1 ዜና መዋዕል 12 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

1 ዜና መዋዕል 12:1-40

ከዳዊት ጋር የተቀላቀሉ ተዋጊዎች

1ዳዊት ከቂስ ልጅ ከሳኦል ፊት ሸሽቶ በጺቅላግ ሳለ ወደ እርሱ የመጡት ሰዎች እነዚህ ናቸው፤ እነርሱም በጦርነቱ ላይ ከረዱት ተዋጊዎች መካከል ነበሩ። 2ሰዎቹ ቀስተኞች ሲሆኑ፣ በቀኝም ሆነ በግራ እጃቸው ፍላጻ መወርወርና ድንጋይ መወንጨፍ የሚችሉ ነበሩ፤ እነርሱም ከብንያም ነገድ የሆነው የሳኦል ሥጋ ዘመዶች ነበሩ፤

3አለቃቸው አሒዔዝር ነበረ፤ ከእርሱም በኋላ ኢዮአስ ነበረ፤ ሁለቱም የጊብዓዊው የሸማዓ ልጆች ነበሩ፤

የዓዝሞት ልጆች ይዝኤልና ፋሌጥ፣ በራኪያ፣ ዓናቶታዊው ኢዩ፤

4ገባዖናዊው ሰማያስ ከሠላሳዎቹ መካከል ኀያልና የሠላሳዎቹም መሪ ነበረ፤

ኤርምያስ፣ የሕዚኤል፣ ዮሐናን፣ ገድሮታዊው ዮዛባት፣ 5ኤሉዛይ፣ ለኢያሪሙት፣ በዓልያ፣ ሰማራያ፣ ሐሩፋዊው ሰፋጥያስ፣

6ቆሬያውያኑ ሕልቃና፣ ይሺያ፣ ዓዘርኤል፣ ዮዛር፣ ያሾብዓም፤

7የጌዶር ሰው ከሆነው ደግሞ የይሮሐም ልጆች ዮዔላና ዝባድያ።

8ዳዊት በምድረ በዳ በሚገኘው ምሽጉ ውስጥ ሳለ፣ ከጋድ ነገድ የሆኑ ሰዎች መጥተው የእርሱን ሰራዊት ተቀላቀሉ፤ እነርሱም ለውጊያ የተዘጋጁ ጋሻና ጦር ለመያዝ የሚችሉ ብርቱ ተዋጊዎች ነበሩ፤ ፊታቸው እንደ አንበሳ ፊት የሚያስፈራና በየተራራውም ላይ እንደሚዘልል ሚዳቋ ፈጣኖች ነበሩ።

9የእነዚህም አለቃ ዔጼር ነበረ፤

ሁለተኛው አዛዥ አብድዩ፣ ሦስተኛው ኤልያብ፣

10አራተኛው መስመና፣ አምስተኛው ኤርምያስ፣

11ስድስተኛው ዓታይ፣ ሰባተኛው ኢሊኤል፣

12ስምንተኛው ዮሐናን፣ ዘጠነኛው ኤልዛባድ፣

13ዐሥረኛው ኤርምያስ፣ ዐሥራ አንደኛው መክበናይ።

14እነዚህ ጋዳውያን የጦር አዛዦች ነበሩ፣ ከእነርሱ ታናሽ የሆነው እንደ መቶ፣ ታላቅ የሆነው ደግሞ እንደ ሺሕ አለቃ ይቈጠር ነበር። 15በመጀመሪያው ወር የዮርዳኖስ ወንዝ ከአፍ እስከ ገደፍ ሞልቶ ሳለ፣ ወንዙን ተሻግረው በስተ ምሥራቅና በስተ ምዕራብ ሸለቆዎች ይኖሩ የነበሩትን ሁሉ ከዚያ ያባረሩት እነዚህ ሰዎች ነበሩ።

16ሌሎች ከብንያምና ከይሁዳም ወገን የሆኑ ሰዎች ዳዊት ወደሚገኝበት ምሽግ መጡ። 17ዳዊትም እነዚህን ሰዎች ሊቀበል ወጥቶ እንዲህ አላቸው፤ “የመጣችሁት ልትረዱኝና በሰላም ከሆነ፣ ከእኔ ጋር እንድትሰለፉ ልቀበላችሁ ዝግጁ ነኝ፤ ነገር ግን እጄ ከበደል ንጹሕ ሆኖ ሳለ፣ ለጠላቶቼ አሳልፋችሁ ልትሰጡኝ ከሆነ፣ የአባቶቻችን አምላክ ይመልከተው፤ ይፍረደውም።”

