1 ነገሥት 12 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

1 ነገሥት 12:1-33

እስራኤል በሮብዓም ላይ ዐመፀ

12፥1-24 ተጓ ምብ – 2ዜና 10፥1–11፥4

1እስራኤላውያን ሁሉ ሊያነግሡት ወደ ሴኬም ስለ ሄዱ፣ ሮብዓም ወደዚያው ሄደ።12፥1 ወይም በግብፅ ቀረ ተብሎ መተርጐም ይችላል። 2የናባጥ ልጅ ኢዮርብዓም ይህን በሰማ ጊዜ፣ ከንጉሥ ሰሎሞን ሸሽቶ ከሚኖርበት ከግብፅ ተመልሶ መጣ። 3ስለዚህም ወደ ኢዮርብዓም ላኩበት፤ እርሱና መላው የእስራኤል ጉባኤም ወደ ሮብዓም መጥተው፣ 4“አባትህ ከባድ ቀንበር ጫነብን፤ አንተ ግን አሁን የአባትህን የጭካኔ አገዛዝ የጫነብንንም ከባድ ቀንበር ብታቀልልን እንገዛልሃለን” አሉት።

5ሮብዓምም፣ “እንግዲያውስ ሂዱ፤ ከሦስት ቀን በኋላ ተመልሳችሁ ወደ እኔ ኑ” አላቸው። ስለዚህ ሕዝቡ ሄዱ።

6ከዚያም ሮብዓም አባቱ ሰሎሞን በሕይወቱ ሳለ ካገለገሉት ሽማግሌዎች ጋር ተማከረ፤ “ለዚህ ሕዝብ ምን መልስ እንድሰጥ ትመክሩኛላችሁ?” አላቸው።

7እነርሱም፣ “ዛሬ አንተ ለዚህ ሕዝብ አገልጋይ ብትሆን፣ ብትገዛለትና ደስ የሚያሰኝ መልስ ብትሰጠው፣ ምንጊዜም የአንተ አገልጋይ ይሆናል” ብለው መለሱለት።

8ሮብዓም ግን ሽማግሌዎቹ የሰጡትን ምክር ንቆ፣ አብሮ አደግ የሆኑትንና እርሱን የሚያገለግሉትን ወጣቶች፣ 9“ሐሳብ ለማግኘት፣ የእናንተስ ምክር ምንድን ነው? ‘አባትህ የጫነብንን ቀንበር አቅልልልን’ ለሚሉኝ ለእነዚህ ሰዎች ምን መልስ እንስጥ?” ሲል ጠየቃቸው።

10ወጣት አብሮ አደጎቹም፣ እንዲህ አሉት፣ “ ‘አባትህ ከባድ ቀንበር ጫነብን፣ አንተ ግን ቀንበራችንን አቅልልልን’ ላሉህ ለእነዚህ ሰዎች፣ ‘ትንሿ ጣቴ ከአባቴ ወገብ ይልቅ ትወፍራለች፤ 11አባቴ ከባድ ቀንበር ጫነባችሁ፤ እኔ ግን ከዚያ ይብስ አከብደዋለሁ፤ አባቴ በዐለንጋ ገረፋችሁ፤ እኔ ግን በጊንጥ እገርፋችኋለሁ’ በላቸው!” አሉ።

12ንጉሡ፣ “በሦስተኛው ቀን ተመልሳችሁ ኑ” ብሏቸው ስለ ነበር፣ ኢዮርብዓምና ሕዝቡ ሁሉ በሦስተኛው ቀን ወደ ሮብዓም ተመልሰው መጡ። 13ንጉሡም በሽማግሌዎቹ የተሰጠውን ምክር ትቶ፣ ሕዝቡን የሚያስከፋ መልስ ሰጣቸው፤ 14ወጣቶቹ የሰጡትን ምክርም ተቀብሎ፣ “አባቴ ቀንበራችሁን አከበደባችሁ፤ እኔ ደግሞ ከዚያ ይብስ አከብደዋለሁ፤ አባቴ በዐለንጋ ገረፋችሁ፣ እኔ ደግሞ በጊንጥ እገርፋችኋለሁ” አላቸው። 15እግዚአብሔር በሴሎናዊው በአኪያ አማካይነት ስለ ናባጥ ልጅ ስለ ኢዮርብዓም የተናገረው ቀድሞውኑ እግዚአብሔር የወሰነው ስለሆነ፣ መፈጸም ነበረበትና ንጉሡ ሕዝቡን አልሰማም።

16እስራኤልም ሁሉ ንጉሡ ሊሰማቸው አለመፈለጉን በተረዱ ጊዜ፣ ለንጉሡ እንዲህ በማለት መለሱ፤

“ከዳዊት ምን ድርሻ አለን?

