1 ዜና መዋዕል 22 – NASV & BPH

New Amharic Standard Version

1 ዜና መዋዕል 22:1-19

1ከዚያም ዳዊት፣ “ከእንግዲህ የእግዚአብሔር አምላክ ቤት በዚህ ይሆናል፤ እንዲሁም ስለ እስራኤል የሚቃጠል መሥዋዕት የሚቀርብበት መሠዊያ በዚሁ ይቆማል” አለ።

ቤተ መቅደሱን ለመሥራት የተደረገ ዝግጅት

2ስለዚህ ዳዊት በእስራኤል የሚኖሩ መጻተኞች እንዲሰበሰቡ አዘዘ፤ ከመካከላቸውም የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ የሚሠራበትን ጥርብ ድንጋይ እንዲያዘጋጁ ጠራቢዎችን መደበ። 3ለቅጥር በሮቹ ምስማርና ማጠፊያ የሚሆን ብዙ ብረትና ከብዛቱ የተነሣ ሊመዘን የማይቻል ናስ አዘጋጀ። 4እንዲሁም ሲዶናውያንና ጢሮሳውያን በብዛት አምጥተውለት ስለ ነበር፣ ስፍር ቍጥር የሌለው የዝግባ ዕንጨት አሰናዳ።

5ዳዊትም፣ “ልጄ ሰሎሞን ወጣት ነው፤ ልምዱም የለውም፤ ለእግዚአብሔር የሚሠራው ቤተ መቅደስ ደግሞ እጅግ የሚያምር፣ በአሕዛብም ሁሉ ዘንድ ዝናው የተሰማና እጅግ የተዋበ መሆን አለበት፤ ስለዚህ ሁሉንም እኔ አዘጋጃለሁ” አለ። እንዳለውም ዳዊት ከመሞቱ በፊት በብዛት አዘጋጀ።

6ከዚያም ልጁን ሰሎሞንን ጠርቶ ለእስራኤል አምላክ ለእግዚአብሔር ቤት እንዲሠራ አዘዘው።

7ዳዊትም ሰሎሞንን እንዲህ አለው፤ “ልጄ ሆይ፤ ለአምላኬ ለእግዚአብሔር ስም ቤት ለመሥራት በልቤ ዐስብ ነበር፤ 8ነገር ግን ከእግዚአብሔር እንዲህ የሚል ቃል መጣልኝ፤ ‘አንተ ብዙ ደም አፍስሰሃል፤ ብዙ ጦርነትም አድርገሃል፤ በፊቴ በምድር ላይ ብዙ ደም ያፈሰስህ ስለሆነ፣ አንተ ለስሜ ቤት አትሠራልኝም፤ 9ነገር ግን የሰላምና የዕረፍት ሰው የሆነ ልጅ ትወልዳለህ፤ በየአቅጣጫው ካሉ ጠላቶቹ አሳርፈዋለሁ፤ ስሙም ሰሎሞን ይባላል። በዘመኑም ለእስራኤል ሰላምንና ጸጥታን እሰጣለሁ። 10ለስሜ ቤት የሚሠራልኝ እርሱ ነው። እርሱ ልጅ ይሆነኛል፤ እኔም አባት እሆነዋለሁ። ዙፋኑንም በእስራኤል ላይ ለዘላለም አጸናለሁ።’

11“አሁንም ልጄ ሆይ፤ እግዚአብሔር ከአንተ ጋር ይሁን፤ እንድትፈጽመው በተናገረውም መሠረት፣ ተሳክቶልህ የአምላክህን የእግዚአብሔርን ቤት ለመሥራት ያብቃህ። 12በእስራኤል ላይ አለቃ ባደረገህ ጊዜ፣ የአምላክህን የእግዚአብሔርን ትእዛዝ ትፈጽም ዘንድ እግዚአብሔር ጥበብንና ማስተዋልን ይስጥህ። 13እግዚአብሔር በሙሴ አማካይነት ለእስራኤል የሰጠውን ሕጉንና ሥርዐቱን ተጠንቅቀህ ብትጠብቅ ይሳካልሃል፤ አይዞህ ጠንክር፤ በርታ፤ ተስፋም አትቍረጥ።

14ለእግዚአብሔር ቤት እንዲሆንም አንድ ሺሕ መክሊት22፥14 3,450 ሜትሪክ ቶን ያህል ነው ወርቅ፣ አንድ ሚሊዮን መክሊት22፥14 34,500 ሜትሪክ ቶን ያህል ነው ብር፣ ከብዛቱ የተነሣ ሊመዘን የማይቻል ናስና ብረት ለማዘጋጀት በተቻለኝ ሁሉ ጥሬአለሁ፤ በተረፈ አንተ ጨምርበት። 15ድንጋይ ጠራቢዎች፣ ግንበኞች፣ ዐናጢዎች የሆኑ ብዙ ሠራተኞች፣ እንዲሁም በልዩ ልዩ ሙያ የተጠበቡ ሰዎች አሉህ፤ 16እነዚህም ቍጥራቸው እጅግ የበዛ የወርቅ፣ የብር፣ የናስና የብረት ሠራተኞች ናቸው። በል ሥራህን ጀምር፤ እግዚአብሔርም ከአንተ ጋር ይሁን።”