18ከዚያም የእግዚአብሔር መንፈስ በሠላሳዎቹ አለቃ በዓማሣይ ላይ ወረደ፤ እርሱም እንዲህ አለ፤

“ዳዊት ሆይ፤ እኛ የአንተ ነን፤

የእሴይ ልጅ ሆይ፤ እኛ ከአንተ ጋር ነን፤

ሰላም ፍጹም ሰላም ለአንተ ይሁን፤

አንተን ለሚረዱም ሁሉ ሰላም ይሁን፤

አምላክህ ይረዳሃልና።”

ስለዚህ ዳዊት ተቀበላቸው፤ የሰራዊቱም አለቃ አደረጋቸው።

19ዳዊት ከፍልስጥኤማውያን ጋር ተባብሮ ሳኦልን ለመውጋት በሄደ ጊዜ፣ ከምናሴ ነገድ የሆኑ ጥቂት ሰዎች ከድተው ከዳዊት ሰራዊት ጋር ተቀላቀሉ። እርሱ ግን ርዳታ አላደረገላቸውም፤ ምክንያቱም የፍልስጥኤማውያን ገዦች ምክር ካደረጉ በኋላ እንዲህ ሲሉ ልከውት ነበር፤ “ከድቶ ወደ ጌታው ወደ ሳኦል ቢሄድ እኛን ያስጨርሰናል።” 20ዳዊት ወደ ጺቅላግ በሄደ ጊዜ ከድተው ወደ እርሱ የተቀላቀሉ የምናሴ ነገድ ሰዎች እነዚህ ነበሩ፤ ዓድና፣ ዮዛባት፣ ይዲኤል፣ ሚካኤል፣ ዮዛባት፣ ኤሊሁ፣ ጺልታይ፤ እነዚህ በምናሴ ግዛት ሳሉ ሻለቆች ነበሩ። 21ሁሉም ብርቱ ተዋጊዎችና በዳዊትም ሰራዊት ውስጥ አዛዦች ስለ ነበሩ፣ አደጋ ጣዮችን በመውጋት ረዱት። 22ሰራዊቱም እንደ እግዚአብሔር ሰራዊት12፥22 ወይም፣ ታላቅና ኀያል ሰራዊት እስኪሆን ድረስ፣ ዳዊትን ለመርዳት በየዕለቱ ብዙ ሰዎች ይጐርፉ ነበር።

ሌሎችም በኬብሮን የዳዊትን ሰራዊት ተቀላቀሉ

23እግዚአብሔር ለዳዊት በገባለት ቃል ኪዳን መሠረት፣ የሳኦልን መንግሥት አንሥተው ለእርሱ ለመስጠት ዳዊት ወደሚገኝበት ወደ ኬብሮን የመጡት ሰዎች ቍጥር ይህ ነው፤

24ጋሻና ጦር አንግበው ለጦርነት የተዘጋጁት የይሁዳ ሰዎች ስድስት ሺሕ ስምንት መቶ፤

25ከስምዖን ነገድ ለጦርነት ዝግጁ የሆኑ ሰባት ሺሕ አንድ መቶ።

26ከሌዊ ነገድ አራት ሺሕ ስድስት መቶ፤ 27የአሮን ቤተ ሰብ መሪ የሆነውን ዮዳሄን ጨምሮ ሦስት ሺሕ ሰባት መቶ ሰዎች፤ 28ወጣቱ ብርቱ ተዋጊ ጻዶቅና ከቤተ ሰቡ ሃያ ሁለት የጦር አለቆች፤

