1 ዜና መዋዕል 11 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

1 ዜና መዋዕል 11:1-47

ዳዊት በእስራኤል ላይ ነገሠ

11፥1-3 ተጓ ምብ – 2ሳሙ 5፥1-3

1እስራኤል ሁሉ በኬብሮን ወደ ዳዊት መጥተው እንዲህ አሉት፤ “እነሆ፤ እኛ የገዛ ሥጋህና ደምህ ነን፤ 2በቀደመው ዘመን ሳኦል ንጉሥ ሆኖ ሳለ እስራኤልን ወደ ጦርነት የምትመራ አንተ ነበርህ፤ እግዚአብሔር አምላክህም፣ ‘ሕዝቤን እስራኤልን የምትጠብቅ አንተ ነህ፤ ንጉሣቸውም ትሆናለህ’ ብሎሃል”።

3የእስራኤል ሽማግሌዎች ሁሉ ንጉሥ ዳዊት ወዳለበት ወደ ኬብሮን መጡ፤ ዳዊትም በኬብሮን በእግዚአብሔር ፊት ከእነርሱ ጋር ቃል ኪዳን ገባ። እግዚአብሔር በሳሙኤል አማካይነት በሰጠው ተስፋ መሠረት ዳዊትን ቀብተው በእስራኤል ላይ አነገሡት።

ዳዊት ኢየሩሳሌምን ድል አደረገ

11፥4-9 ተጓ ምብ – 2ሳሙ 5፥6-10

4ዳዊትና እስራኤላውያን ሁሉ ኢያቡስ ወደምትባለው ወደ ኢየሩሳሌም ሄዱ። በዚያም የሚኖሩ ኢያቡሳውያን 5ዳዊትን፣ “ወደዚህ ፈጽሞ አትገባም” አሉት፤ ዳዊት ግን የጽዮንን ምሽግ ያዘ፤ እርሷም የዳዊት ከተማ ናት።

6ዳዊትም፣ “ኢያቡሳውያንን ቀድሞ የሚወጋ ሰው የሰራዊቱ አዛዥ ይሆናል” አለ፤ ስለዚህ የጽሩያ ልጅ ኢዮአብ በመጀመሪያ ወጣ፤ እርሱም አዛዥ ለመሆን በቃ።

7ከዚያም ዳዊት መኖሪያውን በዐምባዪቱ ውስጥ አደረገ፤ ከዚህም የተነሣ የዳዊት ከተማ ተባለች። 8ዳዊትም ከሚሎ ጀምሮ የከተማዪቱን ዙሪያ ቅጥር ሠራ፤ ኢዮአብ ደግሞ የቀረውን የከተማዪቱን ክፍል መልሶ ሠራ። 9እግዚአብሔር ጸባኦት ከእርሱ ጋር ስለ ነበር፣ ዳዊት በየጊዜው እየበረታ ሄደ።

የዳዊት ኀያላን ሰዎች

11፥10-41 ተጓ ምብ – 2ሳሙ 23፥8-39

10የዳዊት ኀያላን ሰዎች አለቆች እነዚህ ናቸው፤ እነርሱም እግዚአብሔር በሰጠው ተስፋ መሠረት መንግሥቱ በምድሪቱ ሁሉ ትሰፋ ዘንድ ከሌሎቹ እስራኤላውያን ጋር ሆነው ለመንግሥቱ ብርቱ ድጋፍ ሰጡ። 11የዳዊት ኀያላን ሰዎች ስም ዝርዝር ይህ ነው፤

ሐክሞናዊው ያሾብዓም የጦር መኮንኖቹ አለቃ11፥11 ሠላሳ ወይም እንደ አንዳንድ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞች፣ ሦስት (እንዲሁም 2ሳሙ 23፥8 ይመ) ይላሉ ነበረ፤ እርሱም ጦሩን አንሥቶ በአንድ ጊዜ ሦስት መቶ ሰው ገደለ።

