1 ዜና መዋዕል 24 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

1 ዜና መዋዕል 24:1-31

የካህናት አመዳደብ

1የአሮን ልጆች አመዳደብ እንደሚከተለው ነበረ፤

የአሮን ልጆች ናዳብ፣ አብዩድ፣ አልዓዛር፣ ኢታምር ነበሩ። 2ናዳብና አብዩድ ግን ዘር ሳይተኩ ከአባታቸው በፊት ሞቱ፤ ስለዚህ አልዓዛርና ኢታምር ካህናት ሆነው ያገለግሉ ነበር። 3ዳዊትም የአልዓዛር ዘር የሆነው ሳዶቅና የኢታምር ዘር የሆነው አቢሜሌክ እየረዱት እንደየአገልግሎታቸው ሥርዐት እየለየ መደባቸው። 4ከኢታምር ይልቅ በአልዓዛር ዘሮች መካከል ብዙ መሪዎች ተገኙ፤ አከፋፈላቸውም እንደሚከተለው ነበር፤ ከአልዓዛር ዘሮች ዐሥራ ስድስት የቤተ ሰብ አለቆች፤ ከኢታምርም ዘሮች ስምንት የቤተ ሰብ አለቆች። 5ከአልዓዛርና ከኢታምር ዘሮች መካከል የመቅደሱ ሹማምትና የእግዚአብሔር ሹማምት ስለ ነበሩ፣ ያለ አድልዎ በዕጣ ለዩአቸው።

6የሌዋዊው የናትናኤል ልጅ ጸሓፊው ሸማያ በንጉሡና በሹማምቱ፣ በካህኑ በሳዶቅ፣ በአብያታር ልጅ በአቤሜሌክ እንዲሁም በካህናቱና በሌዋውያኑ ቤተ ሰብ አለቆች ፊት ስማቸውን ጻፈ፤ የጻፈውም አንዱን ቤተ ሰብ ከአልዓዛር ሌላውን ደግሞ ከኢታምር በመውሰድ ነው፤

7የመጀመሪያው ዕጣ ለዮአሪብ፣

ሁለተኛውም ዕጣ ለዮዳሄ ወጣ፤

8ሦስተኛው ለካሪም፣

አራተኛው ለሥዖሪም፣

9አምስተኛው ለመልክያ፣

ስድስተኛው ለሚያሚን፣

10ሰባተኛው ለአቆስ፣

ስምንተኛው ለአብያ፣

11ዘጠነኛው ለኢያሱ፣

ዐሥረኛው ለሴኬንያ፣

12ዐሥራ አንደኛው ለኤሊያሴብ፣

ዐሥራ ሁለተኛው ለያቂም፣

13ዐሥራ ሦስተኛው ለኦፖ፣

ዐሥራ አራተኛው ለየሼብአብ፣

14ዐሥራ አምስተኛው ለቢልጋ፣

ዐሥራ ስድስተኛው ለኢሜር፣

15ዐሥራ ሰባተኛው ለኤዚር፣

ዐሥራ ስምንተኛው ለሃፊጼጽ፣

16ዐሥራ ዘጠነኛው ለፈታያ፣

ሃያኛው ለኤዜቄል፣

17ሃያ አንደኛው ለያኪን፣

ሃያ ሁለተኛው ለጋሙል፣

18ሃያ ሦስተኛው ለድላያ፣

ሃያ አራተኛ ለመዓዝያ ወጣ።

19የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር ባዘዘውና ከቀድሞ አባታቸው ከአሮን በተሰጣቸው መመሪያ መሠረት ወደ እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ በሚገቡበት ጊዜ፣ የተወሰነላቸው ሥርዐት ይህ ነበር።

የተቀሩት ሌዋውያን

20ከቀሩት የሌዊ ዘሮች ደግሞ፦

ከእንበረም ወንዶች ልጆች፣ ሱባኤል፤

ከሱባኤል ወንዶች ልጆች፣ ዬሕድያ።

21ከረዓብያ ወንዶች ልጆች፤

አለቃው ይሺያ።

22ከይስዓራውያን ወገን፣ ሰሎሚት፤

ከሰሎሚት ወንዶች ልጆች፣ ያሐት።

23የኬብሮን ወንዶች ልጆች፣ የመጀመሪያው ይሪያ24፥23 ሁለት የዕብራይስጥ ቅጆችና ጥቂት የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞች (እንዲሁም 1ዜና 23፥19 ይመ) ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ አብዛኞቹ የዕብራይስጥ ቅጆች ግን፣ የይሪያ ወንዶች ልጆች ይላሉ፣ ሁለተኛው አማርያ፣ ሦስተኛው የሕዚኤል፣ አራተኛው ይቀምዓም።

