1 ነገሥት 22 – NASV & CCB

New Amharic Standard Version

1 ነገሥት 22:1-53

ሚክያስ በአክዓብ ላይ ትንቢት ተናገረ

22፥1-28 ተጓ ምብ – 2ዜና 18፥1-27

1በሶርያና በእስራኤል መካከል ለሦስት ዓመት ጦርነት አልነበረም። 2በሦስተኛው ዓመት ግን የይሁዳ ንጉሥ ኢዮሣፍጥ የእስራኤልን ንጉሥ ለመጐብኘት ወረደ። 3የእስራኤልም ንጉሥ ሹማምቱን፣ “በገለዓድ የምትገኘው ሬማት የእኛ ሆና ሳለች፣ ከሶርያው ንጉሥ እጅ ለመመለስ ምንም እንዳላደረግን አታውቁምን?” አላቸው።

4ስለዚህ ኢዮሣፍጥን፣ “በገለዓድ የምትገኘው ሬማት ላይ ለመዝመት አብረኸኝ ለመሄድ ትፈቅዳለህን?” ሲል ጠየቀው።

ኢዮሣፍጥም፣ “እኔ ያው እንደ አንተው ነኝ፤ ሕዝቤ እንደ ሕዝብህ፣ ፈረሶቼም እንደ ፈረሶችህ ናቸው” አለ። 5ኢዮሣፍጥም የእስራኤልን ንጉሥ፣ “በመጀመሪያ ግን የእግዚአብሔርን ሐሳብ ጠይቅ” አለው።

6ስለዚህ የእስራኤል ንጉሥ አራት መቶ ነቢያትን በአንድነት ሰብስቦ፣ “በገለዓድ በምትገኘው ሬማት ላይ ልዝመት ወይስ ልተው?” ሲል ጠየቃቸው።

እነርሱም፣ “እግዚአብሔር በንጉሡ እጅ አሳልፎ ይሰጣታልና ዝመትባት” አሉት።

7ኢዮሣፍጥ ግን፣ “የምንጠይቀው የእግዚአብሔር ነቢይ እዚህ የለምን?” አለ።

8የእስራኤልም ንጉሥ ለኢዮሣፍጥ፣ “መኖሩንማ በእርሱ አማካይነት የእግዚአብሔርን ፈቃድ የምንጠይቀው አንድ ሰው አሁንም አለ፤ ነገር ግን ምንጊዜም ቢሆን ስለ እኔ ክፉ እንጂ አንዳችም መልካም ትንቢት ተናግሮ ስለማያውቅ እጠላዋለሁ፤ ይህም ሰው የይምላ ልጅ ሚክያስ ነው” አለ። ኢዮሣፍጥም፣ “ንጉሡ እንዲህ ማለት አይገባውም” ሲል መለሰ።

9ስለዚህ የእስራኤል ንጉሥ ከሹማምቱ አንዱን ጠርቶ፣ “በል የይምላን ልጅ ሚክያስን በፍጥነት አምጣው” አለው።

10የእስራኤል ንጉሥና የይሁዳ ንጉሥ ኢዮሣፍጥ አልባሰ መንግሥታቸውን ለብሰው፣ በሰማርያ ቅጥር በር አጠገብ ባለው አውድማ ላይ በየዙፋናቸው ተቀምጠው ሳለ፣ ነቢያቱ ሁሉ በፊታቸው ትንቢት ይናገሩ ነበር።

11በዚህ ጊዜ ሴዴቅያስ የተባለው የክንዓና ልጅ የብረት ቀንዶች አበጅቶ፣ “እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘ሶርያውያን እስኪጠፉ ድረስ የምትወጋቸው በእነዚህ ነው’ ” አለው።

12የቀሩትም ነቢያት ሁሉ፣ “እግዚአብሔር በንጉሡ እጅ አሳልፎ ይሰጣታልና በገለዓድ የምትገኘውን ሬማትን ወግተህ ድል አድርግ” በማለት በአንድ ቃል ትንቢት ይናገሩ ነበር።

13ከዚያም ሚክያስን ሊጠራ የሄደው መልእክተኛ፣ “እነሆ፤ ሌሎቹ ነቢያት ንጉሡ ድል እንደሚያደርግ በአንድ ቃል ትንቢት እየተናገሩለት ነውና የአንተም ቃል ከእነርሱ ጋር አንድ እንዲሆን እባክህ መልካም ነገር ተናገር” አለው።

