1 ቆሮንቶስ 4 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

1 ቆሮንቶስ 4:1-21

የክርስቶስ ሐዋርያት

1እንግዲህ ሰው ሁሉ እኛን እንደ ክርስቶስ አገልጋዮችና እንደ እግዚአብሔር ምስጢር ባለ ዐደራዎች ሊቈጥረን ይገባል። 2ባለ ዐደራዎችም ታማኝ ሆነው መገኘት አለባቸው። 3በእናንተም ሆነ በሰዎች የፍርድ ሸንጎ ቢፈረድብኝ እኔ በበኩሌ ግድ የለኝም፤ እኔ እንኳ በራሴ ላይ አልፈርድም። 4ኅሊናዬ ንጹሕ ነው፤ ይህ ግን ጥፋት አልባ መሆኔን አያረጋግጥም፤ በእኔ ላይ የሚፈርድ ጌታ ነው። 5ስለዚህ ጊዜው ሳይደርስ በምንም ነገር አትፍረዱ፤ ጌታ እስኪመጣ ጠብቁ። እርሱ በጨለማ ውስጥ የተሰወረውን ወደ ብርሃን ያመጣዋል፤ በሰዎች ልብ ውስጥ ያለውንም ሐሳብ ይገልጠዋል። በዚያን ጊዜ እያንዳንዱ ሰው የሚገባውን ምስጋና ከእግዚአብሔር ዘንድ ይቀበላል።

6እንግዲህ ወንድሞች ሆይ፤ ለእናንተ ጥቅም ብዬ በዚህ ጕዳይ እኔን ራሴንና አጵሎስን ምሳሌ አድርጌ አቅርቤላችኋለሁ፤ ይህንም ያደረግሁት፣ “ከተጻፈው አትለፍ” የሚለውን ከእኛ እንድትማሩ ነው። ስለዚህ አንዱን ሰው ከሌላው አብልጣችሁ አትመኩበት። 7ለመሆኑ፣ አንተን ከሌላው እንድትበልጥ ያደረገህ ማን ነው? ያልተቀበልኸው የራስህ የሆነ ነገር ምን አለ? ከተቀበልህ ታዲያ፣ እንዳልተቀበልህ ለምን ትመካለህ?

8አሁንስ የሚያስፈልጋችሁን ሁሉ አግኝታችኋል! ሀብታምም ሆናችኋል! ከእኛም ተለይታችሁ ነግሣችኋል! በርግጥ ብትነግሡማ እኛም ከእናንተ ጋር በነገሥን ነበር፤ 9ምክንያቱም እግዚአብሔር እኛን ሐዋርያቱን፣ ሞት እንደ ተፈረደባቸው ሰዎች ከሰው ሁሉ መጨረሻ ያሰለፈን ይመስለኛል፤ ለዓለም ሁሉ፣ ለመላእክትም ለሰዎችም ትርኢት ሆነናል። 10እኛ ስለ ክርስቶስ ብለን ሞኞች ነን፤ እናንተ ግን በክርስቶስ ጥበበኞች ናችሁ፤ እኛ ደካሞች ነን፤ እናንተ ግን ብርቱዎች ናችሁ፤ እናንተ የተከበራችሁ ናችሁ፤ እኛ ግን የተዋረድን ነን። 11እስከዚህ ሰዓት ድረስ እንራባለን፤ እንጠማለን፤ እንራቈታለን፤ እንደበደባለን፤ ያለ መጠለያ እንንከራተታለን፤ 12በገዛ እጃችን እየሠራን እንደክማለን፤ ሲረግሙን እንመርቃለን፤ ሲያሳድዱን እንታገሣለን፤ 13ስማችንን ሲያጠፉ መልካም እንመልሳለን፤ እስከ አሁንም ድረስ የዓለም ጕድፍ፣ የምድር ጥራጊ ሆነናል።

