1 ዜና መዋዕል 15 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

1 ዜና መዋዕል 15:1-29

ታቦቱ ወደ ኢየሩሳሌም ተወሰደ

15፥25–16፥3 ተጓ ምብ – 2ሳሙ 6፥12-19

1ዳዊት በስሙ በተጠራችው ከተማ ለራሱ ቤቶችን ሠራ፤ ለእግዚአብሔር ታቦት ቦታ አዘጋጅቶ ድንኳን ተከለ። 2ከዚያም ዳዊት፣ “የእግዚአብሔርን ታቦት እንዲሸከሙና ለዘላለም በፊቱ እንዲያገለግሉ እግዚአብሔር ከመረጣቸው ከሌዋውያን በቀር፣ የእግዚአብሔርን ታቦት ማንም አይሸከም” ሲል አዘዘ።

3ዳዊት የእግዚአብሔርን ታቦት ወዳዘጋጀለት ስፍራ እንዲያመጡ እስራኤልን ሁሉ በኢየሩሳሌም ሰበሰበ።

4የአሮንን ዘሮችና ሌዋውያኑንም በአንድነት ሰበሰበ፤

5ከቀዓት ዘሮች፣

አለቃውን ኡርኤልንና አንድ መቶ ሃያ የሥጋ ዘመዶቹን፤

6ከሜራሪ ዘሮች፣

አለቃውን ዓሣያንና ሁለት መቶ ሃያ የሥጋ ዘመዶቹን፤

7ከጌድሶን ዘሮች፣

አለቃውን ኢዮኤልንና አንድ መቶ ሠላሳ የሥጋ ዘመዶቹን፤

8ከኤሊጻፋን ዘሮች፣

አለቃውን ሸማያንና ሁለት መቶ የሥጋ ዘመዶቹን፤

9ከኬብሮን ዘሮች፣

አለቃውን ኤሊኤልንና ሰማንያ የሥጋ ዘመዶቹን፤

10ከዑዝኤል ዘሮች፣

አለቃውን አሚናዳብንና አንድ መቶ ዐሥራ ሁለት የሥጋ ዘመዶቹን።

11ከዚያም ዳዊት ካህናቱን ሳዶቅንና አብያታርን፣ ሌዋውያኑን ኡርኤልን፣ ዓሣያን፣ ኢዩኤልን፣ ሸማያን፣ ኤሊኤልንና አሚናዳብን ጠርቶ፣ 12እንዲህ አላቸው፤ “እንግዲህ እናንተ የሌዋውያን ቤተ ሰብ አለቆች ስለ ሆናችሁ፣ እናንተና ወንድሞቻችሁ ሌዋውያን ራሳችሁን ቀድሱ፤ ከዚያም የእስራኤልን አምላክ የእግዚአብሔርን ታቦት ወዳዘጋጀሁለት ቦታ አምጡ። 13የአምላካችን የእግዚአብሔር ቍጣ በላያችን ላይ እንዲህ የነደደው እናንተ ሌዋውያኑ ቀድሞም ስላላመጣችሁት ነው፤ እኛም ብንሆን ምን ማድረግ እንዳለብን በታዘዘው መሠረት አልጠየቅነውም።” 14ስለዚህ ካህናቱና ሌዋውያኑ የእስራኤልን አምላክ የእግዚአብሔርን ታቦት ለማምጣት ራሳቸውን ቀደሱ። 15ሙሴ በእግዚአብሔር ቃል እንዳዘዘው፣ ሌዋውያኑ የእግዚአብሔርን ታቦት በትከሻቸው ላይ በመሎጊያዎች አድርገው ተሸከሙ።

16ዳዊትም በዜማ መሣሪያ፣ ማለትም በመሰንቆ፣ በበገናና በጸናጽል እየታጀቡ የደስታ ዜማዎችን የሚያዜሙ መዘምራንን ከወንድሞቻቸው መካከል እንዲሾሙ ለሌዋውያኑ መሪዎች ነገራቸው።

