱ የተወለዱት ዳዊት በኬብሮን ሆኖ ሰባት ዓመት ተኩል በገዛበት ጊዜ ነበር።

ዳዊት በኢየሩሳሌም ሠላሳ ሦስት ዓመት ነገሠ፤ 5በዚያም የወለዳቸው ልጆች እነዚህ ነበሩ፤

ሳሙስ፣3፥5 ዕብራይስጡ፣ ሺማ ይላል፤ ሻሙአ ከሚለው ጋር አንድ ነው። ሶባብ፣ ናታን፣ ሰሎሞን፤ እነዚህ አራት ወንዶች ልጆች ከዓሚኤል ልጅ ከቤርሳቤህ የተወለዱ ናቸው።

6እንዲሁም ሌሎች ወንዶች ልጆች ነበሩት፤ ስማቸውም ኢያቤሐር፣ ኤሊሱዔ፣ ኤሊፋላት፣ 7ኖጋ፣ ናፌቅ፣ ያፍያ፣ 8ኤሊሳማ፣ ኤሊዳሄ፣ ኤሊፋላት ይባላል፤ በአጠቃላይ ዘጠኝ ነበሩ።

9ከቁባቶቹ ከወለዳቸው ወንዶች ልጆች ሌላ እነዚህ ሁሉ ልጆቹ ነበሩ፤ እነዚህም ትዕማር የምትባል እኅት ነበረቻቸው።

የይሁዳ ነገሥታት

10የሰሎሞን ልጅ ሮብዓም ነበረ፤

የሮብዓም ልጅ አቢያ፣

የአቢያ ልጅ አሳ፣

የአሳ ልጅ ኢዮሣፍጥ፣

11የኢዮሣፍጥ ልጅ ኢዮራም፣

የኢዮራም ልጅ አካዝያስ፣

የአካዝያስ ልጅ ኢዮአስ፣

12የኢዮአስ ልጅ አሜስያስ፣

የአሜስያስ ልጅ ዓዛርያስ፣

የዓዛርያስ ልጅ ኢዮአታም፣

13የኢዮአታም ልጅ አካዝ፣

የአካዝ ልጅ ሕዝቅያስ፣

የሕዝቅያስ ልጅ ምናሴ፣

14የምናሴ ልጅ አሞጽ፣

የአሞጽ ልጅ ኢዮስያስ።

15የኢዮስያስ ወንዶች ልጆች፤

በኵሩ ዮሐናን፣

ሁለተኛ ልጁ ኢዮአቄም፣

ሦስተኛ ልጁ ሴዴቅያስ፣

አራተኛ ልጁ ሰሎም።

16የኢዮአቄም ዘሮች፤

ልጁ ኢኮንያ፣

ልጁ ሴዴቅያስ።

ከምርኮ በኋላ የነበረው የነገሥታቱ የትውልድ ሐረግ

17የምርኮኛው የኢኮንያን ዘሮች፤

ልጁ ሰላትያል፣ 18መልኪራም፣ ፈዳያ፣ ሼናጻር፣ ይቃምያ፣ ሆሻማ፣ ነዳብያ።

19የፈዳያ ወንዶች ልጆች፤

ዘሩባቤል፣ ሰሜኢ።

የዘሩባቤል ወንዶች ልጆች፤

ሜሱላም፣ ሐናንያ፤ እኅታቸው ሰሎሚት ትባላለች። 20ሌሎችም አምስት ልጆች ነበሩ፤ እነርሱም ሐሹባ፣ ኦሄል፣ በራክያ፣ ሐሳድያ፣ ዮሻብሒሴድ።