14ሚክያስ ግን፣ “ሕያው እግዚአብሔርን! ለእርሱ የምነግረው እግዚአብሔር የነገረኝን ብቻ ነው” አለ።

15እዚያም እንደ ደረሰ ንጉሡ፣ “ሚክያስ ሆይ፤ በገለዓድ በምትገኘው ሬማት ላይ እንዝመትባት ወይስ እንተው?” ሲል ጠየቀው።

እርሱም፣ “እግዚአብሔር በንጉሡ እጅ አሳልፎ ይሰጣታልና ዘምተህ ድል አድርጋት” ብሎ መለሰለት።

16ንጉሡም፣ “ከእውነት በቀር በእግዚአብሔር ስም አንዳች ነገር እንዳትነግረኝ የማምልህ ስንት ጊዜ ነው?” አለው።

17ከዚያም ሚክያስ እንዲህ ሲል መለሰ፣ “እስራኤል ሁሉ ጠባቂ እንደሌላቸው በጎች በየተራራው ላይ ተበትነው አየሁ፣ እግዚአብሔርም፣ ‘ይህ ሕዝብ ጌታ የለውም፤ እያንዳንዱ በሰላም ወደየቤቱ ይሂድ’ አለ።”

18የእስራኤልም ንጉሥ ለኢዮሣፍጥ፣ “ስለ እኔ ክፉ ብቻ እንጂ ከቶ መልካም ትንቢት አይናገርም አላልሁህምን?” አለው።

19ከዚያም ሚክያስ እንዲህ አለ፤ “እንግዲህ የእግዚአብሔር ቃል የሚለውን ስማ፤ እግዚአብሔር በዙፋኑ ላይ ተቀምጦ፣ የሰማይ ሰራዊት ሁሉ በቀኙና በግራው ቆመው አየሁ፤ 20እግዚአብሔርም፣ ‘በገለዓድ በምትገኘው ሬማት ላይ ዘምቶ እዚያው እንዲሞት፣ አክዓብን ማን ያስተው?’ አለ።

“ታዲያ አንዱ ይህን፣ ሌላውም ያን አለ፤ 21በመጨረሻም፣ አንድ መንፈስ ወጣ፤ ከዚያም በእግዚአብሔር ፊት ቆሞ፣ ‘እኔ አስተዋለሁ’ አለ።

22እግዚአብሔርም፣ ‘እንዴት አድርገህ?’ ሲል ጠየቀው።

“እርሱም፣ ‘እኔ እወጣለሁ፤ በገዛ ነቢያቱም አፍ ሁሉ የሐሰት መንፈስ እሆናለሁ’ አለ።

እግዚአብሔርም፣ ‘በል እንግዲያው ውጣና አስተው፤ ይሳካልሃል’ አለው።

23“ስለዚህ እነሆ እግዚአብሔር በእነዚህ ሁሉ ነቢያትህ አፍ የሐሰት መንፈስ አኖረ፤ በአንተም ላይ መዓቱን እንደሚያመጣብህ ተናገረ።”

24ከዚያም የክንዓና ልጅ ሴዴቅያስ ወጥቶ ሚክያስን በጥፊ መታውና፣ “ለመሆኑ የእግዚአብሔር መንፈስ ከእኔ በየት በኩል ዐልፎ ነው አንተን መጥቶ ያናገረህ?” ሲል ጠየቀው።

25ሚክያስም፤ “ይህንማ ለመደበቅ ወደ አንዲት እልፍኝ በሄድህ ዕለት ታውቀዋለህ” አለው።

26ከዚያም የእስራኤል ንጉሥ እንዲህ ሲል አዘዘ፤ “በሉ ሚክያስን ይዛችሁ ወደ ከተማዪቱ ገዥ ወደ አሞንና ወደ ንጉሡ ልጅ ወደ ኢዮአስ መልሱት፤ 27ከዚያም፣ ‘ንጉሡ፣ በደኅና እስክመለስ ድረስ፣ ይህን ሰው በእስር ቤት አቈዩት፤ ከደረቅ እንጀራና ከውሃ በስተቀር ሌላ እንዳትሰጡት’ ብሏል በሉት” አለ።

28ሚክያስም፣ “አንተ በደኅና ከተመለስህ እግዚአብሔር በእኔ አልተናገረማ!” አለ፤ ከዚያም በመቀጠል፣ “በዚህ ያለኸው ሕዝብ ሁሉ ይህን ቃሌን ልብ ብለህ ያዘው፤” አለ።