29የሳኦል ሥጋ ዘመድ የሆኑ የብንያም ሰዎች ሦስት ሺሕ፤ ከእነዚህም አብዛኞቹ እስከዚያች ጊዜ ድረስ ለሳኦል ቤት ታማኝ ነበሩ፤

30ከኤፍሬም ሰዎች በጐሣዎቻቸው ዘንድ ታዋቂ የሆኑ ብርቱ ተዋጊዎች ሃያ ሺሕ ስምንት መቶ፤

31ከምናሴ ነገድ እኩሌታ ዐሥራ ስምንት ሺሕ ሰዎች፤ እነርሱም ዳዊትን ለማንገሥ በየስማቸው ተጽፈው የመጡ ነበሩ።

32ዘመኑን የተረዱና እስራኤላውያንም ምን ማድረግ እንደሚገባቸው የተገነዘቡ የይሳኮር ሰዎች ሁለት መቶ አለቆች፤ በእነርሱም ሥር ሆነው የሚታዘዙ ዘመዶቻቸው።

33ልምድ ያላቸው፣ በሁሉም ዐይነት መሣሪያ ለመዋጋት የተዘጋጁና ዳዊትን ለመርዳት የመጡት መንታ ልብ የሌላቸው የዛብሎን ሰዎች ሃምሳ ሺሕ፤

34ከንፍታሌም ሰዎች አንድ ሺሕ የጦር አለቆች፤ ከእነርሱም ጋር ጋሻና ጦር የያዙ ሠላሳ ሰባት ሺሕ ሰዎች፤

35ከዳን ሰዎች ለጦርነት የተዘጋጁ ሃያ ስምንት ሺሕ ስድስት መቶ፤

36ከአሴር ሰዎች ልምድ ያላቸውና ለጦርነት የተዘጋጁ ወታደሮች አርባ ሺሕ፤

37ከምሥራቅ ዮርዳኖስ ከሮቤል፣ ከጋድና ከምናሴ ነገድ እኩሌታ ልዩ ልዩ ዐይነት መሣሪያ የታጠቁ አንድ መቶ ሃያ ሺሕ ሰዎች።

38እነዚህ ሁሉ በሰራዊቱ ውስጥ ለማገልገል ፈቃደኞች የሆኑ ተዋጊዎች ናቸው።

ወደ ኬብሮን የመጡትም ዳዊትን በእስራኤል ሁሉ ላይ ለማንገሥ ወስነው ስለ ነበር ነው። የቀሩትም እስራኤላውያን ሁሉ ዳዊትን ለማንገሥ በአንድ ሐሳብ ጸኑ። 39የሚያስፈልጋቸውንም ቤተ ሰቦቻቸው አዘጋጅተውላቸው ስለ ነበር፣ ሰዎቹ እየበሉና እየጠጡ ከዳዊት ጋር ሦስት ቀን ቈዩ። 40እንዲሁም ሩቅ ከሆነው ከይሳኮር፣ ከዛብሎንና ከንፍታሌም አገር ሳይቀር ጎረቤቶቻቸው በአህያ፣ በግመል፣ በበቅሎና በበሬ ጭነው ምግብ አመጡላቸው፤ በእስራኤል ታላቅ ደስታ ስለሆነ ዱቄት፣ የበለስና የዘቢብ ጥፍጥፍ፣ የወይን ጠጅ፣ የወይራ ዘይት፣ የቀንድ ከብትና በጎች በገፍ ቀርበው ነበር።

Thai New Contemporary Bible

1พงศาวดาร 12:1-40

เหล่านักรบมาสมทบกับดาวิด

1ต่อไปนี้คือผู้ที่มาสมทบกับดาวิดที่ศิกลาก ขณะที่เขาถูกไล่ไปให้พ้นจากพระพักตร์ซาอูลบุตรคีช (พวกเขาอยู่ในหมู่นักรบซึ่งช่วยดาวิดสู้รบ 2ล้วนเป็นนักธนูและเป็นมือสลิงผู้เชี่ยวชาญทั้งมือซ้ายและมือขวา ต่างก็มาจากเผ่าเบนยามินเช่นเดียวกับซาอูล) ได้แก่