ከእሴይስ ልጅ ምን የምናገኘው አለ?

እስራኤል ሆይ፤ ወደየድንኳንህ ተመለስ፤

ዳዊት ሆይ፤ እንግዲህ የገዛ ቤትህን ጠብቅ!”

ስለዚህም እስራኤላውያን ወደ ድንኳኖቻቸው ተመለሱ። 17ሮብዓምም በይሁዳ ምድር በሚኖሩት እስራኤላውያን ላይ ገዥ ሆነ።

18ንጉሥ ሮብዓም የጕልበት ሠራተኞች አለቃ የነበረውን አዶኒራምን12፥18 አንዳንድ የሰብዓ ሊቃናት ቅጆችና የሱርስት ትርጕሞች ከዚህ ጋር ይስማማሉ (1ነገ 4፥6 5፥14 ይመ) ዕብራይስጡ፣ አዶራም ይላል። ላከው፤ ነገር ግን እስራኤል ሁሉ በድንጋይ ወግረው ገደሉት። ንጉሡ ሮብዓም ግን እንደ ምንም ብሎ ሠረገላው ላይ በመውጣት ወደ ኢየሩሳሌም ሸሸ። 19ስለዚህ ሕዝቡ በዳዊት ቤት ላይ እስከ ዛሬ ድረስ እንዳመፀ ነው።

20ኢዮርብዓም መመለሱን እስራኤላውያን ሁሉ በሰሙ ጊዜ፣ ወደ ጉባኤያቸው በማስጠራት በመላው እስራኤል ላይ አነገሡት። ለዳዊት ቤት በታማኝነት ጸንቶ የተገኘው የይሁዳ ቤት ብቻ ነው።

21ሮብዓም ኢየሩሳሌም በደረሰ ጊዜ፣ የእስራኤልን ቤት ወግተው መንግሥቱን ለሰሎሞን ልጅ ለሮብዓም እንዲመልሱ መላውን የይሁዳ ቤትና የብንያምን ነገድ ሰበሰበ፤ የሰራዊቱም ቍጥር አንድ መቶ ሰማንያ ሺሕ ነበር።

22ነገር ግን ይህ የአምላክ ቃል፣ የእግዚአብሔር ሰው ወደ ሆነው ወደ ሳማያ መጣ፤ 23“ለይሁዳ ንጉሥ ለሰሎሞን ልጅ ለሮብዓም፣ ለመላው የይሁዳ ቤትና ለብንያም ነገድ፣ ለቀረውም ሕዝብ ሁሉ እንዲህ በል፤ 24እግዚአብሔር የሚለው ይህ ነው፤ ይህ ነገር ከእኔ የሆነ ነውና ወንድሞቻችሁን እስራኤላውያንን ለመውጋት አትውጡ፤ እያንዳንዳችሁ ወደየቤታችሁ ተመለሱ።’ ” ስለዚህ እግዚአብሔር እንዳዘዘው የእግዚአብሔርን ቃል ሰሙ፤ ወደየቤታቸውም ተመለሱ።

በቤቴልና በዳን የቆሙ የወርቅ ጥጆች

25ከዚያም ኢዮርብዓም በኰረብታው አገር በኤፍሬም የምትገኘውን ሴኬምን ምሽግ አድርጎ ሠራ፤ በዚያም ተቀመጠ። ደግሞም ያንን ትቶ በመውጣት የጵኒኤልን ምሽግ ሠራ።12፥25 ዕብራይስጡ ጰኑኤል ይለዋል

26ኢዮርብዓም በልቡ እንዲህ ሲል ዐሰበ፤ “መንግሥቱ ለዳዊት ቤት የሚመለስ ይመስላል፤ 27ይህ ሕዝብ መሥዋዕት ለማቅረብ ኢየሩሳሌም ወዳለው ወደ እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ የሚወጣ ከሆነ፣ እንደ ገና ልቡን ወደ ጌታው ወደ ይሁዳ ንጉሥ ወደ ሮብዓም ሊያዞር ነው። ከዚያም እኔን ይገድለኛል፤ ወደ ንጉሡም ወደ ሮብዓም ይመለሳል።”