17ስለዚህ ሌዋውያኑ የኢዮኤልን ልጅ ኤማንን ሾሙ፤ ከወንድሞቹም የበራክያን ልጅ አሳፍን፣ ከወንድሞቻቸው ከሜራሪ ዘሮች የቂሳን ልጅ ኤታንን ሾሙ፤ 18ከእነርሱም ጋር ወንድሞቻቸው በደረጃ ተሾሙ፤ እነርሱም ዘካርያስ15፥18 ሦስት የዕብራይስጥ ቅጆችና በርካታ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞች (እንዲሁም ቍ20 እና 1ዜና 16፥5 ይመ)፤ በርካታ የዕብራይስጥ ቅጆች የዘካርያስ ልጅ ወይም ዘካርያስ፣ ቤን ይላሉ።፣ ያዝኤል፣ ሰሚራሞት፣ ይሒኤል፣ ዑኒን፣ ኤልያብ፣ በናያስ፣ መዕሤያን፣ መቲትያ፣ ኤሊፍሌሁ፣ ሚቅኔያ፣ ደግሞም በር ጠባቂዎቹ ዖቤድኤዶምና ይዒኤል15፥18 ዕብራይስጡ ከዚህ ጋር ይስማማል፤ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕም (እንዲሁም ቍ21) ግን ይዒኤልና ዓዛዝያ ይላል። ነበሩ።

19መዘምራኑ ኤማን፣ አሳፍና ኤታን በናስ ጸናጽል ድምፁን ከፍ አድርገው እንዲያሰሙ ተሾሙ፤ 20ዘካርያስ፣ ዓዝኤል፣ ሰሚራሞት፣ ይሒኤል፣ ዑኒ፣ ኤልያብ፣ መዕሤያና በናያስ ደግሞ በአላሞት15፥20 ምናልባት የዜማ ስም ነው። ቅኝት መሰንቆ ይገርፉ ነበር። 21እንዲሁም መቲትያ፣ ኤሊፍሌሁ፣ ሚቅኔያ፣ ዖቤድኤዶም፣ ይዒኤል፣ ዓዛዝያ፣ በሺሚኒት15፥21 ምናልባት የዜማ ስም ነው። ቅኝት በገና ይደረድሩ ነበር። 22የዝማሬው ኀላፊ ሌዋዊው አለቃ ክናንያ ነበረ፤ ይህን ኀላፊነት የወሰደው በዝማሬ የተካነ ስለ ነበር ነው።

23በራክያና ሕልቃና የታቦቱ በር ጠባቂዎች ነበሩ፤ 24ካህናቱ ሰበኒያ፣ ኢዮሣፍጥ፣ ናትናኤል፣ ዓማሣይ፣ ዘካርያስ፣ በናያስና አልዓዛር በእግዚአብሔር ታቦት ፊት መለከት ይነፉ ነበር። ዖቤድኤዶምና ይሒያ ደግሞ የታቦቱ በር ጠባቂዎች ነበሩ።

25ስለዚህ ዳዊት የእስራኤል ሽማግሌዎችና የሻለቃው አዛዦች የእግዚአብሔርን የቃል ኪዳኑን ታቦት ከዖቤድኤዶም ቤት በደስታ ለማምጣት ሄዱ። 26የእግዚአብሔርን የቃል ኪዳን ታቦት የተሸከሙትን ሌዋውያን እግዚአብሔር ረድቷቸው ስለ ነበር፣ ሰባት ኮርማዎችና ሰባት አውራ በጎች ሠዉ። 27ታቦቱን የተሸከሙት ሌዋውያን ሁሉ፣ መዘምራኑና የመዘምራኑ አለቃ ክናንያ የለበሱትን ዐይነት ከቀጭን በፍታ የተሠራ ልብስ ዳዊትም ለብሶ ነበር፤ እንዲሁም ከበፍታ የተሠራ ኤፉድ ለብሶ ነበር። 28በዚህ ሁኔታ መላው የእስራኤል ሕዝብ በሆታ ቀንደ መለከትና እንቢልታ እየነፉ፣ ጸናጽል እየጸነጸሉ፣ መሰንቆና በገና እየደረደሩ የእግዚአብሔርን የኪዳኑን ታቦት አመጡ።

29የእግዚአብሔር የኪዳኑ ታቦት ወደ ዳዊት ከተማ ሲገባ የሳኦል ልጅ ሜልኮል በመስኮት ሆና ተመለከተች፤ ንጉሡ ዳዊት ደስ ብሎት ሲያሸበሽብ አይታ በልቧ ናቀችው።

