1 ነገሥት 4 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

1 ነገሥት 4:1-34

የሰሎሞን ሹማምት

1ንጉሥ ሰሎሞን በእስራኤል ሁሉ ላይ ነገሠ፤

2ዋና ዋናዎቹ ሹማምቱም እነዚህ ነበሩ፤

የሳዶቅ ልጅ ዓዛርያስ፣ ካህን፤

3የሺሻ ልጆች ኤሊሖሬፍና አኪያ፣ ጸሓፊዎች፤

የአሒሉድ ልጅ ኢዮሣፍጥ፣ ታሪክ ጸሓፊ፤

4የዮዳሄ ልጅ በናያስ፣ የሰራዊቱ ዋና አዛዥ፤

ሳዶቅና አብያታር፣ ካህናት፤

5የናታን ልጅ ዓዛርያስ፣ የአውራጃ ገዦች የበላይ ኀላፊ፤

የናታን ልጅ ዛቡድ፣ ካህንና የንጉሡ የቅርብ አማካሪ፤

6አሒሳር፣ የቤተ መንግሥቱ አዛዥ፤

የዓብዳ ልጅ አዶኒራም የግዳጅ ሥራ ተቈጣጣሪ።

7እንዲሁም ሰሎሞን ለንጉሡና ለንጉሡ ቤት የሚሆነውን ቀለብ ከመላው እስራኤል የሚሰበስቡ ዐሥራ ሁለት የአውራጃ ገዦች ነበሩት፤ እነዚህም እያንዳንዳቸው በዓመት ውስጥ የወር ቀለብ የሚያቀርቡ ነበሩ።

8ስማቸውም እንደሚከተለው ነው፤

ቤንሑር፣ በኰረብታማው በኤፍሬም ምድር፤

9ቤንጼቄር፣ በማቃጽ፣ በሻዓልቢም፣ በቤትሳሜስ፣ በኤሎንቤትሐናን፤

10ቤንሔሴድ፣ በአሩቦት ውስጥ የሚገኙት ሰኰትና የኦፌር አገር በሙሉ የእርሱ ነበር፤

11ቤን አሚናዳብ፤ በናፎት ዶር፣ እርሱም የሰሎሞንን ልጅ ጣፈትን አግብቶ የነበረ ነው፤4፥11 ወይም በናፎት ቁመት ተብሎ ሊተረጐም ይችላል።

12የአሒሉድ ልጅ በዓና፣ በታዕናክና በመጊዶ እንዲሁም ከጻርታን ቀጥሎ ቍልቍል እስከ ኢይዝራኤል ባለው በቤትሳን ሁሉ፣ ከዚያም ዮቅምዓምን ተሻግሮ እስከ አቤልምሖላና ድረስ፣

13ቤንጌበር፣ በገለዓድ ራሞት ከተማ እዚያው ገለዓድ ውስጥ የምናሴ ልጅ የኢያዕር መንደሮች፣ በባሳንም የአርጎብ አውራጃ እንዲሁም በሮቻቸው የናስ መወርወሪያ በሆኑ ስድሳ ባለ ቅጥር ታላላቅ ከተሞች፤