28ንጉሡ ከመከረበት በኋላ ሁለት የወርቅ ጥጆች አሠርቶ ሕዝቡን፣ “እስራኤል ሆይ፤ ወደ ኢየሩሳሌም እስካሁን የወጣኸው ይበቃል፤ ከግብፅ ምድር ያወጡህ አማልክትህ እነዚህ ናቸው” አለ። 29አንዱን በቤቴል ሌላውንም በዳን አቆመው። 30ይህም አድራጎት ኀጢአት ሆነ፤ ሕዝቡም በዚያ ላለው ለመስገድ እስከ ዳን ድረስ ርቆ ሄደ። 31ኢዮርብዓም በማምለኪያ ኰረብቶች ላይ አብያተ ጣዖታትን ሠራ፤ ከሕዝቡ የተለያዩ ክፍሎች ሁሉ፣ ሌዋውያን ካልሆኑት ካህናትን ሾመ። 32በይሁዳ እንደሚደረገው ሁሉ እርሱም በስምንተኛው ወር ዐሥራ አምስተኛው ቀን በዓል እንዲሆን ወሰነ፤ በመሠዊያውም ላይ መሥዋዕት አቀረበ። ለሠራቸው ጥጆች መሥዋዕት በማቅረብም እንዲህ ያለውን ድርጊት በቤቴል ፈጸመ። በማምለኪያ ኰረብቶች ላይ ላሠራቸው አብያተ ጣዖታት በቤቴል ካህናቱን መደበ። 33ራሱ በመረጠው በስምንተኛው ወር፣ በዐሥራ አምስተኛው ቀን በቤቴል ባቆመው መሠዊያ ላይ መሥዋዕት አቀረበ፤ ስለዚህ ለእስራኤላውያን በዓል ወሰነላቸው፤ ዕጣንም ለማቅረብ ወደ መሠዊያው ወጣ።

Thai New Contemporary Bible

1พงศ์กษัตริย์ 12:1-33

อิสราเอลกบฏต่อเรโหโบอัม

(2พศด.10:1—11:4)

1เรโหโบอัมเสด็จไปที่เชเคม เพราะชาวอิสราเอลทั้งปวงพากันไปที่นั่นเพื่อตั้งเรโหโบอัมขึ้นเป็นกษัตริย์ 2เมื่อเยโรโบอัมบุตรเนบัท (ซึ่งหนีกษัตริย์โซโลมอนไปอยู่ในอียิปต์) ทราบข่าว จึงกลับมาจากอียิปต์12:2 หรือทราบข่าวก็ยังคงอยู่ในอียิปต์ 3พวกเขาก็ส่งคนไปตามเยโรโบอัมมา แล้วเขากับชุมนุมประชากรอิสราเอลทั้งปวงก็เข้าเฝ้าและทูลเรโหโบอัมว่า 4“ราชบิดาของฝ่าพระบาททรงวางแอกหนักให้พวกข้าพระบาท บัดนี้ขอทรงผ่อนภาระและบรรเทาแอกที่วางไว้ แล้วพวกข้าพระบาทจะรับใช้ฝ่าพระบาท”

5เรโหโบอัมตรัสตอบว่า “ให้เวลาเราสามวัน แล้วพวกท่านค่อยกลับมาพบเรา” ประชากรจึงกลับไป

6กษัตริย์เรโหโบอัมทรงหารือกับบรรดาผู้อาวุโสซึ่งเคยถวายคำปรึกษาแด่โซโลมอนราชบิดาเมื่อครั้งยังทรงพระชนม์อยู่ว่า “ท่านว่าเราควรจะตอบประชาชนเหล่านี้ว่าอย่างไร?”

