1 ዜና መዋዕል 11 – NASV & PCB

New Amharic Standard Version

1 ዜና መዋዕል 11:1-47

ዳዊት በእስራኤል ላይ ነገሠ

11፥1-3 ተጓ ምብ – 2ሳሙ 5፥1-3

1እስራኤል ሁሉ በኬብሮን ወደ ዳዊት መጥተው እንዲህ አሉት፤ “እነሆ፤ እኛ የገዛ ሥጋህና ደምህ ነን፤ 2በቀደመው ዘመን ሳኦል ንጉሥ ሆኖ ሳለ እስራኤልን ወደ ጦርነት የምትመራ አንተ ነበርህ፤ እግዚአብሔር አምላክህም፣ ‘ሕዝቤን እስራኤልን የምትጠብቅ አንተ ነህ፤ ንጉሣቸውም ትሆናለህ’ ብሎሃል”።

3የእስራኤል ሽማግሌዎች ሁሉ ንጉሥ ዳዊት ወዳለበት ወደ ኬብሮን መጡ፤ ዳዊትም በኬብሮን በእግዚአብሔር ፊት ከእነርሱ ጋር ቃል ኪዳን ገባ። እግዚአብሔር በሳሙኤል አማካይነት በሰጠው ተስፋ መሠረት ዳዊትን ቀብተው በእስራኤል ላይ አነገሡት።

ዳዊት ኢየሩሳሌምን ድል አደረገ

11፥4-9 ተጓ ምብ – 2ሳሙ 5፥6-10

4ዳዊትና እስራኤላውያን ሁሉ ኢያቡስ ወደምትባለው ወደ ኢየሩሳሌም ሄዱ። በዚያም የሚኖሩ ኢያቡሳውያን 5ዳዊትን፣ “ወደዚህ ፈጽሞ አትገባም” አሉት፤ ዳዊት ግን የጽዮንን ምሽግ ያዘ፤ እርሷም የዳዊት ከተማ ናት።

6ዳዊትም፣ “ኢያቡሳውያንን ቀድሞ የሚወጋ ሰው የሰራዊቱ አዛዥ ይሆናል” አለ፤ ስለዚህ የጽሩያ ልጅ ኢዮአብ በመጀመሪያ ወጣ፤ እርሱም አዛዥ ለመሆን በቃ።

7ከዚያም ዳዊት መኖሪያውን በዐምባዪቱ ውስጥ አደረገ፤ ከዚህም የተነሣ የዳዊት ከተማ ተባለች። 8ዳዊትም ከሚሎ ጀምሮ የከተማዪቱን ዙሪያ ቅጥር ሠራ፤ ኢዮአብ ደግሞ የቀረውን የከተማዪቱን ክፍል መልሶ ሠራ። 9እግዚአብሔር ጸባኦት ከእርሱ ጋር ስለ ነበር፣ ዳዊት በየጊዜው እየበረታ ሄደ።

የዳዊት ኀያላን ሰዎች

11፥10-41 ተጓ ምብ – 2ሳሙ 23፥8-39

10የዳዊት ኀያላን ሰዎች አለቆች እነዚህ ናቸው፤ እነርሱም እግዚአብሔር በሰጠው ተስፋ መሠረት መንግሥቱ በምድሪቱ ሁሉ ትሰፋ ዘንድ ከሌሎቹ እስራኤላውያን ጋር ሆነው ለመንግሥቱ ብርቱ ድጋፍ ሰጡ። 11የዳዊት ኀያላን ሰዎች ስም ዝርዝር ይህ ነው፤

ሐክሞናዊው ያሾብዓም የጦር መኮንኖቹ አለቃ11፥11 ሠላሳ ወይም እንደ አንዳንድ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞች፣ ሦስት (እንዲሁም 2ሳሙ 23፥8 ይመ) ይላሉ ነበረ፤ እርሱም ጦሩን አንሥቶ በአንድ ጊዜ ሦስት መቶ ሰው ገደለ።

12ከእርሱም ቀጥሎ ከሦስቱ ኀያላን አንዱ የሆነው የአሆሃዊው የዱዲ ልጅ አልዓዛር ነው፤ 13እርሱም ፍልስጥኤማውያን ለጦርነት በተሰበሰቡ ጊዜ በፈስደሚም ከዳዊት ጋር አብሮ ነበረ፤ ገብስ በሞላበት የዕርሻ ቦታ ወታደሮቹ ከፍልስጥኤማውያን ፊት ሸሹ፤ 14ይሁን እንጂ በዕርሻው መካከል ቦታ ይዘው ስለ ነበረ ፍልስጥኤማውያንን ገደሉ፤ እግዚአብሔርም ታላቅ ድል ሰጣቸው።