3หัวหน้าอาหิเยเซอร์และโยอาช ทั้งคู่เป็นบุตรของเชมาอาห์แห่งเมืองกิเบอา เยซีเอล และเปเลทบุตรของอัสมาเวท เบราคาห์ เยฮูจากเมืองอานาโธท 4อิชมัยยาห์จากเมืองกิเบโอนผู้เป็นทหารกล้าซึ่งอยู่ในระดับผู้นำของสามสิบยอดนักรบ เยเรมีย์ ยาฮาซีเอล โยฮานัน โยซาบาดจากเมืองเกเดราห์ 5เอลูซัย เยรีโมท เบอัลลิยาห์ เชมาริยาห์ และเชฟาทิยาห์ จากตระกูลฮารูฟ 6เอลคานาห์ อิสชีอาห์ อาซาเรล โยเอเซอร์กับยาโชเบอัมจากตระกูลโคราห์ 7และโยเอลาห์กับเศบาดิยาห์บุตรเยโรฮัมชาวเกโดร์

8นักรบบางคนจากเผ่ากาดก็แปรพรรคมาอยู่กับดาวิดในที่มั่นในถิ่นกันดาร พวกเขาเป็นนักรบกล้าหาญผู้เจนศึกและช่ำชองในการใช้โล่กับหอก เป็นคนหน้าตาดุร้ายเหมือนสิงห์ ไวเหมือนละมั่งบนภูเขา

9เอเซอร์เป็นหัวหน้า

โอบาดีห์เป็นรองหัวหน้า คนที่สามคือเอลีอับ

10คนที่สี่คือมิชมันนาห์ คนที่ห้าคือเยเรมีย์

11คนที่หกคืออัททัย คนที่เจ็ดคือเอลีเอล

12คนที่แปดคือโยฮานัน คนที่เก้าคือเอลซาบาด

13คนที่สิบคือเยเรมีย์ คนที่สิบเอ็ดคือมัคบันนัย

14คนกาดเหล่านี้เป็นนายทัพที่ด้อยที่สุดก็ยังเหมาะกับพลนับร้อย และที่ยิ่งใหญ่ที่สุดก็เหมาะกับพลนับพัน 15พวกเขาข้ามแม่น้ำจอร์แดนไปในเดือนที่หนึ่งซึ่งเป็นฤดูน้ำหลาก และสู้รบกับทุกคนในหุบเขาทั้งด้านตะวันออกและตะวันตก

16มีคนอื่นๆ จากเผ่าเบนยามินและยูดาห์มาหาดาวิดในที่มั่น 17ดาวิดออกไปพบพวกเขาและกล่าวว่า “หากพวกท่านมาหาเราอย่างสันติ มาช่วยเรา เราก็พร้อมที่จะให้ท่านเข้าพวก แต่หากท่านมาเพื่อทรยศมอบเราให้แก่ศัตรูของเรา ทั้งๆ ที่มือของเราไม่ได้ทำร้ายใคร ก็ขอให้พระเจ้าของบรรพบุรุษของเราทอดพระเนตรและตัดสินโทษท่านเถิด”

18แล้วพระวิญญาณเสด็จลงมาเหนืออามาสัยผู้นำของสามสิบยอดนักรบ และเขากล่าวว่า

“ดาวิดเอ๋ย! เราเป็นพวกท่าน

บุตรเจสซีเอ๋ย! เราเป็นฝ่ายท่าน

ความสำเร็จจงเป็นของท่าน

ความสำเร็จจงเป็นของทุกคนที่ช่วยเหลือท่าน

เพราะพระเจ้าของท่านจะทรงช่วยท่าน”

ดาวิดจึงรับพวกเขาไว้และตั้งให้เป็นหัวหน้ากองโจร

19มีบางคนจากเผ่ามนัสเสห์แปรพรรคมาอยู่กับดาวิดเมื่อเขาร่วมทัพฟีลิสเตียจะไปรบกับซาอูล (ดาวิดกับพวกไม่ได้ช่วยชาวฟีลิสเตียรบ เพราะเมื่อขุนพลของฟีลิสเตียปรึกษากันแล้ว พวกเขากล่าวว่า “ถ้าเขาละทิ้งพวกเรา กลับไปเป็นพวกของซาอูลนายเดิม หัวของพวกเราคงหลุดจากบ่า”) 20คนมนัสเสห์ที่มาเป็นพวกกับดาวิดขณะที่เขาไปศิกลากได้แก่ อัดนาห์ โยซาบาด เยดียาเอล มีคาเอล โยซาบาด เอลีฮู และศิลเลธัย ล้วนเป็นหัวหน้ากองพันในมนัสเสห์ 21พวกเขาเป็นนักรบกล้าหาญ เป็นนายทัพช่วยเหลือดาวิดต่อสู้กับกองโจร 22มีคนมาสบทบกับดาวิดมากขึ้นเรื่อยๆ จนกระทั่งดาวิดมีกองทัพยิ่งใหญ่เกรียงไกรเหมือนกองทัพของพระเจ้า12:22 หรือกองทัพยิ่งใหญ่และทรงอานุภาพ