7พวกเขาทูลว่า “หากวันนี้ฝ่าพระบาทจะทรงเป็นผู้รับใช้ประชาชน ปรนนิบัติเขา และตอบตามที่เขาต้องการ พวกเขาก็จะเป็นผู้รับใช้ของฝ่าพระบาทเสมอไป”

8แต่เรโหโบอัมไม่ฟังคำแนะนำของผู้อาวุโส กลับปรึกษาพระสหายหนุ่มๆ ซึ่งเติบโตมาด้วยกันและรับใช้พระองค์อยู่ 9พระองค์ตรัสถามพวกเขาว่า “พวกเจ้าจะแนะนำอย่างไร? เราควรจะตอบคนที่มาพูดกับเราว่า ‘ขอทรงผ่อนปรนแอกที่ราชบิดาของฝ่าพระบาทวางไว้บนเหล่าข้าพระบาท’ ว่าอย่างไร?”

10พวกคนหนุ่มที่เติบโตขึ้นมากับพระองค์ก็ทูลตอบว่า “ขอให้ตรัสกับบรรดาผู้ที่มาทูลว่า ‘ราชบิดาของฝ่าพระบาททรงวางแอกหนักบนเรา ขอทรงทำให้แอกของเราเบาลง’ นั้นว่า ‘นิ้วก้อยของเราก็หนายิ่งกว่าเอวของเสด็จพ่อเสียอีก 11เสด็จพ่อของเราวางแอกหนักบนพวกเจ้า เราจะทำให้หนักยิ่งขึ้นไปอีก เสด็จพ่อของเราเคยใช้แส้เฆี่ยนพวกเจ้า ส่วนเราจะใช้แมงป่องเล่นงานพวกเจ้า’ ”

12สามวันต่อมาเยโรโบอัมและประชากรทั้งปวงกลับมาเข้าเฝ้ากษัตริย์เรโหโบอัมตามที่ตรัสไว้ว่า “อีกสามวันค่อยกลับมาพบเรา” 13กษัตริย์ตรัสตอบประชาชนด้วยท่าทีแข็งกร้าว ทรงปฏิเสธคำแนะนำของบรรดาผู้อาวุโส 14พระองค์ทรงทำตามคำแนะนำของพวกคนหนุ่มและตรัสว่า “เสด็จพ่อของเราวางแอกหนักให้พวกเจ้า เราจะให้หนักยิ่งขึ้นไปอีก เสด็จพ่อของเราเคยใช้แส้เฆี่ยนเจ้า ส่วนเราจะใช้แมงป่องเล่นงานเจ้า” 15ดังนั้นกษัตริย์ไม่ทรงรับฟังประชาชน เหตุการณ์นี้มาจากองค์พระผู้เป็นเจ้า เพื่อให้สำเร็จตามที่องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสไว้กับเยโรโบอัมบุตรเนบัทผ่านทางอาหิยาห์ชาวชิโลห์

16เมื่ออิสราเอลทั้งปวงเห็นว่ากษัตริย์ไม่ทรงฟังพวกตน พวกเขาก็ตอบกษัตริย์ว่า

“เราเกี่ยวข้องอะไรกับดาวิด?

เรามีส่วนอันใดกับบุตรเจสซี?

อิสราเอลเอ๋ย กลับบ้านกันเถิด!

ให้ดาวิดดูแลปกครองพวกตัวเองไปก็แล้วกัน!”

ดังนั้นชนอิสราเอลจึงพากันกลับบ้าน 17แต่เรโหโบอัมยังคงปกครองคนอิสราเอลซึ่งอยู่ในเมืองต่างๆ ของยูดาห์

18กษัตริย์เรโหโบอัมทรงใช้อาโดนีรัม12:18 ภาษาฮีบรูว่าอาโดรัม(ดู 4:6 และ 5:14)ไปเกณฑ์แรงงานโยธาตามหน้าที่ แต่อิสราเอลทั้งปวงรุมเอาก้อนหินขว้างเขาจนตาย ส่วนกษัตริย์เรโหโบอัมรีบหลบขึ้นราชรถ เสด็จหนีกลับกรุงเยรูซาเล็ม 19ตั้งแต่นั้นมาอิสราเอลก็กบฏต่อราชวงศ์ของดาวิดจนถึงทุกวันนี้

20เมื่อชนอิสราเอลทั้งปวงทราบว่าเยโรโบอัมกลับมาแล้ว ก็ให้คนไปเชิญเขามาอยู่ต่อหน้าชุมนุมประชากรอิสราเอล และแต่งตั้งเป็นกษัตริย์ปกครองอิสราเอล มีเพียงเผ่ายูดาห์ที่ยังคงจงรักภักดีต่อราชวงศ์ของดาวิด