14የዒዶ ልጅ አሒናዳብ፤ በማሃናይም፣

15አኪማአስ በንፍታሌም፣ እርሱም የሰሎሞንን ልጅ ባስማትን አግብቶ የነበረ ነው፤

16የኩሲ ልጅ በዓና፤ በአሴርና በበዓሎት፣

17የፋሩዋ ልጅ ኢዮሣፍጥ በይሳኮር፣

18የኤላ ልጅ ሳሚ በብንያም፣

19የኡሪ ልጅ ጌበር፤ በአሞራውያን ንጉሥ በሴዎን ምድር፣ በባሳን ንጉሥ በዐግ አገር፣ እርሱም የአውራጃው ብቸኛ ገዥ ነበር።

ለሰሎሞን በየቀኑ የሚገባለት ቀለብ

20የይሁዳና የእስራኤል ሕዝቦች ብዛታቸው እንደ ባሕር ዳር አሸዋ ሆነ፤ ይበሉ፣ ይጠጡና ይደሰቱም ነበር። 21ሰሎሞንም ከወንዙ4፥21 በዚህና በ24 ላይ የተጠቀሰው የኤፍራጥስ ወንዝ ነው። አንሥቶ እስከ ፍልስጥኤማውያን ምድር፣ ከዚያም እስከ ግብፅ ዳርቻ ያሉትን መንግሥታት ሁሉ ገዛ፤ እነዚህም አገሮች ግብር አመጡለት፤ በሕይወት ዘመኑም ሁሉ ተገዙለት።

22ለሰሎሞን በየቀኑ የሚገባለትም ቀለብ ይህ ነበር፤ ሠላሳ ኮር4፥22 5500 ኪሎ ግራም ያህል ነው። ማለፊያ ዱቄት፣ ስድሳ ኮር4፥22 11000 ኪሎ ግራም ያህል ነው። መናኛ ዱቄት፣ 23ዐሥር ቅልብ ሰንጋዎች፣ ሃያ ግጦሽ መሬት ላይ የሚውሉ በሬዎች፣ መቶ በግና ፍየል እንዲሁም ዋሊያ፣ ሚዳቋ፣ የበረሓ ፍየልና ምርጥ አዕዋፍ። 24ከወንዙ በስተ ምዕራብ፣ ከቲፍሳ እስከ ጋዛ ያሉትን መንግሥታት ስለ ገዛ፣ በሁሉም አቅጣጫ ሰላም ሆኖለት ነበር። 25በሰሎሞን ዘመን ሁሉ ከዳን አንሥቶ እስከ ቤርሳቤህ ያለው ይሁዳና እስራኤል፣ እያንዳንዱ ሰው ከወይኑና ከበለሱ ጥላ ሥር በሰላም ለመኖር በቃ።

26ሰሎሞን ሠረገላ የሚጐትቱ ፈረሶች የሚያድሩበት አራት ሺሕ ጋጣና ዐሥራ ሁለት ሺሕ ፈረሶች4፥26 ዕብራይስጡና አንዳንድ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞች አርባ ይላሉ። ነበሩት4፥26 ወይም ሠረገለኞች ተብሎ መተርጐም ይችላል።

27የየአውራጃው ሹማምትም በየወር ተራቸው ንጉሡን ሰሎሞንንና ወደ ንጉሡ ማእድ የሚቀርቡትን ሁሉ ምንም ሳያጓድሉ ይቀልቡ ነበር፤ 28እንዲሁም ለሠረገላ ፈረሶችና ለፈጣን ፈረሶች የተመደበውን ገብስና ጭድ ከተፈለገው ቦታ ድረስ ያመጡ ነበር።

የሰሎሞን ጥበብ

29አምላክ ለሰሎሞን ጥበብንና እጅግ ታላቅ ማስተዋልን እንዲሁም በባሕር ዳር እንዳለ አሸዋ የልብ ስፋትን ሰጠው። 30የሰሎሞን ጥበብ ከምሥራቅ ሰዎች ሁሉ ጥበብ በጣም የላቀ ከግብፅም ጥበብ ሁሉ የበለጠ ነበር፤ 31እርሱም ከማንም ሰው ይልቅ ጥበበኛ ነበር፣ ከኢይዝራኤላዊው ከኤታን፣ ከማሖል ልጆች ከሄማንና ከከልቀድ ደግሞም ከደራል ይልቅ ጥበበኛ ነበር፤ ዝናውም በዙሪያው ባሉት አሕዛብ ሁሉ ተሰማ። 32እርሱም ሦስት ሺሕ ምሳሌዎችን ተናገረ፤ የመሓልዩም ቍጥር ሺሕ አምስት ነበር። 33ከሊባኖስ ዝግባ አንሥቶ በቅጥር ግንብ ላይ እስከሚበቅለው ሂሶጵ ስለ ዕፀዋት ተናግሯል፤ እንዲሁም ስለ እንስሳት፣ ስለ ወፎች፣ በሆዳቸው ስለሚሳቡ እንስሳትና ስለ ዓሦችም ተናግሯል፤ 34ጥበቡን ከሰሙት ከዓለም ነገሥታት ሁሉ የተላኩ፣ የየአገሩ ሰዎች ሁሉ የሰሎሞንን ጥበብ ለማድመጥ መጡ።