12ከእርሱም ቀጥሎ ከሦስቱ ኀያላን አንዱ የሆነው የአሆሃዊው የዱዲ ልጅ አልዓዛር ነው፤ 13እርሱም ፍልስጥኤማውያን ለጦርነት በተሰበሰቡ ጊዜ በፈስደሚም ከዳዊት ጋር አብሮ ነበረ፤ ገብስ በሞላበት የዕርሻ ቦታ ወታደሮቹ ከፍልስጥኤማውያን ፊት ሸሹ፤ 14ይሁን እንጂ በዕርሻው መካከል ቦታ ይዘው ስለ ነበረ ፍልስጥኤማውያንን ገደሉ፤ እግዚአብሔርም ታላቅ ድል ሰጣቸው።

15ከፍልስጥኤማውያን ሰራዊት ጥቂቱ በራፋይም ሸለቆ ሰፍሮ ሳለ፣ ከሠላሳዎቹ አለቆች ሦስቱ ዳዊትን ለመገናኘት በዓዶላም ዋሻ አጠገብ ወደሚገኘው ወደ ዐለቱ ወረዱ። 16በዚያን ጊዜ ዳዊት በምሽጉ ውስጥ ነበረ፤ የፍልስጥኤማውያን ሰራዊት ደግሞ በቤተ ልሔም ነበረ። 17ዳዊትም ውሃ ፈልጎ ነበርና፣ “ከቤተ ልሔም በር አቅራቢያ ከሚገኘው ጕድጓድ የምጠጣው ውሃ ማን ባመጣልኝ!” አለ። 18በዚህ ጊዜ ሦስቱ የፍልስጥኤማውያንን ሰራዊት ጥሰው በማለፍ በቤተ ልሔም በር አጠገብ ከሚገኘው ጕድጓድ ውሃ ቀድተው ለዳዊት አመጡለት፤ እርሱ ግን ሊጠጣው ስላልፈለገ በእግዚአብሔር ፊት አፈሰሰው። 19ከዚያም፣ “ይህን ከማድረግ እግዚአብሔር ይጠብቀኝ፤ ይህ በሕይወታቸው ቈርጠው የሄዱትን የእነዚህን ሰዎች ደም እንደ መጠጣት አይደለምን?” አለ። ይህን ለማምጣት በሕይወታቸው ቈርጠው ስለ ነበር፣ ዳዊት ሊጠጣው አልፈለገም።

ሦስቱ ኀያላን ሰዎች የሠሩት ይህን ነበር።

20የኢዮአብ ወንድም አቢሳ የሦስቱ አለቃ ነበረ። እርሱም ጦሩን አንሥቶ ሦስት መቶ ሰዎች ገደለ፤ ከዚህም የተነሣ እንደ ሦስቱ ሁሉ ዝነኛ ሆነ። 21ከሦስቱ አንዱ ሆኖ ባይቈጠርም እንኳ፣ ዕጥፍ ክብር አገኘ፤ አዛዣቸውም ሆነ።

22ከቀብስኤል የመጣውና ታላቅ ጀብዱ የሠራው የዮዳሄ ልጅ በናያስ ብርቱ ተዋጊ ነበረ። እርሱም እጅግ የታወቁ ሁለት የሞአብ ሰዎችን ገደለ። እንዲያውም አንድ ጊዜ በረዶ ምድርን በሸፈነበት ቀን ወደ አንድ ጕድጓድ ወርዶ አንበሳ ገደለ። 23ደግሞም ቁመቱ አምስት ክንድ11፥23 2.3 ሜትር ያህል ነው። የሆነ አንድ ግብፃዊ ገደለ፤ ግብፃዊው የሸማኔ መጠቅለያ የመሰለ ጦር በእጁ ቢይዝም፣ በናያስ ግን ቈመጥ ይዞ ገጠመው፤ ከግብፃዊው እጅ ጦሩን ነጥቆ በገዛ ጦሩ ገደለው። 24የዮዳሄ ልጅ በናያስ የፈጸመው ጀብዱ ይህ ነበር፤ እርሱም እንደ ሦስቱ ኀያላን ዝነኛ ሆነ። 25ከሠላሳዎቹም ይልቅ የበለጠ ክብር ተጐናጸፈ፤ ይሁን እንጂ ከሦስቱ አንዱ አልነበረም፤ ዳዊትም የክብር ዘቡ አዣዥ አደረገው።