አክዓብ በገለዓድ በምትገኘው በሬማት ተገደለ

22፥29-36 ተጓ ምብ – 2ዜና 18፥28-34

29ስለዚህ የእስራኤል ንጉሥና የይሁዳ ንጉሥ ኢዮሣፍጥ በገለዓድ ወደምትገኘው ሬማት ወጡ። 30የእስራኤል ንጉሥ ኢዮሣፍጥን፣ “እንዳልታወቅ እኔ ልብስ ለውጬና ሌላ ሰው መስዬ እገባለሁ፤ አንተ ግን ልብሰ መንግሥትህን ልበስ” አለው። ስለዚህ የእስራኤል ንጉሥ ራሱን ደብቆ ወደ ጦርነቱ ገባ።

31በዚህ ጊዜ የሶርያ ንጉሥ ሠላሳ ሁለቱን የሠረገላ አዛዦች፣ “ከራሱ ከእስራኤል ንጉሥ በቀር ትንሽም ይሁን ትልቅ ከማንም ጋር እንዳትገጥሙ” ሲል አዝዟቸው ነበር፤ 32የሠረገላ አዛዦቹ ኢዮሣፍጥን ሲያዩት፣ “ያለ ጥርጥር ይህ የእስራኤል ንጉሥ ነው” አሉ፤ ስለዚህ አደጋ ሊጥሉበት ከበቡት፤ ኢዮሣፍጥ ሲጮህ ግን 33የሠረገላ አዛዦቹ እርሱ የእስራኤል ንጉሥ አለመሆኑን ዐውቀው መከታተሉን ተዉት።

34ነገር ግን አንዱ ቀስቱን ሳያልም እንዲሁ ሲያስፈነጥር በጦር ልብሱ መጋጠሚያ ላይ የእስራኤልን ንጉሥ ወጋው፤ ንጉሡም ሠረገላ ነጂውን፣ “ቈስያለሁና ወደ ኋላ አዙረህ ከጦሩ ሜዳ አውጣኝ” አለው። 35ጦርነቱም ቀኑን ሙሉ ተፋፍሞ ዋለ፤ በዚህ ጊዜም ንጉሡ በሶርያውያን ፊት ለፊት ሠረገላው ላይ ቀና ብሎ እንደ ተደገፈ ነበር፤ የቍስሉ ደም በሠረገላው ወለል ላይ ይወርድ ነበር፤ በዚያኑ ዕለት ማታም ንጉሡ ሞተ። 36ፀሓይ ስትጠልቅም በሰራዊቱ መካከል፣ “እያንዳንዱ ሰው ወደ ቤቱ፣ እያንዳንዱም ወደ ሀገሩ ይሂድ!” የሚል ጩኸት አስተጋባ።

37ንጉሡ ስለ ሞተም ወደ ሰማርያ አምጥተውት እዚያው ተቀበረ። 38ሠረገላውንም አመንዝሮች በታጠቡበት በሰማርያ22፥38 ወይም፣ የጦር መሣሪያ በሚታጠብበት በሰማርያ ተብሎ መተርጐም ይችላል ኵሬ ዐጠቡት፤ እግዚአብሔርም እንደ ተናገረው ቃል ደሙን ውሾች ላሱት።

39ሌላው በአክዓብ ዘመነ መንግሥት የተፈጸመውና ያደረገው ሁሉ፣ ቤተ መንግሥቱን መሥራቱና በዝኆን ጥርስ መለበጡ እንዲሁም የሠራቸው የምሽግ ከተሞች በእስራኤል ነገሥታት ታሪክ የተጻፈ አይደለምን? 40አክዓብም ከአባቶቹ ጋር አንቀላፋ፤ ልጁ አካዝያስም በእግሩ ተተክቶ ነገሠ።

የይሁዳ ንጉሥ ኢዮሣፍጥ

22፥41-50 ተጓ ምብ – 2ዜና 20፥31–21፥1

41የእስራኤል ንጉሥ አክዓብ በነገሠ በአራተኛው ዓመት የአሳ ልጅ ኢዮሣፍጥ በይሁዳ ነገሠ። 42ኢዮሣፍጥ ሲነግሥ ዕድሜው ሠላሳ አምስት ዓመት ነበር፤ እርሱም በኢየሩሳሌም ሃያ አምስት ዓመት ገዛ። እናቱ ዓዙባ ትባላለች፤ እርሷም የሺልሒ ልጅ ነበረች። 43በአካሄዱም ሁሉ የአባቱን የአሳን መንገድ ተከተለ፤ ከዚያች ፈቀቅ አላለም፤ በእግዚአብሔርም ፊት መልካም የሆነውን አደረገ፤ ይሁን እንጂ በየኰረብታው ላይ ያሉትን የማምለኪያ ቦታዎች አላጠፋም፤ ሕዝቡም በዚያ መሥዋዕት ይሠዋ፣ ዕጣንም ያጥን ነበር። 44እንዲሁም ኢዮሣፍጥ ከእስራኤል ንጉሥ ጋር በሰላም ኖረ።

