1 ተሰሎንቄ 5 – NASV & HHH

New Amharic Standard Version

1 ተሰሎንቄ 5:1-28

1ወንድሞች ሆይ፤ ስለ ዘመናትና ስለ ወራት ልንጽፍላችሁ አያስፈልግም። 2ምክንያቱም ሌባ በሌሊት እንደሚመጣ የጌታም ቀን እንዲሁ እንደሚመጣ እናንተ ራሳችሁ በሚገባ ታውቃላችሁ። 3ሰዎች፣ “ሰላምና ደኅንነት ነው” ሲሉ፣ ምጥ እርጉዝ ሴትን እንደሚይዛት እንዲሁ ጥፋት በድንገት ይመጣባቸዋል፤ ከቶም አያመልጡም።

4እናንተ ግን፣ ወንድሞች ሆይ፤ ይህ ቀን እንደ ሌባ ያስደነግጣችሁ ዘንድ በጨለማ ውስጥ አይደላችሁም፤ 5ሁላችሁም የብርሃን ልጆች፣ የቀንም ልጆች ናችሁና። እኛ ከሌሊት ወይም ከጨለማ ወገን አይደለንም፤ 6እንግዲህ እንንቃ፤ ራሳችንንም እንግዛ እንጂ እንደሚያንቀላፉት እንደ ሌሎቹ አንሁን። 7የሚያንቀላፉ በሌሊት ያንቀላፋሉ፤ የሚሰክሩም በሌሊት ይሰክራሉና። 8እኛ ግን የቀን ሰዎች ስለ ሆንን፣ እምነትንና ፍቅርን እንደ ጥሩር ለብሰን፣ የመዳንን ተስፋ እንደ ራስ ቍር ደፍተን፣ ራሳችንን በመግዛት እንኑር፤ 9እግዚአብሔር ድነትን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አማካይነት እንድናገኝ ነው እንጂ ለቍጣ ወስኖ አላስቀመጠንምና። 10ብንነቃም ሆነ ብናንቀላፋ ከእርሱ ጋር በሕይወት እንድንኖር እርሱ ስለ እኛ ሞተ። 11ስለዚህ በርግጥ አሁን እንደምታደርጉት ሁሉ እርስ በርሳችሁ ተጽናኑ፤ አንዱም ሌላውን ያንጽ።

የመጨረሻ ምክር

12እንግዲህ ወንድሞች ሆይ፤ በእናንተ መካከል በትጋት የሚሠሩትን፣ በጌታም የበላዮቻችሁና መካሪዎቻችሁ የሆኑትን እንድታከብሯቸው እንለምናችኋለን፤ 13ስለ ሥራቸውም በፍቅር እጅግ አክብሯቸው። እርስ በርሳችሁም በሰላም ኑሩ። 14ወንድሞች ሆይ፤ ይህን እንመክራችኋለን፤ ሥራ ፈቶችን ገሥጿቸው፤ ፈሪዎችን አደፋፍሯቸው፤ ደካሞችን እርዷቸው፤ ሰውን ሁሉ ታገሡ። 15ማንም በክፉ ፈንታ ክፉ እንዳይመልስ ተጠንቀቁ፤ ነገር ግን እርስ በርሳችሁም ሆነ ለሌሎች ሰዎች ሁልጊዜ መልካም የሆነውን ነገር ለማድረግ ተጣጣሩ።

16ሁልጊዜ ደስ ይበላችሁ፤ 17ሳታቋርጡ ጸልዩ፤ 18በማናቸውም ሁኔታ አመስግኑ፤ የእግዚአብሔር ፈቃድ በክርስቶስ ኢየሱስ ለእናንተ ይህ ነውና።

19የመንፈስን እሳት አታዳፍኑ፤ 20ትንቢትን አትናቁ። 21ነገር ግን ሁሉን ነገር ፈትኑ፤ መልካም የሆነውን ያዙ፤ 22ከማናቸውም ዐይነት ክፉ ነገር ራቁ።

23የሰላም አምላክ ራሱ ሁለንተናችሁን ይቀድስ፤ መንፈሳችሁ፣ ነፍሳችሁና ሥጋችሁ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሚመጣበት ጊዜ ያለ ነቀፋ ይጠበቁ። 24የጠራችሁ የታመነ ነው፤ እርሱም ያደርገዋል።