คนอื่นๆ ที่มาสมทบกับดาวิดที่เมืองเฮโบรน

23ต่อไปนี้เป็นจำนวนพลรบที่มาสมทบกับดาวิดที่เมืองเฮโบรน เพื่อจะตั้งดาวิดเป็นกษัตริย์แทนซาอูล ตามที่องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสไว้แล้ว

24มีนักรบจากยูดาห์ 6,800 คน มีโล่และหอกพร้อม

25มีนักรบพร้อมออกศึกจากสิเมโอน 7,100 คน

26จากเลวี 4,600 คน 27รวมเยโฮยาดาซึ่งเป็นหัวหน้าในครอบครัวของอาโรนพร้อมกับคน 3,700 คน 28และศาโดกนักรบหนุ่มผู้กล้าหาญพร้อมด้วยเจ้าหน้าที่ 22 คนจากครอบครัวของเขา

29จากเบนยามินญาติพี่น้องของซาอูลมี 3,000 คน ซึ่งส่วนใหญ่เคยภักดีต่อฝ่ายซาอูลมาก่อน

30มีนักรบกล้าหาญจากเอฟราอิม 20,800 คน ล้วนมีชื่อเสียงในตระกูลของตน

31เผ่ามนัสเสห์ครึ่งเผ่าส่งคนมาตามรายชื่อที่ระบุไว้ 18,000 คน เพื่อตั้งดาวิดเป็นกษัตริย์

32มีหัวหน้าตระกูลจากอิสสาคาร์ 200 คน พร้อมทั้งญาติที่อยู่ใต้บังคับบัญชาของเขาทุกคนที่เข้าใจจังหวะเวลา และรู้ว่าอิสราเอลควรทำอย่างไร

33มีนักรบเจนศึกจากเศบูลุน 50,000 คน พร้อมออกศึกโดยใช้อาวุธทุกชนิดและมีความภักดีต่อดาวิดอย่างแน่วแน่

34มีเจ้าหน้าที่จากนัฟทาลี 1,000 คน และทหาร 37,000 คน ถือโล่และหอก

35จากดานมี 28,600 คน พร้อมออกศึก

36มีทหารเจนศึกจากอาเชอร์ 40,000 คน พร้อมรบ

37ชนเผ่ารูเบน กาด และมนัสเสห์อีกครึ่งเผ่าจากฟากตะวันออกของแม่น้ำจอร์แดน 120,000 คน มีอาวุธทุกชนิด

38ทั้งหมดนี้เป็นนักรบที่สมัครใจออกศึก พวกเขามายังเมืองเฮโบรน ตั้งใจเต็มที่ที่จะเชิญดาวิดขึ้นเป็นกษัตริย์เหนืออิสราเอล ชาวอิสราเอลอื่นๆ ทั้งหมดก็พร้อมใจกันที่จะตั้งดาวิดเป็นกษัตริย์ 39พวกเขากินเลี้ยงร่วมกับดาวิดเป็นเวลาสามวัน เพราะครอบครัวของพวกเขาได้จัดเตรียมเสบียงมาให้ 40ทั้งยังมีประชาชนทั้งใกล้และไกลเช่น อิสสาคาร์ เศบูลุน และนัฟทาลี นำอาหารบรรทุกมาบนลา อูฐ ล่อ และวัว นอกจากนั้นได้นำสิ่งของมากมายมาร่วมงานฉลองนี้ได้แก่ แป้ง มะเดื่ออัด ขนมลูกเกด เหล้าองุ่น น้ำมัน วัว และแกะ เพราะมีความชื่นชมยินดีในอิสราเอล