1 ዜና መዋዕል 2 – NASV & NIVUK

New Amharic Standard Version

1 ዜና መዋዕል 2:1-55

የእስራኤል ወንዶች ልጆች

2፥1-2 ተጓ ምብ – ዘፍ 35፥23-26

1የእስራኤል ወንዶች ልጆች እነዚህ ነበሩ፤ ሮቤል፣ ስምዖን፣ ሌዊ፣ ይሁዳ፣ ይሳኮር፣ ዛብሎን፣ 2ዳን፣ ዮሴፍ፣ ብንያም፣ ንፍታሌም፣ ጋድ፣ አሴር።

ይሁዳ

2፥5-15 ተጓ ምብ – ሩት 4፥18-22ማቴ 1፥3-6

እስከ ኤስሮን ወንዶች ልጆች

3የይሁዳ ወንዶች ልጆች፤

ዔር፣ አውናን፣ ሴሎም፤ እነዚህን ሦስቱን ከከነዓናዊት ሚስቱ ከሴዋ ወለደ። የበኵር ልጁ ዔር በእግዚአብሔር ፊት ክፉ ሰው ሆነ፤ እግዚአብሔርም ቀሠፈው። 4የልጁም ሚስት የነበረችው ትዕማር ፋሬስንና ዛራን ወለደችለት፤

ይሁዳም በአጠቃላይ አምስት ወንዶች ልጆች ነበሩት።

5የፋሬስ ወንዶች ልጆች፤

ኤስሮም፣ ሐሙል።

6የዛራ ወንዶች ልጆች፤

ዘምሪ፣ ኤታን፣ ሄማን፣ ከልኮል፣ ዳራ2፥6 አያሌ የዕብራይስጥ ቅጆች ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ አንዳንድ የዕብራይስጥ፣ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞችና የሱርስቱ ቅጆች (እንዲሁም 1ነገ 4፥31 ይመ) ግን፣ ዳርዳ ይላሉ።፤ በአጠቃላይ አምስት ናቸው።

7የከርሚ ወንድ ልጅ አካን2፥7 አካን ማለት፣ ችግር ወይም፣ መከራ ማለት ነው።

እርሱም ፈጽሞ መደምሰስ የነበረበትን ነገር ሰርቆ በእስራኤል ላይ ጥፋት2፥7 የዕብራይስጡ ቃል አንድን ሰው ወይም ነገር ሙሉ በሙሉ በማጥፋት ለእግዚአብሔር መስጠትን ያመለክታል። እንዲመጣ ያደረገ ነው።

8የኤታን ወንድ ልጅ፤

አዛርያ።

9የኤስሮም ወንዶች ልጆች፤

ይረሕምኤል፣ አራም፣ ካሌብ።2፥9 ዕብራይስጡ፣ ከሉባይ ይላል፤ ይኸውም፣ ካሌብ ማለት ነው።

ከኤስሮም ልጅ ከአራም ጀምሮ ያለው የትውልድ ሐረግ

10አራም አሚናዳብን ወለደ፤

አሚናዳብም የይሁዳ ሕዝብ መሪ የሆነውን ነአሶንን ወለደ፤

11ነአሶን ሰልሞንን2፥11 የሰብዓ ሊቃናት ትርጕም (እንዲሁም ሩት 4፥21) ከዚህ ጋር ይስማማል፤ ዕብራይስጡ ግን፣ ሳልማ ወለደ፤

ሰልሞን ቦዔዝን ወለደ።

12ቦዔዝ ኢዮቤድን ወለደ፤

ኢዮቤድ እሴይን ወለደ።

13የእሴይ ወንዶች ልጆች፤

የበኵር ልጁ ኤልያብ፣ ሁለተኛ ልጁ አሚናዳብ፣

ሦስተኛ ልጁ ሣማ፣ 14አራተኛ ልጁ ናትናኤል፣

አምስተኛ ልጁ ራዳይ፣ 15ስድስተኛ ልጁ አሳም፣

ሰባተኛ ልጁ ዳዊት።

16እኅቶቻቸውም ጽሩያና አቢግያ ነበሩ።

የጽሩያ ሦስት ወንዶች ልጆች አቢሳ፣ ኢዮአብና አሣኤል ነበሩ።

17አቢግያ አሜሳይን ወለደች፤ አባቱም ዬቴር የተባለ እስማኤላዊ ነበረ።

የኤስሮም ልጅ ካሌብ

18የኤስሮም ልጅ ካሌብ ከሚስቱ ከዓዙባና እንዲሁም ከይሪዖት ወንዶች ልጆች ወለደ፤ ከዓዙባ የተወለዱት ወንዶች ልጆች እነዚህ ናቸው፤ ያሳር፣ ሶባብ፣ አርዶን።