21የሐናንያ ዘሮች፤

ፈላጥያ፣ የሻያ፤ እንዲሁም የረፋያ፣ የአርናን፣ የአብድዩና የሴኬንያ ወንዶች ልጆች።

22የሴኬንያ ዘሮች፤

ሸማያና ወንዶች ልጆቹ፤ ሐጡስ፣ ይግአል፣ ባሪያሕ፣ ነዓርያ፣ ሻፋጥ፤ በአጠቃላይ ስድስት ነበሩ።

23የነዓርያ ወንዶች ልጆች፤

ኤልዮዔናይ፣ ሕዝቅያስ፣ ዓዝሪቃም፤ በአጠቃላይ ሦስት ነበሩ።

24የኤልዩዔናይም ወንዶች ልጆች፤

ሆዳይዋ፣ ኤልያሴብ፣ ፌልያ፣ ዓቁብ፣ ዮሐናን፣ ደላያ፣ ዓናኒ፤ በአጠቃላይ ሰባት ናቸው።

Ketab El Hayat

أخبار الأيام الأول 3:1-24

أسرة داود

1وَهَذَا سِجِلٌّ بِمَوَالِيدِ دَاوُدَ الَّذِينَ أَنْجَبَهُمْ فِي حَبْرُونَ: بِكْرُهُ أَمْنُونُ مِنْ أَخِينُوعَمَ الْيَزْرَعِيلِيَّةِ، ثُمَّ دَانِيئِيلُ مِنْ أَبِيجَايِلَ الْكَرْمَلِيَّةِ، 2وَالثَّالِثُ أَبْشَالُومُ بْنُ مَعْكَةَ بِنْتِ تَلْمَايَ مَلِكِ جَشُورَ، وَالرَّابِعُ أَدُونِيَّا بْنُ حَجِّيثَ، 3وَالْخَامِسُ شَفَطْيَا مِنْ أَبِيطَالَ، وَالسَّادِسُ يَثَرْعَامُ مِنْ عَجْلَةَ زَوْجَتِهِ. 4فَكَانَتْ جُمْلَةُ الْمَوْلُودِينَ لَهُ فِي حَبْرُونَ سِتَّةَ أَبْنَاءٍ، وَقَدْ مَلَكَ هُنَاكَ سَبْعَ سِنِينَ وَسِتَّةَ أَشْهُرٍ، ثُمَّ مَلَكَ فِي أُورُشَلِيمَ ثَلاثاً وَثَلاثِينَ سَنَةً. 5أَمَّا الَّذِينَ أَنْجَبَهُمْ فِي أُورُشَلِيمَ فَهُمْ: شِمْعَى وَشُوبَابُ وَنَاثَانُ وَسُلَيْمَانُ، وَهَؤُلاءِ الأَرْبَعَةُ وَلَدَتْهُمْ بَثْشَبَعُ بِنْتُ عَمِّيئِيلَ. 6وَكَانَ لَهُ تِسْعَةُ أَبْنَاءٍ آخَرُونَ هُمْ يِبْحَارُ وَأَلِشَامَعُ وَأَلِيفَالَطُ، 7وَنُوجَهُ وَنَافَجُ وَيَافِيعُ، 8وَأَلِيشَمَعُ وَأَلِيَادَاعُ وَأَلِيفَلَطُ. 9وَجَمِيعُهُمْ أَبْنَاءُ دَاوُدَ مَاعَدَا أَبْنَاءَ الْمَحْظِيَّاتِ. وَكَانَتْ لَهُمْ أُخْتٌ تُدْعَى ثَامَارَ.

ملوك يهوذا

10وَهَذِهِ أَسْمَاءُ أَبْنَاءِ سُلَيْمَانَ وَأَحْفَادِهِ عَلَى التَّعَاقُبِ الَّذِينَ تَوَالَوْا عَلَى الْمُلْكِ: رَحَبْعَامُ، أَبِيَّا، آسَا، يَهُوشَافَاطُ، 11يُورَامُ، أَخَزْيَا، يُوآشُ، 12أَمَصْيَا، عَزَرْيَا، يُوثَامُ، 13آحَازُ، حَزَقِيَّا، مَنَسَّى، 14آمُونُ وَيُوشِيَّا. 15أَمَّا أَبْنَاءُ يُوشِيَّا فَهُمْ: الْبِكْرُ يُوحَانَانُ، ثُمَّ يَهُويَاقِيمُ، وَصِدْقِيَّا، وَأَخِيراً شَلُّومُ. 16وَابْنَا يَهُويَاقِيمُ يَكُنْيَا وَصِدْقِيَّا.

النسل الملكي بعد السبي

17وَأَنْجَبَ يَكُنْيَا: أَسِيرَ وَشَأَلْتِيئِيلَ (وَمِنْ أَحْفَادِ يَهُويَاقِيمَ): 18مَلْكِيرَامُ وَفَدَايَا وَشِنْأَصَّرُ وَيَقَمْيَا وَهُوشَامَاعُ وَنَدَبْيَا. 19وَأَنْجَبَ فَدَايَا: زَرُبَّابَلَ وَشِمْعِي. أَمَّا أَبْنَاءُ زَرُبَّابَلَ فَهُمْ مَشُلّامُ، وَحَنَنْيَا وَأُخْتُهُمْ شَلُومِيَةُ، 20وَحَشُوبَةُ وَأُوهَلُ، وَبَرَخْيَا وَحَسَدْيَا، وَيُوشَبُ حَسَدَ، وَهُمْ خَمْسَةٌ في جُمْلَتِهِمْ. 21وَابْنَا حَنَنْيَا: فَلَطْيَا، وَيِشْعِيَا، وَمِنْ أَحْفَادِهِ: أَبْنَاءُ رَفَايَا وَأَرْنَانَ وَعُوبَدْيَا وَشَكَنْيَا. 22وَأَنْجَبَ شَكُنْيَا شَمْعِيَا؛ وَأَبْنَاءُ شَمْعِيَا الْخَمْسَةُ هُمْ: حَطُّوشُ وَيَجْآلُ وَبَارِيحُ وَنَعَرْيَا وَشَافَاطُ. 23وَكَانَ لِنَعَرْيَا ثَلاثَةُ أَبْنَاءٍ هُمْ: أَلْيُوعِينِيُّ، وَحَزَقِيَّا، وَعَزْرِيقَامُ. 24أَمَّا أَبْنَاءُ الْيُوعِينِيِّ فَهُمْ هُودَايَاهُو وَأَلِيَاشِيبُ وَفَلايَا وَعَقُّوبُ وَيُوحَانَانُ وَدَلايَا وَعَنَانِي. وَهُمْ سَبْعَةٌ.