45ሌላውም ኢዮሣፍጥ በዘመነ መንግሥቱ የፈጸመው፣ ያከናወነውና ያደረገው ጦርነት ሁሉ በይሁዳ ነገሥታት ታሪክ የተጻፈ አይደለምን? 46ከአባቱ ከአሳ ዘመን በኋላ እንኳ ተርፈው በጣዖት ማምለኪያ ቦታዎች የነበሩትን የወንደቃ ቅሬታዎች ከምድሪቱ አስወገደ። 47በዚያን ጊዜ ኤዶም ንጉሥ አልነበራትም፤ የሚገዛት እንደራሴ ነበር።

48ኢዮሣፍጥ ወርቅ ለማምጣት ወደ ኦፊር የሚሄዱ የንግድ መርከቦች22፥48 ዕብራይስጡ የተርሴስ መርከቦች ይላል አሠርቶ ነበር፤ ይሁን እንጂ በዔጽዮንጋብር ስለ ተሰበሩ ከቶ ወደዚያ መሄድ አልቻሉም ነበር። 49በዚያን ጊዜም የአክዓብ ልጅ አካዝያስ ኢዮሣፍጥን “ሰዎቼ ከሰዎችህ ጋር በመርከብ ይሂዱ” ሲል ጠይቆት ነበር፤ ኢዮሣፍጥ ግን እሺ አላለውም።

50ኢዮሣፍጥ ከአባቶቹ ጋር አንቀላፋ፤ እነርሱ በተቀበሩበት በአባቱ በዳዊት ከተማ ተቀበረ። ልጁ ኢዮራምም በእግሩ ተተክቶ ነገሠ።

የእስራኤል ንጉሥ አካዝያስ

51የይሁዳ ንጉሥ ኢዮሣፍጥ በነገሠ በዐሥራ ሰባተኛው ዓመት የአክዓብ ልጅ አካዝያስ የእስራኤል ንጉሥ ሆኖ በሰማርያ ነገሠ፤ እስራኤልንም ሁለት ዓመት ገዛ። 52እርሱም የአባቱንና የእናቱን፣ እንዲሁም እስራኤልን ያሳተውን የናባጥን ልጅ የኢዮርብዓምን መንገድ በመከተሉ፣ በእግዚአብሔር ፊት የተጠላ ክፉ ሥራ ሠራ። 53አባቱ እንዳደረገው ሁሉ፣ እርሱም በኣልን አመለከ፤ ሰገደለትም። በዚህም የእስራኤልን አምላክ እግዚአብሔርን ለቍጣ እንዲነሣሣ አደረገ።

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

列王纪上 22:1-53

米该雅先知警告亚哈王

1亚兰以色列之间三年无战事。 2第三年,犹大约沙法来见以色列亚哈3以色列王对臣仆说:“你们都知道基列拉末是我们的领土,我们岂能坐视不理,不从亚兰王手中夺回来呢?” 4他问约沙法:“你愿意跟我一起去攻打基列拉末吗?”约沙法回答说:“你我不分彼此,我的民就是你的民,我的马就是你的马。” 5约沙法又对以色列王说:“你要先求问耶和华。”

6于是,以色列王就召来了大约四百名先知,问他们:“我可以去攻打基列拉末吗?”他们说:“可以去,主必把那城交在王手中。” 7约沙法问:“这里没有耶和华的先知供我们求问吗?” 8以色列王回答说:“这里还有一个人,是音拉的儿子米该雅,我们可以托他求问耶和华。可是我厌恶他,因为他给我的预言都是有凶无吉。”约沙法说:“王不要这样说。” 9以色列王召来一名内侍,说:“你快把音拉的儿子米该雅带来。” 10以色列王和犹大约沙法撒玛利亚城门前的麦场,身穿朝服,坐在宝座上,众先知都在他们面前说预言。 11基拿拿的儿子西底迦造了两只铁角,说:“耶和华这样说,‘你必用这铁角抵亚兰人,直到毁灭他们。’” 12所有的先知也都预言说:“去攻打基列拉末吧,一定得胜,耶和华必将那城交在王的手中。”

