1 ዜና መዋዕል 27 – NASV & PCB

New Amharic Standard Version

1 ዜና መዋዕል 27:1-34

የሰራዊቱ ዋና ዋና ክፍሎች

1የእስራኤል የቤተ ሰብ አለቆች፣ የሻለቆች፣ የመቶ አለቆች እንዲሁም ዓመቱን ሙሉ በየወሩ የሚመደቡትን ዋና ዋና ክፍሎች በተመለከተ ንጉሡን ያገለገሉ አለቆቻቸው ዝርዝር ይህ ነው። እያንዳንዱ ዋና ክፍል ሃያ አራት ሺሕ ሰው ነበረው።

2በመጀመሪያው ወር፣ የመጀመሪያው ዋና ክፍል የበላይ የዘብድኤል ልጅ ያሾብዓም ሲሆን፣ በሥሩ የሚታዘዙ ሃያ አራት ሺሕ ሰዎች ነበሩ። 3እርሱም የፋሬስ ዘር ሲሆን፣ በመጀመሪያው ወር የሰራዊቱ ሹማምት ሁሉ የበላይ ነበር።

4በሁለተኛው ወር፣ የክፍለ ጦሩ የበላይ አዛዥ አሆሃዊው ዱዲ ሲሆን፣ የዚሁ ክፍል መሪ ደግሞ ሚቅሎት ነው፤ በሥሩም ሃያ አራት ሺሕ ሰው ነበረ።

5በሦስተኛውም ወር፣ የሦስተኛው ክፍለ ጦር የበላይ አዛዥ የካህኑ የዮዳሄ ልጅ በናያስ ነበረ፤ ዋናው እርሱ ሲሆን፣ በሥሩ ሃያ አራት ሺሕ ሰው ነበረ። 6ይህም ከሠላሳዎቹ ይልቅ ኀያል ሲሆን፣ የሠላሳዎቹ የበላይ ነበረ፤ ልጁ ዓሚዛ ባድም የክፍሉ ሰራዊት አዛዥ ነበረ።

7በአራተኛው ወር፣ አራተኛው የበላይ አዛዥ የኢዮአብ ወንድም አሣሄል ሲሆን፣ በእግሩ የተተካውም ልጁ ዝባድያ ነው፤ በሥሩም ሃያ አራት ሺሕ ሰው ነበረ።

8በአምስተኛው ወር፣ አምስተኛው የበላይ አዛዥ ይዝራዊው ሸምሁት ሲሆን፣ በሥሩም ሃያ አራት ሺሕ ሰው ነበረ።

9በስድስተኛው ወር፣ ስድስተኛው የበላይ አዛዥ የቴቁሐዊው የዒስካ ልጅ ዒራስ ሲሆን፣ በሥሩም ሃያ አራት ሺሕ ሰው ነበረ።

10በሰባተኛው ወር፣ ሰባተኛው የበላይ አዛዥ የኤፍሬም ወገን የሆነው ፍሎናዊው ሴሌስ ሲሆን፣ በሥሩም ሃያ አራት ሺሕ ሰው ነበረ።

11በስምንተኛው ወር፣ ስምንተኛው የበላይ አዛዥ ከካዛራውያን ወገን የሆነው ኩሳታዊው ሲቦካይ ሲሆን፣ በሥሩም ሃያ አራት ሺሕ ሰው ነበረ።

12በዘጠነኛው ወር፣ ዘጠነኛው የበላይ አዛዥ ከብንያም ወገን የሆነው ዓናቶታዊው አቢዔዜር ሲሆን፣ በሥሩም ሃያ አራት ሺሕ ሰው ነበረ።

13በዐሥረኛው ወር፣ ዐሥረኛው የበላይ አዛዥ ከከዛራውያን ወገን የሆነው ነጦፋዊው ኖኤሬ ሲሆን፣ በሥሩም ሃያ አራት ሺሕ ሰው ነበረ።

14በዐሥራ አንደኛው ወር፣ ዐሥራ አንደኛው የበላይ አዛዥ ከኤፍሬም ወገን የሆነው ጲርዓቶናዊው በናያስ ሲሆን፣ በሥሩም ሃያ አራት ሺሕ ሰው ነበረ።