Thai New Contemporary Bible

1พงศาวดาร 15:1-29

อัญเชิญหีบพันธสัญญามายังกรุงเยรูซาเล็ม

(2ซมอ.6:12-19)

1หลังจากดาวิดได้สร้างพระตำหนักต่างๆ สำหรับพระองค์ในเมืองดาวิดแล้ว ดาวิดก็ทรงเตรียมที่สำหรับหีบพันธสัญญาของพระเจ้าและตั้งพลับพลาขึ้นหลังหนึ่ง 2แล้วดาวิดตรัสว่า “อย่าให้ผู้ใดอื่นเว้นแต่ชนเลวีอัญเชิญหีบพันธสัญญาของพระเจ้า เพราะว่าองค์พระผู้เป็นเจ้าทรงเลือกพวกเขาให้หามหีบพันธสัญญาขององค์พระผู้เป็นเจ้า และรับใช้อยู่ต่อหน้าพระองค์ตลอดไป”

3ดาวิดจึงทรงให้เรียกชุมนุมอิสราเอลทั้งปวงในกรุงเยรูซาเล็ม เพื่ออัญเชิญหีบพันธสัญญาขององค์พระผู้เป็นเจ้ามายังที่ซึ่งดาวิดจัดเตรียมไว้ 4แล้วทรงให้วงศ์วานของอาโรนและชนเลวีมาพร้อมหน้ากัน

5จากวงศ์วานโคฮาท

อุรีเอลเป็นหัวหน้าและญาติ 120 คน

6จากวงศ์วานเมรารี

อาสายาห์เป็นหัวหน้าและญาติ 220 คน

7จากวงศ์วานเกอร์โชน15:7 ภาษาฮีบรูว่าเกอร์โชมเป็นอีกรูปหนึ่งของเกอร์โชน

โยเอลเป็นหัวหน้าและญาติ 130 คน

8จากวงศ์วานเอลีซาฟาน

เชไมอาห์เป็นหัวหน้าและญาติ 200 คน

9จากวงศ์วานเฮโบรน

เอลีเอลเป็นหัวหน้าและญาติ 80 คน

10จากวงศ์วานอุสซีเอล

อัมมีนาดับเป็นหัวหน้าและญาติ 112 คน

11แล้วดาวิดทรงบัญชาให้ปุโรหิตทั้งสองคือ ศาโดกกับอาบียาธาร์ และคนเลวีได้แก่ อุรีเอล อาสายาห์ โยเอล เชไมอาห์ เอลีเอล และอัมมีนาดับมาเข้าเฝ้า 12แล้วตรัสว่า “ท่านทั้งหลายเป็นหัวหน้าตระกูลต่างๆ ของเลวี ท่านและพวกพ้องชาวเลวีจงชำระตนให้บริสุทธิ์และนำหีบพันธสัญญาของพระยาห์เวห์พระเจ้าแห่งอิสราเอลมายังสถานที่ซึ่งเราได้จัดเตรียมไว้ 13ครั้งก่อนพระยาห์เวห์พระเจ้าของเราทรงพระพิโรธพวกเรา เพราะพวกท่านซึ่งเป็นคนเลวีไม่ได้เป็นผู้อัญเชิญหีบพันธสัญญา เราไม่ได้ทูลถามพระองค์ถึงวิธีการที่จะนำหีบมาตามที่ทรงกำหนดไว้” 14ฉะนั้นเหล่าปุโรหิตและคนเลวีจึงชำระตนเพื่ออัญเชิญหีบพันธสัญญาของพระยาห์เวห์พระเจ้าของอิสราเอล 15จากนั้นคนเลวีได้ยกหีบพันธสัญญาของพระเจ้าขึ้นบ่าโดยใช้คานหาม ตามที่โมเสสได้สั่งไว้ตามพระดำรัสขององค์พระผู้เป็นเจ้า

