1 ዜና መዋዕል 24 – NASV & HTB

New Amharic Standard Version

1 ዜና መዋዕል 24:1-31

የካህናት አመዳደብ

1የአሮን ልጆች አመዳደብ እንደሚከተለው ነበረ፤

የአሮን ልጆች ናዳብ፣ አብዩድ፣ አልዓዛር፣ ኢታምር ነበሩ። 2ናዳብና አብዩድ ግን ዘር ሳይተኩ ከአባታቸው በፊት ሞቱ፤ ስለዚህ አልዓዛርና ኢታምር ካህናት ሆነው ያገለግሉ ነበር። 3ዳዊትም የአልዓዛር ዘር የሆነው ሳዶቅና የኢታምር ዘር የሆነው አቢሜሌክ እየረዱት እንደየአገልግሎታቸው ሥርዐት እየለየ መደባቸው። 4ከኢታምር ይልቅ በአልዓዛር ዘሮች መካከል ብዙ መሪዎች ተገኙ፤ አከፋፈላቸውም እንደሚከተለው ነበር፤ ከአልዓዛር ዘሮች ዐሥራ ስድስት የቤተ ሰብ አለቆች፤ ከኢታምርም ዘሮች ስምንት የቤተ ሰብ አለቆች። 5ከአልዓዛርና ከኢታምር ዘሮች መካከል የመቅደሱ ሹማምትና የእግዚአብሔር ሹማምት ስለ ነበሩ፣ ያለ አድልዎ በዕጣ ለዩአቸው።

6የሌዋዊው የናትናኤል ልጅ ጸሓፊው ሸማያ በንጉሡና በሹማምቱ፣ በካህኑ በሳዶቅ፣ በአብያታር ልጅ በአቤሜሌክ እንዲሁም በካህናቱና በሌዋውያኑ ቤተ ሰብ አለቆች ፊት ስማቸውን ጻፈ፤ የጻፈውም አንዱን ቤተ ሰብ ከአልዓዛር ሌላውን ደግሞ ከኢታምር በመውሰድ ነው፤

7የመጀመሪያው ዕጣ ለዮአሪብ፣

ሁለተኛውም ዕጣ ለዮዳሄ ወጣ፤

8ሦስተኛው ለካሪም፣

አራተኛው ለሥዖሪም፣

9አምስተኛው ለመልክያ፣

ስድስተኛው ለሚያሚን፣

10ሰባተኛው ለአቆስ፣

ስምንተኛው ለአብያ፣

11ዘጠነኛው ለኢያሱ፣

ዐሥረኛው ለሴኬንያ፣

12ዐሥራ አንደኛው ለኤሊያሴብ፣

ዐሥራ ሁለተኛው ለያቂም፣

13ዐሥራ ሦስተኛው ለኦፖ፣

ዐሥራ አራተኛው ለየሼብአብ፣

14ዐሥራ አምስተኛው ለቢልጋ፣

ዐሥራ ስድስተኛው ለኢሜር፣

15ዐሥራ ሰባተኛው ለኤዚር፣

ዐሥራ ስምንተኛው ለሃፊጼጽ፣

16ዐሥራ ዘጠነኛው ለፈታያ፣

ሃያኛው ለኤዜቄል፣

17ሃያ አንደኛው ለያኪን፣

ሃያ ሁለተኛው ለጋሙል፣

18ሃያ ሦስተኛው ለድላያ፣

ሃያ አራተኛ ለመዓዝያ ወጣ።

19የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር ባዘዘውና ከቀድሞ አባታቸው ከአሮን በተሰጣቸው መመሪያ መሠረት ወደ እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ በሚገቡበት ጊዜ፣ የተወሰነላቸው ሥርዐት ይህ ነበር።

የተቀሩት ሌዋውያን

20ከቀሩት የሌዊ ዘሮች ደግሞ፦

ከእንበረም ወንዶች ልጆች፣ ሱባኤል፤

ከሱባኤል ወንዶች ልጆች፣ ዬሕድያ።

21ከረዓብያ ወንዶች ልጆች፤

አለቃው ይሺያ።

22ከይስዓራውያን ወገን፣ ሰሎሚት፤

ከሰሎሚት ወንዶች ልጆች፣ ያሐት።

23የኬብሮን ወንዶች ልጆች፣ የመጀመሪያው ይሪያ24፥23 ሁለት የዕብራይስጥ ቅጆችና ጥቂት የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞች (እንዲሁም 1ዜና 23፥19 ይመ) ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ አብዛኞቹ የዕብራይስጥ ቅጆች ግን፣ የይሪያ ወንዶች ልጆች ይላሉ፣ ሁለተኛው አማርያ፣ ሦስተኛው የሕዚኤል፣ አራተኛው ይቀምዓም።