15በዐሥራ ሁለተኛው ወር፣ ዐሥራ ሁለተኛው የበላይ አዛዥ ከጎቶንያል ቤተ ሰብ የሆነው ነጦፋዊው ሔልዳይ ነበረ።

የየነገዱ የጦር ሹማምት

16የየነገዱ የእስራኤል የጦር ሹማምት፤

በሮቤል ነገድ ላይ የተሾመው፣ የዝክሪ ልጅ አልዓዛር፤

በስምዖን ነገድ ላይ የተሾመው፣ የመዓካ ልጅ ሰፋጥያስ።

17በሌዊ ነገድ ላይ የተሾመው፣ የቀሙኤል ልጅ ሐሸብያ፤

በአሮን ነገድ ላይ የተሾመው፣ ሳዶቅ።

18በይሁዳ ነገድ ላይ የተሾመው፣ የዳዊት ወንድም ኤሊሁ፤

በይሳኮር ነገድ ላይ የተሾመው፣ የሚካኤል ልጅ ዖምሪ።

19በዛብሎን ነገድ ላይ የተሾመው፣ የአብድዩ ልጅ ይሽማያ፤

በንፍታሌም ነገድ ላይ የተሾመው፣ የዓዝሪኤል ልጅ ለኢያሪሙት።

20በኤፍሬም ነገድ ላይ የተሾመው፣ የዓዛዝያ ልጅ ሆሴዕ፤

በምናሴ ነገድ እኩሌታ ላይ የተሾመው፣ የፈዳያ ልጅ ኢዩኤል።

21በገለዓድ ባለው የምናሴ ነገድ እኩሌታ ላይ የተሾመው፣ የዘካርያስ ልጅ አዶ፤ በብንያም ነገድ ላይ የተሾመው፣ የአበኔር ልጅ የዕሢኤል።

22በዳን ነገድ ላይ የተሾመው፣ የይሮሐም ልጅ ዓዛርኤል፤ እንግዲህ የእስራኤል ነገድ አለቆች እነዚህ ነበሩ።

23እግዚአብሔር እስራኤልን እንደ ሰማይ ከዋክብት እንደሚያበዛቸው ተስፋ ሰጥቶ ስለ ነበር፣ ዳዊት ዕድሜያቸው ሃያና ከዚያ በታች የሆነውን አልቈጠረም ነበር። 24የጽሩያ ልጅ ኢዮአብ መቍጠር ጀመረ፤ ሆኖም አልፈጸመውም፤ መቈጠራቸው በእስራኤል ላይ ቍጣ ስላመጣ፣ የተቈጠረውም በንጉሡ ዳዊት መዝገብ አልገባም።

ንጉሡ የሾማቸው የበላይ ተቈጣጣሪዎች

25የዓዲኤል ልጅ ዓዝሞት የቤተ መንግሥቱ ዕቃ ቤት ኀላፊ ነበረ፤

የዖዚያ ልጅ ዮናታን በየአውራጃው በየከተማው፣ በየመንደሩና በየቃፊር መጠበቂያው ላሉት ዕቃ ቤቶች ኀላፊ ነበረ።

26የክሉብ ልጅ ዔዝሪ ምድሪቱን ለሚያርሱት ገበሬዎች ኀላፊ ነበረ።

27ራማታዊው ሰሜኢ የወይን ተክል ቦታዎች ኀላፊ ነበረ፤ ሸፋማዊው ዘብዲ የወይን ጠጅ ዕቃ ቤት ኀላፊ ነበረ።

28ጌድራዊው በአልሐናን በምዕራባዊው ኰረብታዎች ግርጌ ለሚገኙት የወይንና የወርካ ዛፎች ጥበቃ ኀላፊ ነበረ።

29ሳሮናዊው ሰጥራይ በሳሮን ለሚሰማሩት የከብት መንጋዎች ኀላፊ ነበረ፤

የዓድላይ ልጅ ሻፋጥ በሸለቆው ውስጥ ላሉት የከብት መንጋዎች ኀላፊ ነበረ።

30እስማኤላዊው ኡቢያስ የግመሎች ኀላፊ ነበረ።

ሜሮኖታዊው ዬሕድያ የአህዮች ኀላፊ ነበረ።

31አጋራዊው ያዚዝ የበግና የፍየል መንጋዎች ኀላፊ ነበረ።

እነዚህ ሁሉ የንጉሥ ዳዊት ንብረት ኀላፊዎች ነበሩ።

32አስተዋይ የሆነው የዳዊት አጎት ዮናታን አማካሪና ጸሓፊ ነበረ፤ የሐክሞኒም ልጅ ይሒኤል ደግሞ የንጉሡ ልጆች ሞግዚት ነበረ።

33አኪጦፌል የንጉሡ አማካሪ ሲሆን፣ አርካዊው ኩሲ ደግሞ የንጉሡ ወዳጅ ነበረ።

34የበናያስ ልጅ ዮዳሄና አብያታር በአኪጦፌል እግር ተተኩ።

ኢዮአብም የንጉሡ የክብር ዘብ አዛዥ ሆነ።

Persian Contemporary Bible

اول تواريخ 27:1-34

تقسيمات سپاه اسرائيل

1سپاه اسرائيل از افراد و رؤسای خاندانها و طايفه‌ها و بزرگان تشكيل يافته بود و شامل دوازده سپاه می‌شد. هر سپاه كه متشكل از ۲۴,۰۰۰ نفر بود، به نوبت، سالی يک ماه به خدمت فرا خوانده می‌شد. فرماندهان اين سپاهيان، به ترتيب ماه خدمت، عبارت بودند از:

2‏-3ماه اول: يشبعام، پسر زبدی‌ئيل، از طايفهٔ فارص؛

4ماه دوم: دودای اخوخی (معاون او مقلوت نام داشت)؛

5‏-6ماه سوم: بنايا، پسر يهوياداع كاهن اعظم (بنايا همان كسی است كه فرماندهٔ سی سردار داوود بود؛ پسرش عميزاباد از فرماندهان سپاه او بود)؛

7ماه چهارم: عسائيل، برادر يوآب (بعد از او پسرش زبديا جای او را گرفت)؛

8ماه پنجم: شمهوت يزراحی؛

9ماه ششم: عيرا، پسر عقيش تقوعی؛

10ماه هفتم: حالص فلونی از قبيلهٔ افرايم؛

11ماه هشتم: سبكای حوشاتی از طايفه زارح؛

12ماه نهم: ابيعزر عناتوتی از قبيلهٔ بنيامين؛

13ماه دهم: مهرای نطوفاتی از طايفه زارح؛

14ماه يازدهم: بنايا فرعاتونی از قبيلهٔ افرايم؛

15ماه دوازدهم: خلدای نطوفاتی از نسل عتنی‌ئيل.

رؤسای قبيله‌ها

16‏-22رؤسای قبيله‌های اسرائيل به شرح زير بودند:

العازار پسر زكری، رئيس قبيلهٔ رئوبين؛

شفطيا پسر معكه، رئيس قبيلهٔ شمعون؛

حشبيا پسر قموئيل، رئيس قبيلهٔ لاوی؛

صادوق، رئيس خاندان هارون؛

اليهو برادر داوود پادشاه، رئيس قبيلهٔ يهودا؛

عمری پسر ميكائيل، رئيس قبيلهٔ يساكار؛

يشمعيا پسر عوبديا، رئيس قبيلهٔ زبولون؛

يريموت پسر عزری‌ئيل، رئيس قبيلهٔ نفتالی؛

هوشع پسر عزريا، رئيس قبيلهٔ افرايم؛

يوئيل پسر فدايا، رئيس نصف قبيلهٔ منسی؛

يدو پسر زكريا، رئيس نصف ديگر قبيلهٔ منسی در جلعاد؛

يعسی‌ئيل پسر ابنير، رئيس قبيله بنيامين؛

عزرئيل پسر يروحام، رئيس قبيلهٔ دان.

23داوود هنگام سرشماری، جوانان بيست سال يا كمتر را به حساب نياورد، زيرا خداوند وعده داده بود كه جمعيت اسرائيل را مثل ستارگان آسمان بی‌شمار گرداند. 24يوآب سرشماری را شروع كرد ولی آن را تمام نكرد، چون خشم خداوند بر اسرائيل افروخته شد. لذا آمار نهايی در سالنامهٔ داوود پادشاه ثبت نشد.

ناظران دارايی پادشاه

25عزموت پسر عدی‌ئيل سرپرست انبارهای سلطنتی و يوناتان پسر عزيا سرپرست انبارهای شهرها و روستاها و قلعه‌ها بود.

26عزری پسر كلوب، سرپرست كارگرانی بود كه در املاک پادشاه كار می‌كردند. 27شمعی راماتی بر باغهای انگور پادشاه نظارت می‌كرد. زبدی شفماتی مسئول تهيهٔ شراب و انبار كردن آن بود. 28بعل حانان جديری مسئول باغهای زيتون و درختان افراغ در دشتهای هم مرز كشور فلسطين بود. يوآش متصدی ذخيرهٔ روغن زيتون بود.

29شطرای شارونی در دشت شارون از رمه‌ها نگهداری می‌كرد، و شافاط پسر عدلائی مسئول نگهداری رمه‌هايی بود كه در دره‌ها می‌چريدند. 30عوبيل اسماعيلی بر كار نگهداری شترها و يحديای ميرونوتی بر كار نگهداری الاغها نظارت می‌كردند. 31يازيز مسئول نگهداری گله‌ها بود. تمام اين مردان ناظران دارايی داوود پادشاه بودند.

32يوناتان عموی داوود مشاوری دانا و عالم بود و يحی‌ئيل، پسر حكمونی از پسران پادشاه مواظبت می‌كرد.

33اخيتوفل مشاور پادشاه و حوشای اركی دوست پادشاه بود. 34پس از اخيتوفل، يهوياداع (پسر بنايا) و ابياتار به جای او مشاور شدند. فرماندهٔ سپاه اسرائيل يوآب بود.