1 ዜና መዋዕል 12 – NASV & PCB

New Amharic Standard Version

1 ዜና መዋዕል 12:1-40

ከዳዊት ጋር የተቀላቀሉ ተዋጊዎች

1ዳዊት ከቂስ ልጅ ከሳኦል ፊት ሸሽቶ በጺቅላግ ሳለ ወደ እርሱ የመጡት ሰዎች እነዚህ ናቸው፤ እነርሱም በጦርነቱ ላይ ከረዱት ተዋጊዎች መካከል ነበሩ። 2ሰዎቹ ቀስተኞች ሲሆኑ፣ በቀኝም ሆነ በግራ እጃቸው ፍላጻ መወርወርና ድንጋይ መወንጨፍ የሚችሉ ነበሩ፤ እነርሱም ከብንያም ነገድ የሆነው የሳኦል ሥጋ ዘመዶች ነበሩ፤

3አለቃቸው አሒዔዝር ነበረ፤ ከእርሱም በኋላ ኢዮአስ ነበረ፤ ሁለቱም የጊብዓዊው የሸማዓ ልጆች ነበሩ፤

የዓዝሞት ልጆች ይዝኤልና ፋሌጥ፣ በራኪያ፣ ዓናቶታዊው ኢዩ፤

4ገባዖናዊው ሰማያስ ከሠላሳዎቹ መካከል ኀያልና የሠላሳዎቹም መሪ ነበረ፤

ኤርምያስ፣ የሕዚኤል፣ ዮሐናን፣ ገድሮታዊው ዮዛባት፣ 5ኤሉዛይ፣ ለኢያሪሙት፣ በዓልያ፣ ሰማራያ፣ ሐሩፋዊው ሰፋጥያስ፣

6ቆሬያውያኑ ሕልቃና፣ ይሺያ፣ ዓዘርኤል፣ ዮዛር፣ ያሾብዓም፤

7የጌዶር ሰው ከሆነው ደግሞ የይሮሐም ልጆች ዮዔላና ዝባድያ።

8ዳዊት በምድረ በዳ በሚገኘው ምሽጉ ውስጥ ሳለ፣ ከጋድ ነገድ የሆኑ ሰዎች መጥተው የእርሱን ሰራዊት ተቀላቀሉ፤ እነርሱም ለውጊያ የተዘጋጁ ጋሻና ጦር ለመያዝ የሚችሉ ብርቱ ተዋጊዎች ነበሩ፤ ፊታቸው እንደ አንበሳ ፊት የሚያስፈራና በየተራራውም ላይ እንደሚዘልል ሚዳቋ ፈጣኖች ነበሩ።

9የእነዚህም አለቃ ዔጼር ነበረ፤

ሁለተኛው አዛዥ አብድዩ፣ ሦስተኛው ኤልያብ፣

10አራተኛው መስመና፣ አምስተኛው ኤርምያስ፣

11ስድስተኛው ዓታይ፣ ሰባተኛው ኢሊኤል፣

12ስምንተኛው ዮሐናን፣ ዘጠነኛው ኤልዛባድ፣

13ዐሥረኛው ኤርምያስ፣ ዐሥራ አንደኛው መክበናይ።

14እነዚህ ጋዳውያን የጦር አዛዦች ነበሩ፣ ከእነርሱ ታናሽ የሆነው እንደ መቶ፣ ታላቅ የሆነው ደግሞ እንደ ሺሕ አለቃ ይቈጠር ነበር። 15በመጀመሪያው ወር የዮርዳኖስ ወንዝ ከአፍ እስከ ገደፍ ሞልቶ ሳለ፣ ወንዙን ተሻግረው በስተ ምሥራቅና በስተ ምዕራብ ሸለቆዎች ይኖሩ የነበሩትን ሁሉ ከዚያ ያባረሩት እነዚህ ሰዎች ነበሩ።

16ሌሎች ከብንያምና ከይሁዳም ወገን የሆኑ ሰዎች ዳዊት ወደሚገኝበት ምሽግ መጡ። 17ዳዊትም እነዚህን ሰዎች ሊቀበል ወጥቶ እንዲህ አላቸው፤ “የመጣችሁት ልትረዱኝና በሰላም ከሆነ፣ ከእኔ ጋር እንድትሰለፉ ልቀበላችሁ ዝግጁ ነኝ፤ ነገር ግን እጄ ከበደል ንጹሕ ሆኖ ሳለ፣ ለጠላቶቼ አሳልፋችሁ ልትሰጡኝ ከሆነ፣ የአባቶቻችን አምላክ ይመልከተው፤ ይፍረደውም።”