15ከፍልስጥኤማውያን ሰራዊት ጥቂቱ በራፋይም ሸለቆ ሰፍሮ ሳለ፣ ከሠላሳዎቹ አለቆች ሦስቱ ዳዊትን ለመገናኘት በዓዶላም ዋሻ አጠገብ ወደሚገኘው ወደ ዐለቱ ወረዱ። 16በዚያን ጊዜ ዳዊት በምሽጉ ውስጥ ነበረ፤ የፍልስጥኤማውያን ሰራዊት ደግሞ በቤተ ልሔም ነበረ። 17ዳዊትም ውሃ ፈልጎ ነበርና፣ “ከቤተ ልሔም በር አቅራቢያ ከሚገኘው ጕድጓድ የምጠጣው ውሃ ማን ባመጣልኝ!” አለ። 18በዚህ ጊዜ ሦስቱ የፍልስጥኤማውያንን ሰራዊት ጥሰው በማለፍ በቤተ ልሔም በር አጠገብ ከሚገኘው ጕድጓድ ውሃ ቀድተው ለዳዊት አመጡለት፤ እርሱ ግን ሊጠጣው ስላልፈለገ በእግዚአብሔር ፊት አፈሰሰው። 19ከዚያም፣ “ይህን ከማድረግ እግዚአብሔር ይጠብቀኝ፤ ይህ በሕይወታቸው ቈርጠው የሄዱትን የእነዚህን ሰዎች ደም እንደ መጠጣት አይደለምን?” አለ። ይህን ለማምጣት በሕይወታቸው ቈርጠው ስለ ነበር፣ ዳዊት ሊጠጣው አልፈለገም።

ሦስቱ ኀያላን ሰዎች የሠሩት ይህን ነበር።

20የኢዮአብ ወንድም አቢሳ የሦስቱ አለቃ ነበረ። እርሱም ጦሩን አንሥቶ ሦስት መቶ ሰዎች ገደለ፤ ከዚህም የተነሣ እንደ ሦስቱ ሁሉ ዝነኛ ሆነ። 21ከሦስቱ አንዱ ሆኖ ባይቈጠርም እንኳ፣ ዕጥፍ ክብር አገኘ፤ አዛዣቸውም ሆነ።

22ከቀብስኤል የመጣውና ታላቅ ጀብዱ የሠራው የዮዳሄ ልጅ በናያስ ብርቱ ተዋጊ ነበረ። እርሱም እጅግ የታወቁ ሁለት የሞአብ ሰዎችን ገደለ። እንዲያውም አንድ ጊዜ በረዶ ምድርን በሸፈነበት ቀን ወደ አንድ ጕድጓድ ወርዶ አንበሳ ገደለ። 23ደግሞም ቁመቱ አምስት ክንድ11፥23 2.3 ሜትር ያህል ነው። የሆነ አንድ ግብፃዊ ገደለ፤ ግብፃዊው የሸማኔ መጠቅለያ የመሰለ ጦር በእጁ ቢይዝም፣ በናያስ ግን ቈመጥ ይዞ ገጠመው፤ ከግብፃዊው እጅ ጦሩን ነጥቆ በገዛ ጦሩ ገደለው። 24የዮዳሄ ልጅ በናያስ የፈጸመው ጀብዱ ይህ ነበር፤ እርሱም እንደ ሦስቱ ኀያላን ዝነኛ ሆነ። 25ከሠላሳዎቹም ይልቅ የበለጠ ክብር ተጐናጸፈ፤ ይሁን እንጂ ከሦስቱ አንዱ አልነበረም፤ ዳዊትም የክብር ዘቡ አዣዥ አደረገው።