Thai New Contemporary Bible

1พงศ์กษัตริย์ 4:1-34

ข้าราชการของโซโลมอน

1โซโลมอนทรงปกครองเหนืออิสราเอลทั้งปวง 2ข้าราชการคนสำคัญของโซโลมอน ได้แก่

อาซาริยาห์บุตรศาโดกเป็นปุโรหิต

3เอลีโฮเรฟและอาหิยาห์บุตรชิชาเป็นราชเลขา

เยโฮชาฟัทบุตรอาหิลูดเป็นอาลักษณ์

4เบไนยาห์บุตรเยโฮยาดาเป็นแม่ทัพ

ศาโดกและอาบียาธาร์เป็นปุโรหิต

5อาซาริยาห์บุตรนาธันดูแลข้าหลวงประจำเขต

ศาบุดบุตรนาธันเป็นปุโรหิตและราชมนตรี

6อาหิชาร์เป็นเจ้ากรมวัง

อาโดนีรัมบุตรอับดาเป็นผู้ควบคุมแรงงานโยธา

7และโซโลมอนยังมีข้าหลวงประจำเขตสิบสองนายดูแลทั่วอิสราเอล รับผิดชอบจัดหาเสบียงจากประชากรสำหรับกษัตริย์และข้าราชบริพาร แต่ละคนรับหน้าที่จัดหาเสบียงสำหรับแต่ละเดือนในรอบปี 8ต่อไปนี้เป็นรายชื่อของพวกเขา

เบนเฮอร์ในแดนเทือกเขาแห่งเอฟราอิม

9เบนเดเคอร์ในมาคาส ชาอัลบิม เบธเชเมช และเอโลนเบธฮานัน

10เบนเฮเสดในอารุบโบท (โสโคห์และดินแดนเฮเฟอร์ทั้งหมดเป็นของเขา)

11เบนอาบีนาดับ (ผู้ซึ่งแต่งงานกับทาฟัทราชธิดาของโซโลมอน) ในนาโฟทโดร์4:11 หรือในเขตที่สูงโดร์

12บาอานาบุตรอาหิลูดในทาอานาคและเมกิดโด เบธชานทั้งหมดถัดจากศาเรธานใต้ยิสเรเอล จากเบธชานจดอาเบลเมโหลาห์ไปถึงโยกเมอัม

13เบนเกเบอร์ในราโมทกิเลอาด (ถิ่นฐานของยาอีร์บุตรมนัสเสห์ในกิเลอาด รวมทั้งภูมิภาคอารโกบในบาชาน และเมืองป้อมปราการของบาชานหกสิบเมืองซึ่งมีลูกกรงประตูทองสัมฤทธิ์ล้วนเป็นของเขา)

14อาหินาดับบุตรอิดโดในมาหะนาอิม

15อาหิมาอัส (ซึ่งแต่งงานกับบาเสมัทราชธิดาของโซโลมอน) ในเขตนัฟทาลี

16บาอานาบุตรหุชัยในอาเชอร์ และอาโลท

17เยโฮชาฟัทบุตรปารูอาห์ในอิสสาคาร์

18ชิเมอีบุตรเอลาในเบนยามิน

19เกเบอร์บุตรอุรีในกิเลอาด (ดินแดนของกษัตริย์สิโหนแห่งอาโมไรต์ และดินแดนของกษัตริย์โอกแห่งบาชาน) เขาเป็นข้าหลวงประจำเขตคนเดียวของที่นั่น