26ኀያላኑም እነዚህ ነበሩ፤

የኢዮአብ ወንድም አሣሄል፣

የቤተ ልሔሙ የዱዲ ልጅ ኤልያናን፣

27ሃሮራዊው ሳሞት፣

ፊሎናዊው ሴሌድ፣

28የቴቍሔ ሰው የሆነው የዒስካ ልጅ፣

ዒራስ፣ የዓናቶቱ ሰው አቢዔዜር፣

29ኩሳታዊው ሴቤካይ፣

አሆሃዊው ዔላይ፣

30ነጦፋዊው ማህራይ፣

የነጦፋዊው የበዓና ልጅ ሔሌድ፣

31ከብንያም ወገን የጊብዓ ሰው የሆነው የሪባይ ልጅ ኤታይ፣

ጲርዓቶናዊው በናያስ፣

32የገዓስ ሸለቆዎች ሰው የሆነው ኡሪ፣

ዐረባዊው አቢኤል፣

33ባሕሩማዊው ዓዝሞት፣

ሰዓልቦናዊው ኤሊያሕባ፣

34የጊዞናዊው የአሳን ልጆች፣

የሃራራዊው የሻጌ ልጅ ዮናታን፣

35የሃራራዊው የሳኮር ልጅ አሒአም፣

የኡር ልጅ ኤሊፋል፣

36ምኬራታዊው ኦፌር፣

ፍሎናዊው አኪያ፣

37ቀርሜሎሳዊው ሐጽሮ፣

የኤዝባይ ልጅ ነዕራይ፤

38የናታን ወንድም ኢዮኤል፣

የሃግሪ ልጅ ሚብሐር፣

39አሞናዊው ጼሌቅ፣

የጽሩያ ልጅ የኢዮአብ ጋሻ ጃግሬ ቤሮታዊው ነሃራይ፣

40ይትራዊው ዒራስ፣

ይትራዊው ጋሬብ፣

41ኬጢያዊው ኦርዮ፣

የአሕላይ ልጅ ዛባድ፣

42የሮቤላዊው የሺዛ ልጅ ዓዲና፤ እርሱም የሮቤላውያንና አብረውት ለነበሩት የሠላሳ ሰዎች አለቃ ነበረ።

43የማዕካ ልጅ ሐናን፣

ሚትናዊው ኢዮሣፍጥ፣

44አስታሮታዊው ዖዝያ፣

የአሮዔራዊው የኮታም ልጆች ሻማና ይዒኤል፣

45የሺምሪ ልጅ ይዲኤል፣

ወንድሙም ቴዳዊው ዮሐ፣

46መሐዋዊው ኤሊኤል፣

የኤልነዓም ልጆች ይሪባይና ዮሻውያ፣

ሞዓባዊው ይትማ፣

47ኤሊኤል፣ ዖቤድና ምጾባዊው የዕሢኤል።

Thai New Contemporary Bible

1พงศาวดาร 11:1-47

ดาวิดขึ้นเป็นกษัตริย์

(2ซมอ.5:1-3)

1ชาวอิสราเอลทั้งปวงมาเข้าเฝ้าดาวิดที่เมืองเฮโบรน และทูลว่า “ข้าพระบาททั้งหลายเป็นพี่น้องร่วมสายโลหิตของฝ่าพระบาท 2ตั้งแต่ในรัชกาลของกษัตริย์ซาอูล ฝ่าพระบาทก็ทรงเป็นผู้นำอิสราเอลในการรบ พระยาห์เวห์พระเจ้าของฝ่าพระบาทได้ตรัสกับฝ่าพระบาทไว้ว่า ‘เจ้าจะเป็นผู้เลี้ยงดูและเป็นผู้ปกครองของอิสราเอลประชากรของเรา’ ”

3เมื่อผู้อาวุโสทั้งปวงของอิสราเอลมาเข้าเฝ้ากษัตริย์ดาวิดที่เมืองเฮโบรน พระองค์ทรงทำสัญญากับพวกเขาที่นั่นต่อหน้าองค์พระผู้เป็นเจ้า และพวกเขาเจิมตั้งดาวิดเป็นกษัตริย์ปกครองอิสราเอล เป็นจริงตามที่องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงสัญญาไว้แล้วผ่านทางซามูเอล

ดาวิดพิชิตเยรูซาเล็ม

(2ซมอ.5:6-10)