13去召米该雅的使者对米该雅说:“众先知都异口同声地向王说吉言,你就像他们一样说些吉言吧。” 14米该雅回答说:“我凭永活的耶和华起誓,耶和华对我说什么,我就说什么。” 15米该雅来到以色列王面前,王就问他:“米该雅啊,我可不可以去攻打基列拉末?”米该雅回答说:“上去攻打吧,一定得胜,耶和华必将那城交在王手中。” 16王却说:“我要嘱咐你多少次,你才肯奉耶和华的名对我说实话呢?” 17米该雅说:“我看见以色列人四散在山上,好像没有牧人的羊群一样。耶和华说,‘这些人没有主人,让他们各自平安地回家去吧。’” 18以色列王对约沙法说:“我不是告诉过你吗?他给我的预言都是有凶无吉。” 19米该雅说:“你要听耶和华的话。我看见耶和华坐在宝座上,众天军侍立在祂左右。 20耶和华说,‘谁愿意去引诱亚哈基列拉末去送死呢?’众天军议论纷纷。 21后来,有一个灵站出来对耶和华说他愿意去。 22耶和华问他用什么方法,他说,‘我要做谎言之灵,进入他众先知的口中。’耶和华说,‘你必能成功,就这样做吧。’ 23现在,耶和华已经把谎言之灵放进这些先知口中,耶和华已决意降祸给你。”

24基拿拿的儿子西底迦听了米该雅的话就上前打他的脸,说:“耶和华的灵怎会离开我向你说话呢?” 25米该雅说:“你躲进密室的那天就知道了。” 26以色列王下令说:“把米该雅交给亚们总督和约阿施王子, 27告诉他们,‘王说,要把这人关在监牢,只给他一些饼和水,直到我平安地回来。’” 28米该雅说:“如果你能够平安地回来,耶和华就没有借着我说话。”他又说:“众民啊,你们都记住我的话。”

亚哈之死

29以色列王和犹大约沙法出兵攻打基列拉末30以色列王对约沙法说:“我要改装上阵,你就穿王袍吧。”以色列王就改装上阵。 31亚兰王已经吩咐他的三十二名战车长不要跟对方的大小军兵交锋,只攻击以色列王。 32战车长看见约沙法,以为他一定是以色列王,便转过来攻击他。约沙法高声喊叫, 33战车长见他不是以色列王,便不再追杀他。 34有人随手放了一箭,射进了以色列王的铠甲缝中。王对驾车的说:“调转车头拉我离开战场吧,我受了重伤。” 35那天的战事非常激烈,亚哈王被人扶着站在车上,迎战亚兰人。到了黄昏,王就死了,车上流满了血。 36太阳快要下山的时候,以色列军中传出号令,叫人各回本乡本城。

37王死后,他们把王的尸体运回撒玛利亚安葬, 38并在撒玛利亚妓女洗浴的池边洗他的战车,有狗来舔他的血,正如耶和华所言。 39亚哈其他的事,他的一切所作所为和他建造的象牙宫及各城邑,都记在以色列的列王史上。 40亚哈与祖先同眠后,他儿子亚哈谢继位。

约沙法做犹大王

41亚哈以色列王第四年,亚撒的儿子约沙法登基做犹大王。 42约沙法三十五岁登基,在耶路撒冷执政二十五年。他母亲叫阿苏巴,是示利希的女儿。 43约沙法事事效法他父亲亚撒,不偏不离,做耶和华视为正的事。但他没有拆毁丘坛,百姓仍然在那里献祭烧香。 44约沙法以色列王修好。

45约沙法其他的事,包括他的功业和战绩,都记在犹大的列王史上。 46约沙法除掉了他父亲亚撒时代遗留的男庙妓。 47那时以东没有王,由总督治理。 48约沙法又建造了一批他施船,要到俄斐去运载黄金,可是没有成行,因为船只在以旬·迦别失事了。 49后来,亚哈的儿子亚哈谢请求约沙法让他的人跟约沙法的人一起出海,但约沙法拒绝了。 50约沙法与祖先同眠后葬在大卫城他的祖坟里。他儿子约兰继位。

亚哈谢做以色列王

51犹大约沙法执政第十七年,亚哈的儿子亚哈谢撒玛利亚登基做以色列王,执政两年。 52他做耶和华视为恶的事,步他父母的后尘,效法使以色列人陷入罪中的尼八之子耶罗波安53他像他父亲一样供奉、祭拜巴力,惹以色列的上帝耶和华发怒。