21เมื่อเรโหโบอัมเสด็จมาถึงเยรูซาเล็ม พระองค์ทรงระดมพลรบจากเผ่ายูดาห์ทั้งหมดและเผ่าเบนยามินรวมทั้งหมด 180,000 คน เพื่อทำสงครามกับชนอิสราเอล กอบกู้อาณาจักรคืนมาให้เรโหโบอัมโอรสของโซโลมอน

22แต่พระดำรัสของพระเจ้ามาถึงเชไมอาห์คนของพระเจ้าดังนี้ 23“จงไปบอกเรโหโบอัมโอรสของโซโลมอนกษัตริย์แห่งยูดาห์ ชนเผ่ายูดาห์กับเบนยามินทั้งหมด และประชากรที่เหลือว่า 24องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสดังนี้ว่า อย่าไปรบกับอิสราเอลพี่น้องของเจ้า ทุกคนจงกลับบ้านไป เพราะทั้งหมดนี้เราเป็นผู้กระทำ’ ” พวกเขาก็เชื่อฟังพระดำรัสขององค์พระผู้เป็นเจ้าและพากันกลับบ้านตามที่องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงบัญชา

ลูกวัวทองคำที่เบธเอลและดาน

25ครั้งนั้นเยโรโบอัมทรงสร้างป้อมปราการที่เมืองเชเคมในแดนเทือกเขาแห่งเอฟราอิมและประทับที่นั่น จากที่นั่นทรงไปสร้างเมืองเปนีเอล12:25 ภาษาฮีบรูว่าเปนูเอลเป็นอีกรูปหนึ่งของเปนีเอล

26เยโรโบอัมดำริว่า “บัดนี้ราชอาณาจักรอาจจะหวนกลับไปยังราชวงศ์ดาวิดก็ได้ 27หากประชากรเหล่านี้ไปถวายเครื่องบูชาที่พระวิหารขององค์พระผู้เป็นเจ้าในเยรูซาเล็ม พวกเขาจะกลับไปสวามิภักดิ์ต่อกษัตริย์เรโหโบอัมแห่งยูดาห์นายของเขา เขาจะฆ่าเราและหันกลับไปหากษัตริย์เรโหโบอัม”

28หลังจากขอคำแนะนำของที่ปรึกษาแล้ว กษัตริย์เยโรโบอัมจึงทรงสร้างลูกวัวทองคำสองตัว และแจ้งประชากรว่า “เป็นเรื่องยุ่งยากเกินไปที่จะดั้นด้นไปถึงกรุงเยรูซาเล็ม พี่น้องอิสราเอลทั้งหลาย นี่แหละเทพเจ้าของท่านซึ่งได้นำท่านออกมาจากอียิปต์” 29พระองค์ทรงตั้งลูกวัวทองคำตัวหนึ่งไว้ที่เบธเอล ส่วนอีกตัวหนึ่งอยู่ที่ดาน 30สิ่งนี้ได้กลายเป็นบาป เพราะเหล่าประชากรยังอุตส่าห์ไปถึงเมืองดานเพื่อนมัสการลูกวัวทองคำที่นั่น

31เยโรโบอัมทรงสร้างสถานบูชาบนที่สูงทั้งหลาย และทรงแต่งตั้งปุโรหิตจากคนทุกประเภทแม้พวกเขาไม่ใช่คนเลวี 32พระองค์ทรงกำหนดเทศกาลฉลองในวันที่สิบห้าเดือนที่แปด คล้ายคลึงกับเทศกาลในยูดาห์และถวายเครื่องบูชาบนแท่นบูชา กษัตริย์ทรงทำเช่นนี้ในเบธเอลคือ ถวายบูชาแก่ลูกวัวที่ทรงสร้างขึ้น พระองค์ยังได้ทรงแต่งตั้งปุโรหิตประจำสถานบูชาบนที่สูงทั้งหลายที่ทรงสร้างที่เบธเอล 33ในวันที่สิบห้าเดือนที่แปด เป็นวันที่พระองค์เองทรงกำหนดไว้เพื่อทรงถวายเครื่องบูชาบนแท่นบูชาที่สร้างขึ้นในเบธเอล ดังนั้นจึงทรงกำหนดเทศกาลฉลองนี้แก่ชนอิสราเอล และเสด็จขึ้นไปยังแท่นบูชาเพื่อถวายเครื่องบูชา