1 ተሰሎንቄ 4 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

1 ተሰሎንቄ 4:1-18

እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝ አኗኗር

1በቀረውስ ወንድሞች ሆይ፤ እግዚአብሔርን ደስ ለማሰኘት እንዴት መኖር እንደሚገባችሁ አስተምረናችኋል፤ በርግጥም እንደዚያው እየኖራችሁ ነው። ስለሆነም በጌታ በኢየሱስ የምንለምናችሁና የምንመክራችሁ ከዚህ በበለጠ ሁኔታ በዚሁ እንድትገፉበት ነው። 2በጌታ በኢየሱስ ሥልጣን ምን ዐይነት ትእዛዝ እንደ ሰጠናችሁ ታውቃላችሁ።

3የእግዚአብሔር ፈቃድ ከዝሙት ርቃችሁ እንድትቀደሱ ነው፤ 4ደግሞም እያንዳንዱ የገዛ ሰውነቱን በቅድስናና በክብር መያዝ4፥4 ወይም ከገዛ ሚስቱ ጋር መኖርን መማር ወይም ሚስት ለማግኘት መማር እንዳለበት እንዲያውቅ ነው፤ 5ይህም እግዚአብሔርን እንደማያውቁ አሕዛብ በፍትወተ ሥጋ ምኞት አይሁን። 6በዚህም ነገር ማንም ተላልፎ ወንድሙን አያታልል፤ ምክንያቱም ከዚህ በፊት እንደ ነገርናችሁና እንዳስጠነቀቅናችሁ ጌታ እንደ እነዚህ ያለውን ኀጢአት ሁሉ የሚፈጽሙትን ይበቀላል፤ 7እግዚአብሔር በቅድስና እንድንመላለስ እንጂ ለርኩሰት አልጠራንምና። 8እንግዲህ ይህን ምክር ንቆ የማይቀበል፣ የናቀው ቅዱስ መንፈሱን የሰጣችሁን እግዚአብሔርን እንጂ ሰውን አይደለም።

9ስለ ወንድማማች መዋደድ ማንም እንዲጽፍላችሁ አያስፈልግም፤ ምክንያቱም እርስ በርሳችሁ እንድትዋደዱ እናንተ ራሳችሁ ከእግዚአብሔር ተምራችኋልና።

10በመላዪቱ መቄዶንያ የሚገኙትን ወንድሞች ሁሉ እንደምትወድዷቸው የታወቀ ነው፤ ነገር ግን ወንድሞች ሆይ፤ ከዚህ በበለጠ እንድታደርጉት እንመክራችኋለን።

11ከዚህ በፊት እንዳዘዝናችሁ በገዛ እጃችሁ ሥሩ፤ በጸጥታ ኑሩ፤ በራሳችሁ ጕዳይ ላይ ብቻ አተኵሩ። 12ይኸውም፣ በዕለት ተለት ኑሯችሁ በውጭ ባሉት ዘንድ እንዲያስከብራችሁና በማንም ሰው ላይ ሸክም እንዳትሆኑ ነው።

የጌታ ዳግም ምጽአት

13ወንድሞች ሆይ፤ አንቀላፍተው ስላሉ ሰዎች ሳታውቁ እንድትቀሩ አንፈልግም፤ ደግሞም ተስፋ እንደሌላቸው እንደ ሌሎች ሰዎች እንድታዝኑ አንሻም። 14ኢየሱስ እንደ ሞተና እንደ ተነሣ ካመንን፣ በኢየሱስ ሆነው ያንቀላፉትን እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር እንደዚሁ ያመጣቸዋል። 15በጌታ ቃል የምንላችሁ ይህን ነው፤ እኛ በሕይወት ያለንና ጌታ እስኪመጣ ድረስ የምንቀር ያንቀላፉትን አንቀድምም፤ 16ጌታ ራሱ በታላቅ ትእዛዝ፣ በመላእክት አለቃ ድምፅና በእግዚአብሔር የመለከት ድምፅ ከሰማይ ይወርዳልና። በክርስቶስ የሞቱትም አስቀድመው ይነሣሉ። 17ከዚያም በኋላ እኛ የቀረነው፣ በሕይወትም የምንኖረው ጌታን በአየር ላይ ለመቀበል ከእነርሱ ጋር በደመና እንነጠቃለን፤ በዚህም መሠረት ለዘላለም ከጌታ ጋር እንሆናለን። 18ስለዚህ በዚህ ቃል እርስ በርሳችሁ ተጽናኑ።