18ከዚያም የእግዚአብሔር መንፈስ በሠላሳዎቹ አለቃ በዓማሣይ ላይ ወረደ፤ እርሱም እንዲህ አለ፤

“ዳዊት ሆይ፤ እኛ የአንተ ነን፤

የእሴይ ልጅ ሆይ፤ እኛ ከአንተ ጋር ነን፤

ሰላም ፍጹም ሰላም ለአንተ ይሁን፤

አንተን ለሚረዱም ሁሉ ሰላም ይሁን፤

አምላክህ ይረዳሃልና።”

ስለዚህ ዳዊት ተቀበላቸው፤ የሰራዊቱም አለቃ አደረጋቸው።

19ዳዊት ከፍልስጥኤማውያን ጋር ተባብሮ ሳኦልን ለመውጋት በሄደ ጊዜ፣ ከምናሴ ነገድ የሆኑ ጥቂት ሰዎች ከድተው ከዳዊት ሰራዊት ጋር ተቀላቀሉ። እርሱ ግን ርዳታ አላደረገላቸውም፤ ምክንያቱም የፍልስጥኤማውያን ገዦች ምክር ካደረጉ በኋላ እንዲህ ሲሉ ልከውት ነበር፤ “ከድቶ ወደ ጌታው ወደ ሳኦል ቢሄድ እኛን ያስጨርሰናል።” 20ዳዊት ወደ ጺቅላግ በሄደ ጊዜ ከድተው ወደ እርሱ የተቀላቀሉ የምናሴ ነገድ ሰዎች እነዚህ ነበሩ፤ ዓድና፣ ዮዛባት፣ ይዲኤል፣ ሚካኤል፣ ዮዛባት፣ ኤሊሁ፣ ጺልታይ፤ እነዚህ በምናሴ ግዛት ሳሉ ሻለቆች ነበሩ። 21ሁሉም ብርቱ ተዋጊዎችና በዳዊትም ሰራዊት ውስጥ አዛዦች ስለ ነበሩ፣ አደጋ ጣዮችን በመውጋት ረዱት። 22ሰራዊቱም እንደ እግዚአብሔር ሰራዊት12፥22 ወይም፣ ታላቅና ኀያል ሰራዊት እስኪሆን ድረስ፣ ዳዊትን ለመርዳት በየዕለቱ ብዙ ሰዎች ይጐርፉ ነበር።

ሌሎችም በኬብሮን የዳዊትን ሰራዊት ተቀላቀሉ

23እግዚአብሔር ለዳዊት በገባለት ቃል ኪዳን መሠረት፣ የሳኦልን መንግሥት አንሥተው ለእርሱ ለመስጠት ዳዊት ወደሚገኝበት ወደ ኬብሮን የመጡት ሰዎች ቍጥር ይህ ነው፤

24ጋሻና ጦር አንግበው ለጦርነት የተዘጋጁት የይሁዳ ሰዎች ስድስት ሺሕ ስምንት መቶ፤

25ከስምዖን ነገድ ለጦርነት ዝግጁ የሆኑ ሰባት ሺሕ አንድ መቶ።

26ከሌዊ ነገድ አራት ሺሕ ስድስት መቶ፤ 27የአሮን ቤተ ሰብ መሪ የሆነውን ዮዳሄን ጨምሮ ሦስት ሺሕ ሰባት መቶ ሰዎች፤ 28ወጣቱ ብርቱ ተዋጊ ጻዶቅና ከቤተ ሰቡ ሃያ ሁለት የጦር አለቆች፤

29የሳኦል ሥጋ ዘመድ የሆኑ የብንያም ሰዎች ሦስት ሺሕ፤ ከእነዚህም አብዛኞቹ እስከዚያች ጊዜ ድረስ ለሳኦል ቤት ታማኝ ነበሩ፤

30ከኤፍሬም ሰዎች በጐሣዎቻቸው ዘንድ ታዋቂ የሆኑ ብርቱ ተዋጊዎች ሃያ ሺሕ ስምንት መቶ፤

31ከምናሴ ነገድ እኩሌታ ዐሥራ ስምንት ሺሕ ሰዎች፤ እነርሱም ዳዊትን ለማንገሥ በየስማቸው ተጽፈው የመጡ ነበሩ።

32ዘመኑን የተረዱና እስራኤላውያንም ምን ማድረግ እንደሚገባቸው የተገነዘቡ የይሳኮር ሰዎች ሁለት መቶ አለቆች፤ በእነርሱም ሥር ሆነው የሚታዘዙ ዘመዶቻቸው።

33ልምድ ያላቸው፣ በሁሉም ዐይነት መሣሪያ ለመዋጋት የተዘጋጁና ዳዊትን ለመርዳት የመጡት መንታ ልብ የሌላቸው የዛብሎን ሰዎች ሃምሳ ሺሕ፤