19ዓዙባ ስትሞት፣ ካሌብ ኤፍራታን አገባ፤ እርሷም ሆርን ወለደችለት።

20ሆር ኡሪን ወለደ፤ ኡሪም ባስልኤልን ወለደ።

21ከዚያም በኋላ ኤስሮም ስድሳ ዓመት ሲሆነው የገለዓድን አባት የማኪርን ልጅ አገባ፤ እርሷም ሠጉብን ወለደችለት።

22ሠጉብም ኢያዕርን ወለደ፤ እርሱም በገለዓድ ምድር ሃያ ሦስት ከተሞች ያስተዳድር ነበር።

23ይሁን እንጂ ጌሹርና አራም፣ ቄናትንና በዙሪያዋ የሚገኙትን ስድሳ መንደሮች ጨምሮ የኢያዕርን ከተሞች ነጠቁት2፥23 ወይም፣ የኢያዕርን መኖሪያ ነጠቁ

እነዚህ ሁሉ የገለዓድ አባት የማኪር ዘሮች ነበሩ።

24ኤስሮም በካሌብ ኤፍራታ ከሞተ በኋላ፣ ሚስቱ አቢያ የቴቁሔን አባት2፥24 በዚህም ሆነ በቍጥር 42፡45፡49-52 ላይ፣ አባት ማለት፣ የአገር ሽማግሌ ወይም፣ የጦር መሪ ማለት ነው። አሽሑርን ወለደችለት።

የኤስሮም ልጅ ይረሕምኤል

25የኤስሮም የበኵር ልጅ የይረሕምኤል ወንዶች ልጆች፤

የበኵር ልጁ ራም፣ ቡናህ፣ ኦሬን፣ ኦጼም፣ አኪያ። 26ይረሕምኤል ዓጣራ የተባለች ሌላ ሚስት ነበረችው፤ እርሷም የኦናም እናት ነበረች።

27የይረሕምኤል የበኵር ልጁ የራም ወንዶች፤

መዓስ፣ ያሚን፣ ዔቄር።

28የኦናም ወንዶች ልጆች፤

ሸማይና ያዳ።

የሸማይ ወንዶች ልጆች፤

ናዳብና አቢሱር።

29የአቢሱር ሚስት አቢካኢል ትባላለች፤ እርሷም አሕባንንና ሞሊድ የተባሉ ልጆች ወለደችለት።

30የናባድ ወንዶች ልጆች፤

ሴሌድ፣ አፋይም፤ ሴሌድ ወንድ ልጅ ሳይወልድ ሞተ።

31የአፋይም ወንድ ልጅ፤

ይሽዒ። ይሽዒም ሶሳን ወለደ።

ሶሳን አሕላይን ወለደ።

32የሸማይ ወንድም የያዳ ወንዶች ልጆች፤ ዬቴር፣ ዮናታን፤ ዬቴርም ልጅ ሳይወልድ ሞተ።

33የዮናታን ወንዶች ልጆች፤

ፌሌት፣ ዛዛ።

እነዚህ የይረሕምኤል ዘሮች ነበሩ።

34ሶሳን ሴቶች ልጆች እንጂ ወንዶች ልጆች አልነበሩትም።

እርሱም ኢዮሄል የተባለ ግብፃዊ አገልጋይ ነበረው። 35ሶሳን ልጁን ለአገልጋዩ ለኢዮሄል ሚስት ትሆነው ዘንድ ሰጠው፤ እርሷም ዓታይ የተባለ ወንድ ልጅ ወለደችለት።