24የዑዝኤል ልጅ፣

ሚካ ከሚካ ወንዶች ልጆች ሻሚር።

25የሚካ ወንድም ይሺያ፤

ከይሺያ ወንዶች ልጆች ዘካርያስ።

26የሜራሪ ወንዶች ልጆች፤ ሞሖሊ፣ ሙሲ።

የያዝያ ወንድ ልጅ በኖ።

27የሜራሪ ወንዶች ልጆች፤

ከያዝያ በኖ፣ ሾሃም፣ ዘኩር፣ ዔብሪ።

28ከሞሖሊ፤ አልዓዛር፤ ይህ ሰው ወንዶች ልጆች አልነበሩትም።

29ከቂስ፤ የቂስ ወንድ ልጅ፤

ይረሕምኤል።

30የሙሲ ወንዶች ልጆች፤ ሞሖሊ፣ ዔዳር፣ ለኢያሪሙት።

እነዚህ እንግዲህ እንደየቤተ ሰባቸው የተቈጠሩ ሌዋውያን ነበሩ።

31ወንድሞቻቸው የአሮን ዘሮች እንዳደረጉት ሁሉ፣ እነዚህም በንጉሥ ዳዊት፣ በሳዶቅ፣ በአቢሜሌክ እንዲሁም የካህናቱና የሌዋውያኑ ቤተ ሰብ አለቆች ባሉበት ዕጣ ተጣጣሉ፤ የበኵሩም ቤተ ሰቦች እንደ ትንሹ ወንድም ቤተ ሰብ እኩል ዕጣ ተጣለላቸው።

Japanese Contemporary Bible

歴代誌Ⅰ 24:1-31

24

祭司の組み分け

1-2アロンの子孫の祭司は、アロンの二人の息子エルアザルとイタマルの名にちなんで、二つの組に分けられました。ナダブとアビフもアロンの息子でしたが、二人とも父に先立って死に、しかも、子どもがいませんでした。それで、エルアザルとイタマルだけが祭司の務めを果たしたのです。 3ダビデは、エルアザルの氏族を代表するツァドクと、イタマルの氏族を代表するアヒメレクとに相談して、交替で奉仕できるよう、祭司を多くのグループに分けました。 4エルアザルの子孫は、指導者となる人材に恵まれていたので、十六組に分けられ、イタマルの子孫は八組に分けられました。

5あらゆる務めは特定の組に片寄らないよう、くじで各組に割り当てられました。どの組にも多くのすぐれた人材がいて、神殿の重要な務めにつけたからです。 6レビ人でネタヌエルの子シェマヤが書記となり、王をはじめ祭司ツァドク、エブヤタルの子アヒメレク、ならびに祭司とレビ人の長たちの前で、それぞれの名と役割を書き留めました。エルアザルの組からの二つのグループと、イタマルの組からの一つのグループが、交互に務めにつくようになっていました。

7-18くじで、次の各グループの順序に従って、仕事が割り当てられました。

第一はエホヤリブのグループ。第二はエダヤのグループ。第三はハリムのグループ。第四はセオリムのグループ。第五はマルキヤのグループ。第六はミヤミンのグループ。第七はコツのグループ。第八はアビヤのグループ。第九はヨシュアのグループ。第十はシェカヌヤのグループ。第十一はエルヤシブのグループ。第十二はヤキムのグループ。第十三はフパのグループ。第十四はエシェブアブのグループ。第十五はビルガのグループ。第十六はイメルのグループ。第十七はヘジルのグループ。第十八はピツェツのグループ。第十九はペタフヤのグループ。第二十はエヘズケルのグループ。第二十一はヤキンのグループ。第二十二はガムルのグループ。第二十三はデラヤのグループ。第二十四はマアズヤのグループ。

19各グループは、先祖アロンによって主から最初に指示されたとおり、神殿での務めにつきました。

その他のレビ人

20そのほかのレビの子孫は次のとおり。アムラムおよび彼の子孫シュバエル、シュバエルの子孫エフデヤ、 21長子イシヤを長とするレハブヤのグループ、 22シェロミテと彼の子孫ヤハテからなるイツハルのグループ。

23ヘブロンのグループは次のとおり。ヘブロンの長男エリヤ。次男アマルヤ。三男ヤハジエル。四男エカムアム。

24-25ウジエルのグループの長は、その子ミカ、孫シャミル、ミカの兄弟イシヤ、イシヤの子ゼカリヤ。

26-27メラリのグループの長は、その子マフリとムシ。その子孫ヤアジヤのグループは彼の子ベノを長とし、その兄弟ショハム、ザクル、イブリ。 28-29マフリの子孫はエルアザルとキシュで、エルアザルには息子がなく、キシュには息子があり、その子孫、エラフメエル。 30ムシの子孫はマフリ、エデル、エリモテ。以上が、それぞれの氏族に属するレビの子孫です。 31アロンの子孫と同じように、彼らは年齢や身分に関係なく、くじで決まった順番で奉仕が割り当てられました。その順番は、ダビデ、ツァドク、アヒメレク、そのほかの祭司やレビ人の長たちの前で決められました。