25ወንድሞች ሆይ፤ ስለ እኛ ደግሞ5፥25 አንዳንድ ትርጕሞች ደግሞ የሚለው ቃል የላቸውም ጸልዩ።

26ወንድሞችን ሁሉ በተቀደሰ አሳሳም ሰላም በሏቸው።

27ይህ መልእክት ለወንድሞች ሁሉ እንዲነበብ በጌታ ዐደራ እላችኋለሁ።

28የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ ከእናንተ ጋር ይሁን።

Habrit Hakhadasha/Haderekh

אגרת פולוס הראשונה אל-התסלוניקים 5:1-28

1אחים יקרים, איני צריך לכתוב לכם מתי כל זה יתרחש, 2כי הלא יודעים אתם שאיש אינו יודע את המועד. יום ה׳ יבוא במפתיע – כגנב בלילה.

3כאשר בני־האדם יחיו בשלווה ויחשבו שלא יקרה דבר, יירד עליהם האסון במפתיע, כיולדת שאינה יודעת מתי יתקפוה צירי הלידה, ואיש לא יוכל לברוח.

4אבל אתם, אחים יקרים, אינכם שרויים בחשכה בכל הנוגע לדברים אלה, ולכן יום ה׳ לא יפתיע אתכם כגנב. 5כולכם בני־האור ובני־היום; אינכם בני־הלילה ואינכם שייכים לחושך. 6משום כך עמדו על המשמר! אל תירדמו כמו האחרים, אלא צפו לבואו בשקידה ובערנות, 7כי אלה שנרדמים נרדמים בלילה והשיכורים משתכרים בלילה. 8אולם אנחנו בני אור־היום, ועל כן נישאר ערים ומפוכחים, מוגנים על־ידי אמונתנו ואהבתנו וחוסים בתקווה הנפלאה של ישועתנו.

9אלוהים לא בחר בנו כדי לשפוך את זעמו עלינו, אלא כדי להושיענו על־ידי אדוננו ישוע המשיח, 10אשר מת בעדנו למען נחיה איתו לנצח, בין אם נהיה חיים או מתים בשובו. 11לכן המשיכו לעודד ולבנות איש את אחיו כפי שעשיתם עד כה.

12אחים יקרים, אנו מבקשים מכם לכבד את האחראים עליכם מטעם הקהילה, כי אלוהים מינה אותם להשגיח עליכם ולהוכיח אתכם בעת הצורך. 13עליכם להעריך את העבודה שהם עושים למענכם ולאהוב אותם, שכן הם משתדלים לעזור לכם. זכרו, חיו בשלום זה עם זה.

14אחים יקרים, הזהירו את העצלנים שביניכם, עודדו את הפוחדים, חזקו את החלשים והיו סבלנים עם כולם. 15אל תניחו לאיש לשלם רעה תחת רעה, אלא עזרו תמיד איש לאחיו ולכל אדם. 16שמחו תמיד באמונתכם. 17התמידו בתפילה. 18הודו לאלוהים על כל דבר, כי זהו רצון אלוהים מכל המאמינים במשיח.

19אל תבלמו ואל תכלאו את רוח הקודש. 20לעולם אל תזלזלו במה שנאמר בשם ה׳. 21בחנו כל דבר והאמינו רק במה שטוב, ישר ואמיתי. 22התרחקו מכל מעשה רע. 23ואלוהי השלום יטהר ויקדש אתכם לעצמו, וישמור את רוחכם, נפשכם וגופכם בריאים וללא־חטא, עד יום שובו של אדוננו ישוע המשיח. 24אתם יכולים לסמוך על האלוהים אשר בחר בכם שימלא את כל הבטחותיו.

25אחים יקרים, התפללו בעדנו. 26דרשו בשלום כל האחים בנשיקה הקדושה. 27בשם ישוע המשיח אדוננו אני משביע אתכם שתקראו מכתב זה באוזני כל המאמינים.

28חסד אדוננו ישוע המשיח עם כל אחד ואחד מכם. – אמן.