4ดาวิดและชนอิสราเอลทั้งปวงเดินทัพมายังเยรูซาเล็ม (คือเมืองเยบุส) ชาวเยบุสซึ่งอาศัยอยู่ที่นั่น 5กล่าวกับดาวิดว่า “เจ้าเข้ามาในนี้ไม่ได้หรอก” แต่ดาวิดยึดป้อมของเมืองศิโยน ซึ่งเรียกว่า “เมืองดาวิด” ได้

6ดาวิดบอกไว้ว่า “ผู้ใดที่นำทัพบุกโจมตีเมืองเยบุสจะได้เป็นแม่ทัพ” โยอาบบุตรนางเศรุยาห์บุกไปเป็นคนแรก จึงได้เป็นแม่ทัพของดาวิด

7ดาวิดจึงประทับอยู่ในป้อมปราการนั้น ที่นั่นจึงได้ชื่อว่า “เมืองดาวิด” 8ดาวิดทรงขยายเมืองนั้นออกไปรอบๆ ป้อมปราการ11:8 หรือมิลโลไปจนถึงกำแพงที่ล้อมรอบเมือง ในขณะที่โยอาบซ่อมแซมส่วนอื่นๆ ที่เหลือของเมือง 9และดาวิดทรงยิ่งใหญ่ขึ้นเรื่อยๆ เพราะพระยาห์เวห์ผู้ทรงฤทธิ์สถิตอยู่ด้วย

ยอดนักรบของดาวิด

(2ซมอ.23:8-39)

10ต่อไปนี้คือหัวหน้านักรบของดาวิด ซึ่งร่วมกับชนอิสราเอลทั้งปวงเสริมแสนยานุภาพของดาวิดทั่วราชอาณาจักร ตามที่องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงสัญญาไว้แล้ว 11รายชื่อหัวหน้านักรบของดาวิดคือ

ยาโชเบอัม11:11 อาจจะเป็นอีกรูปหนึ่งของยาโชบบาอัลแห่งตระกูลฮัคโมนี เป็นหัวหน้ากองทหาร11:11 หรือหัวหน้าสามสิบยอดนักรบหรือหัวหน้าสามยอดนักรบ(ดู2ซมอ.23:8)ของดาวิด เขาใช้หอกสังหารข้าศึกถึงสามร้อยคนในคราวเดียวกัน

12คนต่อมาคือเอเลอาซาร์ บุตรโดดัยชาวอาโหอาห์ 13เขาอยู่เคียงข้างดาวิดในสงครามกับฟีลิสเตียที่เมืองปัสดัมมิม กองทัพอิสราเอลที่อยู่ในทุ่งข้าวบาร์เลย์กำลังเริ่มถอยหนี 14แต่ดาวิดกับเขาปักหลักอยู่กลางทุ่ง รับมือและพิชิตชาวฟีลิสเตีย และองค์พระผู้เป็นเจ้าประทานชัยชนะอันยิ่งใหญ่

15ครั้งหนึ่งสามยอดนักรบของสามสิบยอดนักรบมาหาดาวิดที่ศิลาที่ถ้ำอดุลลัม ขณะกองทหารของฟีลิสเตียตั้งค่ายอยู่ในหุบเขาเรฟาอิม 16ครั้งนั้นดาวิดอยู่ในที่มั่น ส่วนแนวรบของฟีลิสเตียอยู่ที่เมืองเบธเลเฮม 17ดาวิดกระหายน้ำและเปรยขึ้นว่า “ถ้ามีใครไปนำน้ำจากบ่อใกล้ประตูเมืองเบธเลเฮมมาให้เราดื่มก็ดี!” 18สามยอดนักรบนี้ก็ตีฝ่าแนวรบของฟีลิสเตียไปตักน้ำจากบ่อนั้นมาให้ แต่ดาวิดไม่ยอมดื่ม กลับรินลงต่อหน้าองค์พระผู้เป็นเจ้า 19และกล่าวว่า “ขอพระเจ้าห้ามไว้ไม่ให้เราดื่มน้ำนี้! ควรหรือที่เราจะดื่มเลือดของคนเหล่านี้ซึ่งเสี่ยงชีวิตไปเอามา?” เนื่องจากพวกเขาเสี่ยงชีวิตไปเอาน้ำมา ดาวิดจึงไม่ยอมดื่ม