24የዑዝኤል ልጅ፣

ሚካ ከሚካ ወንዶች ልጆች ሻሚር።

25የሚካ ወንድም ይሺያ፤

ከይሺያ ወንዶች ልጆች ዘካርያስ።

26የሜራሪ ወንዶች ልጆች፤ ሞሖሊ፣ ሙሲ።

የያዝያ ወንድ ልጅ በኖ።

27የሜራሪ ወንዶች ልጆች፤

ከያዝያ በኖ፣ ሾሃም፣ ዘኩር፣ ዔብሪ።

28ከሞሖሊ፤ አልዓዛር፤ ይህ ሰው ወንዶች ልጆች አልነበሩትም።

29ከቂስ፤ የቂስ ወንድ ልጅ፤

ይረሕምኤል።

30የሙሲ ወንዶች ልጆች፤ ሞሖሊ፣ ዔዳር፣ ለኢያሪሙት።

እነዚህ እንግዲህ እንደየቤተ ሰባቸው የተቈጠሩ ሌዋውያን ነበሩ።

31ወንድሞቻቸው የአሮን ዘሮች እንዳደረጉት ሁሉ፣ እነዚህም በንጉሥ ዳዊት፣ በሳዶቅ፣ በአቢሜሌክ እንዲሁም የካህናቱና የሌዋውያኑ ቤተ ሰብ አለቆች ባሉበት ዕጣ ተጣጣሉ፤ የበኵሩም ቤተ ሰቦች እንደ ትንሹ ወንድም ቤተ ሰብ እኩል ዕጣ ተጣለላቸው።

Het Boek

1 Kronieken 24:1-31

De taak van de priesters

1-2 Ook de priesters, de nakomelingen van Aäron, waren onderverdeeld in twee groepen, die de namen droegen van de zonen van Aäron: Eleazar en Itamar. Nadab en Abihu waren ook zonen van Aäron, maar zij stierven eerder dan hun vader en hadden geen kinderen, zo bleven alleen Eleazar en Itamar over voor de bediening van het priesterambt. 3Na overleg met Zadok en Ahimelech, de leiders van respectievelijk de Eleazar-groep en de Itamar-groep, verdeelde David Aärons nakomelingen over talloze kleine groepen, al naar gelang het soort werk dat zij verrichtten. 4Eleazars nakomelingen werden onderverdeeld in zestien en Itamars nakomelingen in acht groepen. Het bleek namelijk dat onder de nakomelingen van Eleazar meer groepshoofden waren dan onder de nakomelingen van Itamar. 5Door middel van het lot werden de priesters bij de groepen ingedeeld, zodat niemand werd bevoordeeld, want er bevonden zich heel wat beroemde mannen en hoogwaardigheidsbekleders van de tempel in elke groep. 6Semaja, een Leviet en de zoon van Netanel, fungeerde als secretaris en noteerde de namen in het bijzijn van de koning, de leiders van Israël, de priester Zadok, Abjathars zoon Ahimelech en de hoofden van de priesters en de Levieten. Beurtelings werd één familie getrokken voor de Eleazar-groep en één voor de Itamar-groep.

7-18De families werden door middel van het lot op de volgende manier verdeeld: als eerste viel het lot op Jojarib; als tweede op Jedaja; de derde was Harim; de vierde was Seorim; vijfde was Malkia; zesde Mijamin; zevende Hakkoz; achtste Abia; negende Jesua; tiende Sechanja; elfde Eljasib; twaalfde Jakim; dertiende Huppa; veertiende Jesebeab; vijftiende Bilga; zestiende Immer; zeventiende Hezir; achttiende Happizzes; negentiende Petahja; twintigste Jehezkel; eenentwintigste Jachin; tweeëntwintigste Gamul; drieëntwintigste Delaja; vierentwintigste Maäzja. 19Elke groep voerde zijn eigen taken in de tempel uit, zoals God die aan hun voorvader Aäron had opgedragen.

20Dit waren de andere nakomelingen van Levi: Amram, zijn nakomeling Subaël en diens telg Jehdeja, 21de groep van Rehabja, onder leiding van zijn oudste zoon Jissia, 22de groep van Jizha, bestaande uit Selomoth en zijn nakomeling Jahath. 23De groep van Hebron, bestaande uit Jeria, Hebrons oudste zoon, Amarja, zijn tweede zoon, Jahaziël, zijn derde zoon, en Jekameam, de vierde zoon. 24-25 De groep van Uzziël stond onder leiding van zijn zoon Micha. Van de groep van Micha had zijn zoon Samir de leiding. De leiding van de groep van Michaʼs broer Jissia was in handen van diens zoon Zecharja. 26-27 De groep van Merari stond onder leiding van zijn zonen Machli en Musi. De groep van Jaäzia, ook een zoon van Merari, bestond uit Beno, Soham, Zakkur en Hibri. 28Machliʼs nakomelingen waren Eleazar, die geen zonen had, 29en Kis, die onder meer Jerachmeël als zoon had. 30De zonen van Musi waren Machli, Eder en Jerimoth. Dit waren de nakomelingen van Levi, verdeeld over hun families. 31Evenals de nakomelingen van Aäron werden ook zij door middel van het lot ingedeeld, zonder dat daarbij werd gelet op leeftijd of rang. Dat gebeurde in het bijzijn van koning David, Zadok, Ahimelech en de leiders van de priesters en Levieten.