26ኀያላኑም እነዚህ ነበሩ፤

የኢዮአብ ወንድም አሣሄል፣

የቤተ ልሔሙ የዱዲ ልጅ ኤልያናን፣

27ሃሮራዊው ሳሞት፣

ፊሎናዊው ሴሌድ፣

28የቴቍሔ ሰው የሆነው የዒስካ ልጅ፣

ዒራስ፣ የዓናቶቱ ሰው አቢዔዜር፣

29ኩሳታዊው ሴቤካይ፣

አሆሃዊው ዔላይ፣

30ነጦፋዊው ማህራይ፣

የነጦፋዊው የበዓና ልጅ ሔሌድ፣

31ከብንያም ወገን የጊብዓ ሰው የሆነው የሪባይ ልጅ ኤታይ፣

ጲርዓቶናዊው በናያስ፣

32የገዓስ ሸለቆዎች ሰው የሆነው ኡሪ፣

ዐረባዊው አቢኤል፣

33ባሕሩማዊው ዓዝሞት፣

ሰዓልቦናዊው ኤሊያሕባ፣

34የጊዞናዊው የአሳን ልጆች፣

የሃራራዊው የሻጌ ልጅ ዮናታን፣

35የሃራራዊው የሳኮር ልጅ አሒአም፣

የኡር ልጅ ኤሊፋል፣

36ምኬራታዊው ኦፌር፣

ፍሎናዊው አኪያ፣

37ቀርሜሎሳዊው ሐጽሮ፣

የኤዝባይ ልጅ ነዕራይ፤

38የናታን ወንድም ኢዮኤል፣

የሃግሪ ልጅ ሚብሐር፣

39አሞናዊው ጼሌቅ፣

የጽሩያ ልጅ የኢዮአብ ጋሻ ጃግሬ ቤሮታዊው ነሃራይ፣

40ይትራዊው ዒራስ፣

ይትራዊው ጋሬብ፣

41ኬጢያዊው ኦርዮ፣

የአሕላይ ልጅ ዛባድ፣

42የሮቤላዊው የሺዛ ልጅ ዓዲና፤ እርሱም የሮቤላውያንና አብረውት ለነበሩት የሠላሳ ሰዎች አለቃ ነበረ።

43የማዕካ ልጅ ሐናን፣

ሚትናዊው ኢዮሣፍጥ፣

44አስታሮታዊው ዖዝያ፣

የአሮዔራዊው የኮታም ልጆች ሻማና ይዒኤል፣

45የሺምሪ ልጅ ይዲኤል፣

ወንድሙም ቴዳዊው ዮሐ፣

46መሐዋዊው ኤሊኤል፣

የኤልነዓም ልጆች ይሪባይና ዮሻውያ፣

ሞዓባዊው ይትማ፣

47ኤሊኤል፣ ዖቤድና ምጾባዊው የዕሢኤል።

Persian Contemporary Bible

اول تواريخ 11:1-47

داوود پادشاه اسرائيل می‌شود

(دوم سموئيل 5‏:1‏-10)

1رهبران اسرائيل به حبرون نزد داوود رفتند و به او گفتند: «ما گوشت و استخوان تو هستيم؛ 2حتی زمانی كه شائول پادشاه بود، سپاهيان ما را تو به جنگ می‌بردی و به سلامت بر می‌گرداندی؛ و خداوند، خدايت فرموده است كه تو بايد شبان و رهبر قوم او باشی.»

3پس در حبرون داوود در حضور خداوند با رهبران اسرائيل عهد بست و ايشان همانطور كه خداوند به سموئيل فرموده بود، او را به عنوان پادشاه اسرائيل انتخاب كردند. 4سپس داوود و آن رهبران به اورشليم كه محل سكونت يبوسی‌ها بود و يبوس نيز ناميده می‌شد، رفتند. 5ولی اهالی يبوس از ورود آنها به شهر جلوگيری كردند. پس داوود قلعهٔ صهيون را كه بعد به «شهر داوود» معروف شد، تسخير كرد 6و به افراد خود گفت: «اولين كسی كه به يبوسی‌ها حمله كند، فرماندهٔ سپاه خواهد شد.» يوآب پسر صرويه اولين كسی بود كه به يبوسی‌ها حمله كرد؛ پس مقام فرماندهی سپاه داوود به او داده شد. 7داوود در آن قلعه ساكن شد و به همين جهت آن قسمت از شهر اورشليم را شهر داوود ناميدند.

8داوود بخش قديمی شهر را كه اطراف قلعه بود به سمت بيرون وسعت داد و يوآب بقيهٔ شهر اورشليم را تعمير كرد. 9به اين ترتيب روز‌به‌روز بر قدرت و نفوذ داوود افزوده می‌شد، زيرا خداوند، خدای قادر متعال با او بود.

سربازان شجاع داوود

(دوم سموئيل 23‏:8‏-39)

10اين است اسامی سربازان شجاع داوود كه همراه قوم اسرائيل او را مطابق كلام خداوند، پادشاه خود ساختند و سلطنت او را استوار نمودند:

11يشبعام (مردی از اهالی حكمون) فرماندهٔ افسران شجاع داوود پادشاه بود. او يكبار با نيزه خود سيصد نفر را كشت.

12العازار پسر دودو، از خاندان اخوخ در رتبهٔ دوم قرار داشت. 13او در جنگی كه با فلسطينی‌ها در فَسدَميم درگرفت، داوود را همراهی می‌كرد. در محلی كه مزرعهٔ جو بود، سپاه اسرائيل در برابر فلسطينی‌ها تاب نياوردند و پا به فرار گذاشتند، 14ولی العازار و افرادش در آن مزرعهٔ جو در برابر فلسطينی‌ها ايستادگی كردند و آنها را شكست دادند و خداوند پيروزی بزرگی نصيب ايشان نمود.