36ዓታይ ናታንን ወለደ፤

ናታንም ዛባድን ወለደ፤

37ዛባድ ኤፍላልን ወለደ፤

ኤፍላል ዖቤድን ወለደ፤

38ዖቤድ ኢዩን ወለደ፤

ኢዩ ዓዛርያስን ወለደ፤

39ዓዛርያስ ኬሌስን ወለደ፤

ኬሌስ ኤልዓሣን ወለደ፤

40ኤልዓሣ ሲስማይን ወለደ፤

ሲስማይ ሰሎምን ወለደ፤

41ሰሎም የቃምያን ወለደ፤

የቃምያም ኤሊሳማን ወለደ።

የካሌብ ጐሣዎች

42የይረሕምኤል ወንድም የካሌብ ወንዶች ልጆች፤

የበኵር ልጁ ሞሳ ሲሆን፣ እርሱም ዚፍን ወለደ፤

ዚፍም መሪሳን2፥42 የዚህ ቃል የዕብራይስጡ ትርጕም በትክክል አይታወቅም። ወለደ፤ መሪሳም ኬብሮንን ወለደ።

43የኬብሮን ወንዶች ልጆች፤

ቆሬ፣ ተፉዋ፣ ሬቄም፣ ሽማዕ።

44ሽማዕ ረሐምን ወለደ፤

ረሐምም ዮርቅዓምን ወለደ።

ሬቄም ሸማይን ወለደ፤

45ሸማይም ማዖንን ወለደ፤

ማዖንም ቤት ጹርን ወለደ።

46የካሌብ ቁባት ዔፉ ሐራንን፣ ሞዳን፣ ጋዜዝን ወለደች።

ሐራንም ጋዜዝን ወለደ።

47የያህዳይ ወንዶች ልጆች፤

ሬጌም፣ ኢዮታም፣ ጌሻን፣ ፋሌጥ፣ ዔፋ፣ ሸዓፍ።

48የካሌብ ቁባት ማዕካ ሼቤርን፣ ቲርሐናን ወለደችለት።

49እንዲሁም የመድማናን አባት ሸዓፍን፣ የመክቢናንና የጊብዓን አባት ሱሳን ወለደች።

ካሌብ ዓክሳ የተባለች ልጅ ነበረችው።

50እነዚህ ሁሉ የካሌብ ዘሮች ነበሩ።

የኤፍራታ የበኵር ልጅ የሑር ወንዶች ልጆች፤

ሦባል የቂርያትይዓሪም አባት፤ 51ሰልሞን የቤተ ልሔም አባት፤ ሐሬፍ የቤት ጋዴር አባት።

52የቂርያትይዓሪም አባት የሦባል ዘሮች፤

የመናሕታውያን ነዋሪዎች እኩሌታ፣ ሀሮኤ፤ 53እንዲሁም የቂርያትይዓሪም ጐሣዎች፤ ይትራውያን፣ ፉታውያን፣ ሹማታውያን፣ ሚሽራውያን፣ ጾርዓውያንና ኤሽታኦላውያን ከእነዚህ የመጡ ጐሣዎች ነበሩ።

54የሰልሞን ዘሮች፤

ቤተ ልሔም፣ ነጦፋውያን፣ ዓጣሮት ቤት ዮአብ፣ የመናሕታውያን እኩሌታ፣ ጾርዓውያን። 55በያቤጽ የሚኖሩ የጸሐፍት ጐሣዎች2፥55 ወይም፣ ሶፍራውያን ቲርዓውያን፣ ሺምዓታውያን፣ ሡካታውያን። እነዚህ ከሬካብ ቤት አባት ከሐማት የመጡ ቄናውያን ናቸው።

New International Version – UK

1 Chronicles 2:1-55

Israel’s sons

1These were the sons of Israel: Reuben, Simeon, Levi, Judah, Issachar, Zebulun, 2Dan, Joseph, Benjamin, Naphtali, Gad and Asher.

Judah

To Hezron’s sons

3The sons of Judah:

Er, Onan and Shelah. These three were born to him by a Canaanite woman, the daughter of Shua.

(Er, Judah’s firstborn, was wicked in the Lord’s sight; so the Lord put him to death.)

4Judah’s daughter-in-law Tamar bore Perez and Zerah to Judah.

He had five sons in all.

5The sons of Perez:

Hezron and Hamul.

6The sons of Zerah:

Zimri, Ethan, Heman, Kalkol and Darda2:6 Many Hebrew manuscripts, some Septuagint manuscripts and Syriac (see also 1 Kings 4:31); most Hebrew manuscripts Dara – five in all.

7The son of Karmi:

Achar,2:7 Achar means trouble; Achar is called Achan in Joshua. who brought trouble on Israel by violating the ban on taking devoted things.2:7 The Hebrew term refers to the irrevocable giving over of things or persons to the Lord, often by totally destroying them.

8The son of Ethan:

Azariah.

9The sons born to Hezron were:

Jerahmeel, Ram and Caleb.2:9 Hebrew Kelubai, a variant of Caleb

From Ram son of Hezron

10Ram was the father of Amminadab,

and Amminadab the father of Nahshon, the leader of the people of Judah.

11Nahshon was the father of Salmon,2:11 Septuagint (see also Ruth 4:21); Hebrew Salma

Salmon the father of Boaz,

12Boaz the father of Obed

and Obed the father of Jesse.