17ከዚያም ዳዊት የእስራኤል መሪዎች ሁሉ ልጁን ሰሎሞንን እንዲረዱት አዘዘ፤ 18እንዲህም አለ፤ “እግዚአብሔር አምላካችሁ እስካሁን ከእናንተ ጋር አይደለምን? በየአቅጣጫውስ ዕረፍትን ሰጥቷችሁ የለምን? የምድሪቱን ነዋሪዎች በእጄ አሳልፎ ሰጥቶኛል፤ ምድሪቱም ለእግዚአብሔርና ለሕዝቡ ተገዝታለች። 19አሁንም እግዚአብሔር አምላካችሁን ለመፈለግ ልባችሁንና ነፍሳችሁን ሰብስቡ። የእግዚአብሔርን የኪዳኑን ታቦትና ንዋያተ ቅድሳቱን ለእግዚአብሔር ስም ወደሚሠራው ቤተ መቅደስ አምጥታችሁ የአምላክን የእግዚአብሔርን መቅደስ ሥሩ።”

Bibelen på hverdagsdansk

1. Krønikebog 22:1-19

David gør klar til, at et tempel kan bygges

1Derefter bekendtgjorde David: „Her er stedet, hvor Herrens Hus skal bygges. Her skal Israels folk bringe brændofre.” 2Så befalede han, at alle udlændinge, der boede i landet, skulle samles og sættes i arbejde med at tilhugge stenblokke til templet. 3Han skaffede også en masse jern til at smede søm og hængsler til portene foruden en umådelig mængde bronze. 4Fra Tyrus og Sidon skaffede han enorme mængder af cedertræ til byggeriet.

5David tænkte nemlig: „Det tempel, som skal bygges for Herren, skal være så storslået, at det bliver berømt ud over hele verden. Men min søn Salomon, som skal bygge det, er stadig ung og uerfaren, så jeg vil hjælpe ham ved at gøre det hele klar.” Det var grunden til, at David inden sin død gjorde alle disse forberedelser.

6David gav derpå Salomon ansvaret for at bygge et tempel for Herren, Israels Gud. 7„Det var min plan at bygge et hus til Herren, min Gud,” forklarede David ham, 8„men han sagde til mig: ‚Du har dræbt mange mennesker i de hårde krige, du har udkæmpet. Fordi du har udgydt så meget blod, bliver det ikke dig, der kommer til at bygge mit tempel. 9Men du skal få en søn, som vil blive en fredens mand. Jeg vil sørge for, at han kan leve i fred med alle nabofolkene rundt omkring jer. Han skal hedde Salomon,22,9 Navnet „Salomon” (hebraisk Shlomoh) minder om ordet for „fred” (shalom). for i hans regeringstid vil Israel have fred. 10Han skal bygge mig et hus og være min søn. Jeg vil være hans far, og jeg vil gøre hans herredømme over Israel urokkeligt for evigt.’

11Og nu, min søn, må Herren hjælpe dig, så du kan få bygget det hus for Herren, din Gud, som han har talt om. 12Og må han give dig visdom og dømmekraft, så han kan gøre dig til konge over Israel, og så du følger Herren, din Guds, bud. 13Hvis du nøje følger de love og forskrifter, han gav Israel gennem Moses, vil det gå dig godt. Vær frimodig og stærk. Vær ikke bange og lad dig ikke skræmme. 14Med hensyn til templet har jeg gjort et stort forarbejde. Jeg har samlet næsten 4000 tons guld og 40.000 tons sølv samt umådelige mængder af jern og bronze. Jeg har også skaffet bjælker og stenblokke, og du kan selv sørge for mere. 15-16Mange erfarne arbejdere står til din rådighed, både stenhuggere, murere og tømrere, samt kunsthåndværkere, der kan udføre al slags arbejde i guld, sølv, bronze og jern. Gå blot i gang! Og må Herren være med dig!”

17David befalede alle Israels ledere at hjælpe Salomon med projektet. 18„Herren vil være med jer!” sagde han. „Han har givet os fred med nabofolkene. Han har hjulpet mig med at besejre dem, og de er nu underlagt Herren og hans folk. 19Sæt derfor alt ind på at adlyde Herren, jeres Gud, og tag fat på at bygge hans helligdom, så Herrens Pagts Ark og alle de andre hellige ting kan blive anbragt deri.”