16ดาวิดตรัสสั่งบรรดาหัวหน้าของคนเลวีให้แต่งตั้งพี่น้องเป็นนักร้อง เพื่อขับร้องบทเพลงรื่นเริงยินดีคลอเสียงเครื่องดนตรีต่างๆ ได้แก่ พิณใหญ่ พิณเขาคู่ และฉาบ

17ชนเลวีจึงแต่งตั้งเฮมานบุตรโยเอล แต่งตั้งอาสาฟบุตรเบเรคิยาห์จากหมู่พี่น้องของเขา และแต่งตั้งเอธานบุตรคูชายาห์จากพี่น้องตระกูลเมรารี 18พี่น้องที่เป็นผู้ช่วยรองลงมาได้แก่ เศคาริยาห์15:18 สำเนาต้นฉบับภาษาฮีบรูส่วนใหญ่ว่าเศคาริยาห์ บุตร และหรือเศคาริยาห์ เบน และ(ดู ข้อ 20 และ 16:5) ยาอาซีเอล เชมิราโมท เยฮีเอล อุนนี เอลีอับ เบไนยาห์ มาอาเสอาห์ มัททีธิยาห์ เอลีเฟเลหุ มิกเนยาห์ โอเบดเอโดม และเยอีเอล15:18 ฉบับ LXX. ว่าเยอีเอลและอาซาซิยาห์(ดูข้อ 21)ยามเฝ้าประตู

19นักดนตรีคือเฮมาน อาสาฟ และเอธานเป็นผู้ตีฉาบทองสัมฤทธิ์ 20เศคาริยาห์ เอซีเอล เชมิราโมท เยฮีเอล อุนนี เอลีอับ มาอาเสอาห์ และเบไนยาห์เล่นพิณใหญ่คลอตามทำนองอาลาโมท 21มัททีธิยาห์ เอลีเฟเลหุ มิกเนยาห์ โอเบดเอโดม เยอีเอล และอาซาซิยาห์ เล่นพิณเขาคู่คลอตามทำนองเชมินิท 22เคนานิยาห์หัวหน้าของคนเลวีรับผิดชอบดูแลการขับร้องเพราะเขาเชี่ยวชาญมาก

23เบเรคิยาห์และเอลคานาห์เป็นยามประตูเฝ้าหีบพันธสัญญา 24เชบานิยาห์ โยชาฟัท เนธันเอล อามาสัย เศคาริยาห์ เบไนยาห์ และเอลีเอเซอร์ ล้วนเป็นปุโรหิตผู้เป่าแตรนำหน้าหีบพันธสัญญาของพระเจ้า โอเบดเอโดมกับเยฮียาห์ก็เป็นยามประตูเฝ้าหีบพันธสัญญาด้วย

25ดาวิดและบรรดาผู้อาวุโสของอิสราเอลและนายทัพนายกองจึงไปอัญเชิญหีบพันธสัญญาขององค์พระผู้เป็นเจ้ามาจากบ้านของโอเบดเอโดมด้วยความชื่นชมยินดี 26เพราะพระเจ้าทรงช่วยคนเลวีที่หามหีบพันธสัญญาขององค์พระผู้เป็นเจ้า เขาทั้งปวงจึงถวายวัวผู้เจ็ดตัวและแกะผู้เจ็ดตัว 27ดาวิดพร้อมทั้งคนเลวีทั้งหมดที่อัญเชิญหีบพันธสัญญา คณะนักร้อง และเคนานิยาห์ผู้รับผิดชอบคณะนักร้องต่างก็สวมชุดผ้าลินิน ดาวิดทรงสวมเอโฟดลินินด้วย 28เป็นอันว่าปวงชนอิสราเอลได้อัญเชิญหีบพันธสัญญาขององค์พระผู้เป็นเจ้ามายังกรุงเยรูซาเล็มท่ามกลางเสียงโห่ร้องชื่นชมยินดี เสียงเป่าเขาแกะและแตร เสียงฉาบ เสียงพิณใหญ่และพิณเขาคู่

29ขณะที่หีบพันธสัญญาขององค์พระผู้เป็นเจ้าเข้าสู่เมืองดาวิด มีคาลราชธิดาของซาอูลมองจากหน้าต่าง เห็นกษัตริย์ดาวิดทรงร่ายรำและเฉลิมฉลองก็นึกดูแคลนอยู่ในใจ