13Jesse was the father of

Eliab his firstborn; the second son was Abinadab,

the third Shimea, 14the fourth Nethanel,

the fifth Raddai, 15the sixth Ozem

and the seventh David.

16Their sisters were Zeruiah and Abigail.

Zeruiah’s three sons were Abishai, Joab and Asahel.

17Abigail was the mother of Amasa, whose father was Jether the Ishmaelite.

Caleb son of Hezron

18Caleb son of Hezron had children by his wife Azubah (and by Jerioth). These were her sons:

Jesher, Shobab and Ardon.

19When Azubah died, Caleb married Ephrath, who bore him Hur.

20Hur was the father of Uri, and Uri the father of Bezalel.

21Later, Hezron, when he was sixty years old, married the daughter of Makir the father of Gilead. He made love to her, and she bore him Segub.

22Segub was the father of Jair, who controlled twenty-three towns in Gilead.

23(But Geshur and Aram captured Havvoth Jair,2:23 Or captured the settlements of Jair as well as Kenath with its surrounding settlements – sixty towns.)

All these were descendants of Makir the father of Gilead.

24After Hezron died in Caleb Ephrathah, Abijah the wife of Hezron bore him Ashhur the father2:24 Father may mean civic leader or military leader; also in verses 42, 45, 49-52 and possibly elsewhere. of Tekoa.

Jerahmeel son of Hezron

25The sons of Jerahmeel the firstborn of Hezron:

Ram his firstborn, Bunah, Oren, Ozem and2:25 Or Oren and Ozem, by Ahijah. 26Jerahmeel had another wife, whose name was Atarah; she was the mother of Onam.

27The sons of Ram the firstborn of Jerahmeel:

Maaz, Jamin and Eker.

28The sons of Onam:

Shammai and Jada.

The sons of Shammai:

Nadab and Abishur. 29Abishur’s wife was named Abihail, who bore him Ahban and Molid.

30The sons of Nadab:

Seled and Appaim. Seled died without children.

31The son of Appaim:

Ishi, who was the father of Sheshan. Sheshan was the father of Ahlai.

32The sons of Jada, Shammai’s brother:

Jether and Jonathan. Jether died without children.

33The sons of Jonathan:

Peleth and Zaza.

These were the descendants of Jerahmeel.

34Sheshan had no sons – only daughters.

He had an Egyptian servant named Jarha. 35Sheshan gave his daughter in marriage to his servant Jarha, and she bore him Attai.

36Attai was the father of Nathan,

Nathan the father of Zabad,

37Zabad the father of Ephlal,

Ephlal the father of Obed,

38Obed the father of Jehu,

Jehu the father of Azariah,

39Azariah the father of Helez,

Helez the father of Eleasah,

40Eleasah the father of Sismai,

Sismai the father of Shallum,

41Shallum the father of Jekamiah,

and Jekamiah the father of Elishama.

The clans of Caleb

42The sons of Caleb the brother of Jerahmeel:

Mesha his firstborn, who was the father of Ziph,

and his son Mareshah,2:42 The meaning of the Hebrew for this phrase is uncertain. who was the father of Hebron.

43The sons of Hebron:

Korah, Tappuah, Rekem and Shema.

44Shema was the father of Raham,

and Raham the father of Jorkeam.

Rekem was the father of Shammai.

45The son of Shammai was Maon,

and Maon was the father of Beth Zur.

46Caleb’s concubine Ephah was the mother of

Haran, Moza and Gazez.

Haran was the father of Gazez.

47The sons of Jahdai:

Regem, Jotham, Geshan, Pelet, Ephah and Shaaph.

48Caleb’s concubine Maakah was the mother of

Sheber and Tirhanah.

49She also gave birth to Shaaph the father of Madmannah

and to Sheva the father of Makbenah and Gibea.

Caleb’s daughter was Aksah.

50These were the descendants of Caleb.

The sons of Hur the firstborn of Ephrathah:

Shobal the father of Kiriath Jearim, 51Salma the father of Bethlehem, and Hareph the father of Beth Gader.

52The descendants of Shobal the father of Kiriath Jearim were:

Haroeh, half the Manahathites, 53and the clans of Kiriath Jearim: the Ithrites, Puthites, Shumathites and Mishraites. From these descended the Zorathites and Eshtaolites.

54The descendants of Salma:

Bethlehem, the Netophathites, Atroth Beth Joab, half the Manahathites, the Zorites, 55and the clans of scribes2:55 Or of the Sopherites who lived at Jabez: the Tirathites, Shimeathites and Sucathites. These are the Kenites who came from Hammath, the father of the Rekabites.2:55 Or father of Beth Rekab