Thai New Contemporary Bible

1เธสะโลนิกา 4:1-18

ดำเนินชีวิตเพื่อให้พระเจ้าพอพระทัย

1สุดท้ายนี้พี่น้องทั้งหลาย เราได้สั่งสอนท่านแล้วว่าจะดำเนินชีวิตเพื่อให้พระเจ้าพอพระทัยได้อย่างไร อันที่จริงท่านก็ทำเช่นนั้นอยู่แล้ว แต่บัดนี้เราขอวิงวอนท่านและหนุนใจท่านในองค์พระเยซูเจ้าให้ทำสิ่งนี้มากยิ่งๆ ขึ้น 2เพราะท่านทราบถึงคำสั่งสอนต่างๆ ที่เรามอบให้ท่านโดยสิทธิอำนาจขององค์พระเยซูเจ้า

3พระเจ้าทรงประสงค์ให้ท่านได้รับการชำระให้บริสุทธิ์คือ ให้ท่านหลีกห่างจากการผิดศีลธรรมทางเพศ 4ให้ท่านแต่ละคนรู้จักควบคุมร่างกายของตน4:4 หรืออยู่กับภรรยาของตนหรือมีภรรยาในทางที่บริสุทธิ์น่านับถือ 5ไม่ใช่มัวเมาในราคะตัณหาเหมือนคนนอกศาสนาซึ่งไม่รู้จักพระเจ้า 6อย่าให้ผู้ใดล่วงเกินหรือทำผิดต่อพี่น้องในเรื่องนี้ องค์พระผู้เป็นเจ้าจะทรงลงโทษคนที่ทำบาปอย่างนั้นตามที่เราได้กล่าวเตือนท่านแล้ว 7เพราะพระเจ้าไม่ได้ทรงเรียกเราให้เป็นคนมีมลทิน แต่ทรงให้เราดำเนินชีวิตอันบริสุทธิ์ 8ฉะนั้นคนที่ละเลยคำสอนนี้ไม่ได้ปฏิเสธมนุษย์ แต่ปฏิเสธพระเจ้าผู้ประทานพระวิญญาณบริสุทธิ์ของพระองค์แก่ท่านทั้งหลาย

9เราไม่จำเป็นต้องเขียนถึงท่านเกี่ยวกับความรักฉันพี่น้อง เพราะพระเจ้าทรงสอนท่านเองอยู่แล้วให้รักกัน 10และที่จริงท่านก็รักพี่น้องทั้งปวงทั่วแคว้นมาซิโดเนีย ถึงกระนั้นพี่น้องทั้งหลาย เราขอให้ท่านรักพี่น้องยิ่งๆ ขึ้นอีก

11ท่านจงมุ่งมาดว่าจะดำเนินชีวิตอันสงบ จะเอาใจใส่ธุรกิจของตน และจะลงมือทำงานเองเหมือนที่เราได้บอกท่านไว้ 12เพื่อชีวิตประจำวันของท่านจะเป็นที่นับถือของคนภายนอกและไม่ต้องพึ่งพาใคร

การเสด็จมาขององค์พระผู้เป็นเจ้า

13พี่น้องทั้งหลาย เราไม่อยากให้ท่านไม่รู้ความจริงเกี่ยวกับคนที่ล่วงลับไปหรือทุกข์โศกเหมือนคนอื่นๆ ซึ่งไม่มีความหวัง 14เราเชื่ออยู่ว่าพระเยซูสิ้นพระชนม์และทรงเป็นขึ้นอีก เราจึงเชื่อว่าพระเจ้าจะทรงให้ผู้ที่ล่วงลับไปในพระเยซูมากับพระเยซูอีก 15เราขอบอกท่านตามพระดำรัสขององค์พระผู้เป็นเจ้าเองว่า พวกเราผู้ที่ยังมีชีวิต ผู้ซึ่งเหลืออยู่จนองค์พระผู้เป็นเจ้าเสด็จมา จะไม่นำหน้าไปก่อนผู้ที่ล่วงลับไปอย่างแน่นอน 16เพราะองค์พระผู้เป็นเจ้าเองจะเสด็จลงมาจากสวรรค์ด้วยพระบัญชากึกก้อง ด้วยเสียงแห่งเทพบดีและเสียงแตรของพระเจ้า และผู้ที่ตายในพระคริสต์จะเป็นขึ้นก่อน 17จากนั้นพวกเราผู้ที่ยังมีชีวิตและเหลืออยู่ก็จะถูกรับขึ้นไปในเมฆพร้อมกับคนเหล่านั้น เพื่อไปเฝ้าองค์พระผู้เป็นเจ้าในฟ้าอากาศและเราจะอยู่กับองค์พระผู้เป็นเจ้าตลอดนิรันดร์ 18ฉะนั้นจงให้กำลังใจกันและกันด้วยข้อความเหล่านี้เถิด