14ይህን የምጽፍላችሁ እንደ ተወደዳችሁ ልጆቼ አድርጌ ልመክራችሁ እንጂ ላሳፍራችሁ ብዬ አይደለም። 15ምንም እንኳ በዐሥር ሺሕ የሚቈጠሩ ሞግዚቶች በክርስቶስ ቢኖሯችሁም፣ ብዙ አባቶች ግን የሏችሁም፤ በወንጌል አማካይነት በክርስቶስ ኢየሱስ ወልጄአችኋለሁና። 16ስለዚህ እኔን እንድትመስሉ እለምናችኋለሁ። 17እንግዲህ በጌታ የተወደደውንና የታመነውን ልጄን ጢሞቴዎስን የላክሁላችሁ በዚህ ምክንያት ነው፤ እርሱም በየስፍራው በሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ከማስተምረው ትምህርት ጋር የሚስማማውን፣ በክርስቶስ ኢየሱስ ያለውን የሕይወት አካሄዴን ያሳስባችኋል።

18ከእናንተ አንዳንዶቹ ወደ እናንተ የማልመጣ መስሏቸው ታብየዋል፤ 19ይሁን እንጂ የጌታ ፈቃድ ቢሆን ፈጥኜ ወደ እናንተ እመጣለሁ፤ ከዚያም እነዚህ ትዕቢተኞች የሚናገሩትን ብቻ ሳይሆን፣ ምን ኀይል እንዳላቸውም ማየት እሻለሁ። 20ምክንያቱም የእግዚአብሔር መንግሥት የወሬ ጕዳይ ሳይሆን የኀይል ጕዳይ ነው። 21ለመሆኑ የምትፈልጉት የቱን ነው? በትር ይዤ ልምጣ ወይስ በፍቅርና በገርነት መንፈስ?

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

哥林多前書 4:1-21

基督的使徒

1因此,人應該把我們當作是基督的僕人,是上帝奧祕之事的管家。 2對管家的要求是忠心。 3我對你們或別人給我的評價毫不介意,我也不評價我自己。 4就算我今日問心無愧,也不能自以為義,因為評價我的是主。 5所以,時候未到,不可妄下斷語。到主耶穌再來的時候,祂會揭開暗中的隱情,使人心裡的動機顯露。到時候上帝會給各人應得的稱讚。

6弟兄姊妹,為了你們的益處,我以亞波羅和自己作例子,好讓你們效法我們不越過聖經的準則,免得有人自高自大、厚此薄彼。 7誰使你與眾不同呢?你有哪一樣不是領受的呢?既然一切都是領受的,你為什麼還自誇,好像不是領受的? 8你們已經飽足了,富有了,不需要我們,自己已經作王了。我倒希望你們真的能作王,好讓我們也和你們一同作王。 9我想,上帝把我們使徒排在隊伍的末尾,好像被判了死罪的囚犯,讓我們成了一台戲,給全宇宙看,就是給世人和天使觀看。

10我們為了基督的緣故被人看為愚昧,你們在基督裡倒成了聰明人;我們軟弱,你們倒強壯;你們受人尊敬,我們倒被人藐視。 11我們至今還是又饑又渴,衣不蔽體,遭受毒打,居無定所, 12還要親手勞作。我們被人咒罵,就為對方祝福;受人迫害,就逆來順受; 13被人毀謗,就好言相勸。人們至今仍將我們看作世上的廢物,萬物中的渣滓。

14我之所以寫這些事,並非是叫你們羞愧,而是像勸誡我親愛的兒女一樣勸誡你們。 15雖然有千萬老師將基督的事教導你們,但父親並不多,因為我藉著福音在基督耶穌裡成為你們的父親。 16所以,我勸你們效法我。 17正因如此,我派了提摩太去你們那裡。他在主裡忠心耿耿,是我所愛的孩子。他會提醒你們我在基督裡如何行事為人,在各地、各教會如何教導人。

18你們當中有些人以為我不會再去你們那裡,就傲慢自大起來。 19但主若許可,我會很快去你們那裡。那時我要看看這些驕傲的人究竟是只會空談,還是真有上帝的權能。 20因為上帝的國不在於空談,而在於權能。 21到底你們要什麼呢?要我帶著刑杖去呢?還是要我帶著溫柔慈愛的心去呢?