34ከንፍታሌም ሰዎች አንድ ሺሕ የጦር አለቆች፤ ከእነርሱም ጋር ጋሻና ጦር የያዙ ሠላሳ ሰባት ሺሕ ሰዎች፤

35ከዳን ሰዎች ለጦርነት የተዘጋጁ ሃያ ስምንት ሺሕ ስድስት መቶ፤

36ከአሴር ሰዎች ልምድ ያላቸውና ለጦርነት የተዘጋጁ ወታደሮች አርባ ሺሕ፤

37ከምሥራቅ ዮርዳኖስ ከሮቤል፣ ከጋድና ከምናሴ ነገድ እኩሌታ ልዩ ልዩ ዐይነት መሣሪያ የታጠቁ አንድ መቶ ሃያ ሺሕ ሰዎች።

38እነዚህ ሁሉ በሰራዊቱ ውስጥ ለማገልገል ፈቃደኞች የሆኑ ተዋጊዎች ናቸው።

ወደ ኬብሮን የመጡትም ዳዊትን በእስራኤል ሁሉ ላይ ለማንገሥ ወስነው ስለ ነበር ነው። የቀሩትም እስራኤላውያን ሁሉ ዳዊትን ለማንገሥ በአንድ ሐሳብ ጸኑ። 39የሚያስፈልጋቸውንም ቤተ ሰቦቻቸው አዘጋጅተውላቸው ስለ ነበር፣ ሰዎቹ እየበሉና እየጠጡ ከዳዊት ጋር ሦስት ቀን ቈዩ። 40እንዲሁም ሩቅ ከሆነው ከይሳኮር፣ ከዛብሎንና ከንፍታሌም አገር ሳይቀር ጎረቤቶቻቸው በአህያ፣ በግመል፣ በበቅሎና በበሬ ጭነው ምግብ አመጡላቸው፤ በእስራኤል ታላቅ ደስታ ስለሆነ ዱቄት፣ የበለስና የዘቢብ ጥፍጥፍ፣ የወይን ጠጅ፣ የወይራ ዘይት፣ የቀንድ ከብትና በጎች በገፍ ቀርበው ነበር።

Persian Contemporary Bible

اول تواريخ 12:1-40

پيروان داوود از قبيلهٔ بنيامين

1وقتی داوود از دست شائول پادشاه خود را پنهان كرده بود، عده‌ای از سربازان شجاع اسرائيلی در صقلغ به او ملحق شدند. 2همهٔ اينها در تيراندازی و پرتاب سنگ با فلاخن بسيار مهارت داشتند و می‌توانستند دست چپ خود را مثل دست راستشان به کار ببرند. آنها مانند شائول از قبيلهٔ بنيامين بودند.

3‏-7رئيس آنان اخيعزر پسر شماعه اهل جبعات بود. بقيهٔ افراد عبارت بودند از:

يوآش (برادر اخيعزر)؛ يزی‌ئيل و فالط (پسران عزموت)؛ براكه و ييهو اهل عناتوت؛ يشمعيا اهل جبعون (جنگجوی شجاعی كه در رديف يا برتر از آن سی سردار بود)؛ ارميا، يحزی‌ئيل، يوحانان و يوزاباد اهل جديرات؛ العوزای، يريموت، بعليا، شمريا و شفطيا اهل حروف؛ القانه، يشيا، عزرئيل، يوعزر و يشبعام از طايفه قورح؛ يوعيله و زبديا (پسران يروحام) اهل جدور.

پيروان داوود از قبيلهٔ جاد

8‏-13سربازان شجاع قبيلهٔ جاد نيز نزد داوود به پناهگاه او در بيابان رفتند. ايشان در جنگيدن با نيزه و سپر بسيار ماهر بودند، دل شير داشتند و مثل غزال كوهی چابک و تيزرو بودند. اين است اسامی ايشان به ترتيب رتبه:

عازر، عوبديا، الی‌آب، مشمنه، ارميا، عتای، الی‌ئيل، يوحانان، الزاباد، ارميا و مكبنای.

14اين افراد همه سردار بودند. كم توانترين آنها ارزش صد سرباز معمولی را داشت و پرتوانترين ايشان با هزار سرباز حريف بود! 15آنها در ماه اول سال، آنگاه که رود اردن طغيان می‌كند، از رود گذشتند و ساكنان كناره‌های شرقی و غربی رود را پراكنده ساختند.

پيروان داوود از قبيلهٔ بنيامين و يهودا

16افراد ديگری نيز از قبيله‌های بنيامين و يهودا نزد داوود آمدند. 17داوود به استقبال ايشان رفت و گفت: «اگر به كمک من آمده‌ايد، دست دوستی به هم می‌دهيم ولی اگر آمده‌ايد مرا كه هيچ ظلمی نكرده‌ام به دشمنانم تسليم كنيد، خدای اجدادمان ببيند و حكم كند.»