นี่คือวีรกรรมของสามยอดนักรบ

20อาบีชัยน้องชายของโยอาบเป็นหัวหน้าของสามยอดนักรบ เขาใช้หอกสังหารข้าศึกถึงสามร้อยคน เขาจึงมีชื่อเสียงเลื่องลือเทียบเท่าสามยอดนักรบ 21เขาเป็นหัวหน้าและมีเกียรติเป็นสองเท่าเหนือสามยอดนักรบ แม้จะไม่ได้เป็นหนึ่งในจำนวนนั้น

22เบไนยาห์บุตรเยโฮยาดาเป็นทหารกล้าจากเมืองขับเซเอลผู้สร้างวีรกรรมหลายครั้ง เขาสังหารยอดฝีมือสองคนของโมอับ ครั้งหนึ่งเขาลงไปในหลุมฆ่าสิงโตในวันที่หิมะตกหนัก 23และเขาได้สังหารคนอียิปต์คนหนึ่งซึ่งสูงถึง 5 ศอก11:23 คือ ประมาณ 2.3 เมตร แม้ว่าคนนั้นถือหอกใหญ่เท่ากับไม้กระพั่นทอผ้า แต่เบไนยาห์ถือไม้พลองเข้าสู้ เขากระชากหอกจากมือของชาวอียิปต์คนนั้นและสังหารด้วยหอก 24นี่คือวีรกรรมของเบไนยาห์บุตรเยโฮยาดา เขาก็มีชื่อเสียงเลื่องลือเทียบเท่าสามยอดนักรบด้วย 25เขามีเกียรติมากกว่าใครๆ ในสามสิบยอดนักรบ แต่ไม่ได้รวมอยู่ในสามยอดนักรบ ดาวิดทรงแต่งตั้งให้เขาดูแลกองทหารรักษาพระองค์

26เหล่านักรบ ได้แก่

อาสาเฮลน้องชายของโยอาบ

เอลฮานันบุตรโดโด คนเบธเลเฮม

27ชัมโมทคนฮาโรด

เฮเลสคนเปโลน

28อิราบุตรอิกเขชคนเทโคอา

อาบีเอเซอร์คนอานาโธท

29สิบเบคัยคนหุชาห์

อิลัยคนอาโหอาห์

30มาหะรัยคนเนโทฟาห์

เฮเลดบุตรบาอานาห์คนเนโทฟาห์

31อิธัยบุตรรีบัยคนกิเบอาห์ในเขตเบนยามิน

เบไนยาห์คนปิราโธน

32หุรัยคนห้วยกาอัช

อาบีเอลคนอารบา

33อัสมาเวทคนบาฮารู

เอลียาห์บาคนชาอัลโบน

34เหล่าบุตรของฮาเชมคนกิโซ

โยนาธานบุตรชากีคนฮาราร์

35อาหิอัมบุตรสาคาร์คนฮาราร์

เอลีฟัลบุตรเออร์

36เฮเฟอร์คนเมเคราห์

อาหิยาห์คนเปโลน

37เฮสโรคนคารเมล

นาอารัยบุตรเอสบัย

38โยเอลน้องชายของนาธัน

มิบฮาร์บุตรฮากรี

39เศเลกคนอัมโมน

นาหะรัยคนเบโรท ผู้เชิญอาวุธประจำตัวของโยอาบบุตรนางเศรุยาห์

40อิราคนอิธรา

กาเรบคนอิธรา

41อุรียาห์คนฮิตไทต์

ศาบาดบุตรอาห์ลัย

42อาดีนาบุตรชิซาคนรูเบน เป็นหัวหน้าของคนรูเบนและคนสามสิบคนที่อยู่กับเขา

43ฮานานบุตรมาอาคาห์ โยชาฟัทคนมิธเน

44อุสซียาคนอัชเทรัท

ชามาและเยอีเอลบุตรโฮธามคนอาโรเออร์

45เยดียาเอลบุตรชิมรีและโยฮาคนทิไซต์ผู้เป็นน้องชาย

46เอลีเอลคนมาหะไวต์

เยรีบัยและโยชาวิยาห์บุตรเอลนาอัม

อิทมาห์คนโมอับ

47เอลีเอล โอเบด และยาอาซีเอลคนเมโซบัย