เสบียงประจำวันของโซโลมอน

20ประชากรยูดาห์และอิสราเอลมีมากมายดั่งเม็ดทรายที่ชายทะเล พวกเขาล้วนอิ่มหนำสุขสำราญกันทั่วหน้า 21และโซโลมอนทรงครอบครองดินแดนทั้งหมดจากแม่น้ำยูเฟรติสจนถึงดินแดนของชาวฟีลิสเตียจดพรมแดนของอียิปต์ ดินแดนเหล่านี้ต่างนำเครื่องบรรณาการมาถวายและอยู่ใต้อำนาจของโซโลมอนตลอดพระชนม์ชีพ

22เสบียงประจำวันที่โซโลมอนต้องการคือ แป้งละเอียดประมาณ 6.6 กิโลลิตร4:22 ภาษาฮีบรูว่า 30 โคระ แป้งขนมประมาณ 13.2 กิโลลิตร4:22 ภาษาฮีบรูว่า 60 โคระ 23วัวขุน 10 ตัว วัวจากทุ่งหญ้า 20 ตัว แพะแกะรวม 100 ตัว นอกจากนี้ยังมีกวาง เก้ง สมัน และไก่ที่คัดแล้ว 24โซโลมอนทรงครอบครองอาณาจักรทั้งปวงทางทิศตะวันตกของแม่น้ำยูเฟรติส จากทิฟสาห์ไปถึงกาซา และมีความสงบสุขทุกๆ ด้าน 25ตลอดพระชนม์ชีพของโซโลมอน ยูดาห์และอิสราเอลจากดานจดเบเออร์เชบาล้วนดำเนินชีวิตอย่างปลอดภัย แต่ละคนอยู่ใต้เถาองุ่นและต้นมะเดื่อของตน

26โซโลมอนทรงมีคอกสำหรับม้าที่ใช้เทียมรถ 4,000 แห่ง4:26 ภาษาฮีบรูว่า40,000 แห่ง(ดู2พศด.9:25) และม้า 12,000 ตัว4:26 หรือพลรถรบ 12,000 คน

27ในแต่ละเดือนจะกำหนดให้ข้าหลวงเขตส่งเสบียงมาให้โซโลมอนและผู้ร่วมโต๊ะเสวย ไม่ให้มีสิ่งใดขาดตกบกพร่อง 28อีกทั้งยังจัดหาข้าวบาร์เลย์และฟางสำหรับม้าศึกที่ใช้เทียมรถและม้าอื่นๆ ในคอกม้าหลวงด้วย

สติปัญญาของโซโลมอน

29พระเจ้าประทานสติปัญญากับการหยั่งรู้อันลึกซึ้ง และความเข้าใจอันกว้างขวางสุดคะเน ดั่งเม็ดทรายที่ชายทะเลแก่โซโลมอน 30โซโลมอนทรงเฉลียวฉลาดยิ่งกว่าบรรดานักปราชญ์ของทิศตะวันออก และปราชญ์ทั้งปวงของอียิปต์ 31พระองค์ทรงฉลาดกว่าใครๆ รวมทั้งเอธานแห่งวงศ์เอสราห์ เฮมาน คาลโคล์ และดารดา บุตรทั้งหลายของมาโฮล และพระนามของพระองค์เลื่องลือไปทั่วทุกประชาชาติที่อยู่แวดล้อม 32ทรงกล่าว สุภาษิต 3,000 ข้อ และมีบทเพลงพระราชนิพนธ์ 1,005 บท 33ทรงพรรณนาเรื่องพฤกษชาติ ตั้งแต่สนซีดาร์แห่งเลบานอนลงไปถึงต้นหุสบซึ่งงอกออกมาจากกำแพง พระองค์ยังทรงตรัสสอนเกี่ยวกับสัตว์และนก สัตว์เลื้อยคลานและปลา 34กษัตริย์ทุกชาติในโลกได้ยินถึงพระปัญญาของโซโลมอนก็ส่งคนมาฟังพระปัญญาของพระองค์