18سپس روح خدا بر عماسای (كه بعد رهبر آن سی نفر شد) آمد و او جواب داد: «ای داوود، ما در اختيار تو هستيم. ای پسر يسی، ما طرفدار تو می‌باشيم. بركت بر تو و بر تمام يارانت باد، زيرا خدايت با توست.»

پس داوود آنها را پذيرفت و ايشان را فرماندهان سپاه خود كرد.

پيروان داوود از قبيلهٔ منسی

19بعضی از سربازان قبيلهٔ منسی به داوود كه همراه فلسطينی‌ها به جنگ شائول می‌رفت، ملحق شدند. (اما سرداران فلسطينی به داوود و افرادش اجازه ندادند كه همراه آنها بروند. آنها پس از مشورت با يكديگر داوود و افرادش را پس فرستادند، چون می‌ترسيدند ايشان به شائول بپيوندند) 20وقتی داوود به صقلغ می‌رفت، اين افراد از قبيلهٔ منسی به او پيوستند: عدناح، يوزاباد، يديعی‌ئيل، ميكائيل، يوزاباد، اليهو و صلتای. اين افراد سرداران سپاه منسی بودند. 21ايشان جنگاورانی قوی و بی‌باک بودند و داوود را در جنگ با عماليقی‌های مهاجم كمک كردند. 22هر روز عده‌ای به داوود می‌پيوستند تا اينكه سرانجام سپاه بزرگ و نيرومندی تشكيل شد.

سربازانی كه در حبرون به داوود پيوستند

23اين است تعداد افراد مسلحی كه در حبرون به داوود ملحق شدند تا سلطنت شائول را به داوود واگذار كنند، درست همانطور كه خداوند فرموده بود:

24‏-37از قبيلهٔ يهودا ۶,۸۰۰ نفر مجهز به نيزه و سپر؛

از قبيلهٔ شمعون ۷,۱۰۰ مرد زبدهٔ جنگی؛

از قبيلهٔ لاوی ۴,۶۰۰ نفر، شامل يهوياداع، سرپرست خاندان هارون با ۳,۷۰۰ نفر و صادوق كه جنگاوری جوان و بسيار شجاع بود با ۲۲ سردار؛

از قبيلهٔ بنيامين، همان قبيله‌ای كه شائول به آن تعلق داشت، ۳,۰۰۰ مرد كه اكثر آنها تا آن موقع نسبت به شائول وفادار مانده بودند؛

از قبيلهٔ افرايم ۲۰,۸۰۰ مرد جنگی و نيرومند كه همه در طايفهٔ خود معروف بودند؛ از نصف قبيلهٔ منسی ۱۸,۰۰۰ نفر كه انتخاب شده بودند تا بيايند و داوود را برای پادشاه شدن كمک كنند؛

از قبيلهٔ يساكار ۲۰۰ سردار، با افراد زير دست خود (اين سرداران موقعيت جنگی را خوب تشخيص می‌دادند و می‌دانستند چگونه اسرائيلی‌ها را برای جنگ بسيج كنند)؛

از قبيلهٔ زبولون ۵۰,۰۰۰ مرد جنگی كارآزموده و مسلح كه نسبت به داوود وفادار بودند؛

از قبيلهٔ نفتالی ۱,۰۰۰ سردار و ۳۷,۰۰۰ سرباز مجهز به نيزه و سپر؛

از قبيلهٔ دان ۲۸,۶۰۰ سرباز آمادهٔ جنگ؛

از قبيلهٔ اشير ۴۰,۰۰۰ سرباز تعليم ديده و آمادهٔ جنگ؛

از آن سوس رود اردن (محل سكونت قبايل رئوبين و جاد و نصف قبيلهٔ منسی) ۱۲۰,۰۰۰ سرباز مجهز به انواع اسلحه؛

38تمام اين جنگجويان برای يک هدف به حبرون آمدند و آن اينكه داوود را بر تمام اسرائيل پادشاه سازند. در حقيقت، تمام قوم اسرائيل با پادشاه شدن داوود موافق بودند. 39اين افراد جشن گرفتند و سه روز با داوود خوردند و نوشيدند. چون قبلاً خانواده‌هايشان برای ايشان تدارک ديده بودند. 40همچنين مردم اطراف از سرزمين يساكار، زبولون و نفتالی خوراک بر پشت الاغ و شتر و قاطر و گاو گذاشته، آورده بودند. مقدار خيلی زيادی آرد، نان شيرينی، كشمش، شراب، روغن و تعداد بی‌شماری گاو و گوسفند برای اين جشن آورده شد، زيرا در سراسر كشور شادی و سرور بود.