15در حالی كه عده‌ای از فلسطينی‌ها در درهٔ رفائيم اردو زده بودند، سه نفر از سی سردار شجاع داوود پيش او كه در غار عدولام پنهان شده بود، رفتند. 16داوود در پناهگاه خود بود و اردوی فلسطينی‌ها در بيت‌لحم مستقر شده بود. 17در اين هنگام داوود گفت: «چقدر دلم می‌خواهد از آب چاهی كه نزديک دروازهٔ بيت‌لحم است بنوشم!» 18پس آن سه سردار قلب اردوی فلسطينی‌ها را شكافته، از آن گذشتند و از آن چاه آب كشيدند و برای داوود آوردند. ولی داوود آن آب را ننوشيد، بلكه آن را چون هديه به حضور خداوند ريخت 19و گفت: «نه ای خدا، من اين آب را نمی‌نوشم! اين آب، خون اين سه نفر است كه برای آوردنش جان خود را به خطر انداختند.»

20ابيشای برادر يوآب، فرماندهٔ آن سه نفر بود. او يكبار با كشتن سيصد نفر با نيزهٔ خود، مانند آن سه نفر معروف شد. 21هر چند ابيشای رئيس آن سه دلاور و معروفتر از ايشان بود، ولی جزو آن سه نفر محسوب نمی‌شد.

22بنايا پسر يهوياداع اهل قبصئيل، سرباز معروفی بود و كارهای متهورانه انجام می‌داد. بنايا دو سردار معروف موآبی را كشت. او همچنين در يک روز برفی به حفره‌ای داخل شد و شيری را كشت. 23يكبار با يک چوبدستی يک جنگجوی مصری را كه قدش دو متر و نيم و نيزه‌اش به كلفتی چوب نساجان بود، از پای درآورد. آن مصری نيزه‌ای در دست داشت و بنايا نيزه را از دست او ربود و وی را با آن نيزه كشت. 24اين بود كارهای بنايا كه او را مانند سه سردار ارشد معروف ساخت. 25او از آن سی نفر معروفتر بود ولی جزو سه سردار ارشد محسوب نمی‌شد. داوود او را به فرماندهی گارد سلطنتی گماشت.

26‏-47سربازان معروف ديگر داوود پادشاه اينها بودند:

عسائيل (برادر يوآب)،

الحانان (پسر دودو) اهل بيت‌لحم،

شموت اهل هرور،

حالص اهل فلونی،

عيرا (پسر عقيش) اهل تقوع،

ابيعزر اهل عناتوت،

سبكای11‏:26‏-47 سبکای يا «مبونای».‏ اهل حوشات،

عيلای اهل اخوخ،

مهرای اهل نطوفات،

حالد11‏:26‏-47 حالد يا «حالب».‏ (پسر بعنه) اهل نطوفات،

اتای (پسر ريبای) از جبعهٔ بنيامين،

بنايا اهل فرعاتون،

حورای11‏:26‏-47 ورای يا «حدای».‏ اهل وادیهای جاعش،

ابی‌ئيل اهل عربات،

عزموت اهل بحروم،

اليحبای اهل شعلبون،

پسران هاشم اهل جزون،

يوناتان (پسر شاجای) اهل حرار،

اخيام (پسر ساكار) اهل حرار،

اليفال (پسر اور)،

حافر اهل مكرات،

اخيا اهل فلون،

حصرو اهل كرمل،

نعرای (پسر ازبای)،

يوئيل (برادر ناتان)،

مبحار (پسر هجری)،

صالق اهل عمون،

نحرای اهل بيروت (او سلاحدار سردار يوآب بود)،

عيرا اهل يتر،

جارب اهل يتر،

اوريا اهل حيت،

زاباد (پسر احلای)،

عدينا (پسر شيزا) از قبيلهٔ رئوبين (او جزو سی و يک رهبر قبيلهٔ رئوبين بود.)

حانان (پسر معكه)،

يوشافاط از اهالی متنا،

عزيا اهل عشتروت،

شاماع و يعوئيل (پسران حوتام) اهل عروعير،

يديعی‌ئيل (پسر شمری)،

يوخا (برادر يديعی‌ئيل) از اهالی تيص،

الی‌ئيل اهل محوی،

يريبای و يوشويا (پسران الناعم)،

يتمه اهل موآب،

الی‌ئيل، عوبيد و يعسی‌ئيل اهل مصوبات.