1 ቆሮንቶስ 3 – NASV & NIRV

New Amharic Standard Version

1 ቆሮንቶስ 3:1-23

በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የተከሠተ መለያየት

1ወንድሞች ሆይ፤ በክርስቶስ ገና ሕፃናት እንደ መሆናችሁ፣ እንደ ሥጋውያን እንጂ እንደ መንፈሳውያን ልናገራችሁ አልቻልሁም። 2ገና ስላልጠነከራችሁ ወተት እንጂ ጠንካራ ምግብ አልመገብኋችሁም፤ አሁንም ቢሆን ገና ናችሁ። 3አሁንም ሥጋውያን ናችሁ፤ በመካከላችሁ ቅናትና ክርክር አለ። ታዲያ፣ ሥጋውያን መሆናችሁ አይደለምን? ተግባራችሁስ እንደ ማንኛውም ሰው ተግባር መሆኑ አይደለምን? 4ምክንያቱም አንዱ፣ “እኔ የጳውሎስ ነኝ”፣ ሌላው ደግሞ፣ “እኔ የአጵሎስ ነኝ” ቢል፣ ሰብአዊ ፍጡር ብቻ መሆናችሁ አይደለምን?

5ለመሆኑ አጵሎስ ምንድን ነው? ጳውሎስስ ምንድን ነው? ጌታ ለእያንዳንዳቸው በሰጣቸው መጠን የሚሠሩ አገልጋዮች ናቸው፤ እናንተም ወደ እምነት የመጣችሁት በእነርሱ አማካይነት ነው። 6እኔ ተከልሁ፤ አጵሎስ ውሃ አጠጣ፤ ያሳደገው ግን እግዚአብሔር ነው። 7ስለዚህ የሚያሳድግ እግዚአብሔር እንጂ፣ የሚተክልም ሆነ ውሃ የሚያጠጣ ምንም አይደለም። 8የሚተክልም ሆነ የሚያጠጣ አንድ ናቸው፤ እያንዳንዱም እንደ ሥራው መጠን የራሱን ሽልማት ይቀበላል። 9እኛ ከእግዚአብሔር ጋር አብረን የምንሠራ ነንና፤ እናንተም የእግዚአብሔር ዕርሻ ናችሁ፤ የእግዚአብሔር ሕንጻ ናችሁ።

10ከእግዚአብሔር በተሰጠኝ ጸጋ መጠን፣ እንደ አንድ ብልኅ ግንበኛ መሠረትን ጣልሁ፤ ሌላውም በላዩ ላይ ይገነባል፤ ነገር ግን እያንዳንዱ እንዴት እንደሚገነባ መጠንቀቅ አለበት። 11ምክንያቱም አንድ ጊዜ ከተመሠረተው መሠረት በቀር ሌላ መሠረት መጣል የሚችል ማንም የለም፤ ይህም መሠረት ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። 12ማንም በዚህ መሠረት ላይ በወርቅ ወይም በብር፣ በከበረ ድንጋይ ወይም በዕንጨት፣ በሣር ወይም በአገዳ ቢያንጽ፣ 13ሥራው እንዴት እንደ ሆነ ይታያል፤ ምክንያቱም ያ ቀን ወደ ብርሃን ያመጣዋል። በእሳት ስለሚገለጥ እሳቱ የእያንዳንዱን ሰው ሥራ ምንነት ይፈትናል።

14ማንም የገነባው ሥራ ቢጸናለት ሽልማቱን ይቀበላል፤ 15ሥራው የተቃጠለበት ግን ሽልማት ይቀርበታል፤ እርሱ ራሱ ግን ይድናል፤ ይሁን እንጂ የሚድነው በእሳት ውስጥ በጭንቅ እንደሚያልፍ ሆኖ ነው።

16እናንተ ራሳችሁ የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ እንደ ሆናችሁ፣ የእግዚአብሔርም መንፈስ በውስጣችሁ እንደሚኖር አታውቁምን? 17ማንም የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ቢያፈርስ እግዚአብሔር እርሱን ያፈርሰዋል፤ የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ቅዱስ ነውና፤ ያም ቤተ መቅደስ እናንተ ናችሁ።

18ማንም ራሱን አያታልል፤ ከእናንተ ማንም በዚህ ዓለም ጥበበኛ የሆነ ቢመስለው፣ ጥበበኛ ይሆን ዘንድ ራሱን እንደ ሞኝ ይቍጠር። 19የዚህ ዓለም ጥበብ በእግዚአብሔር ፊት ሞኝነት ነውና፤ እንዲህ ተብሎ ተጽፏልና፤ “እርሱ ጥበበኞችን በራሳቸው ተንኰል ይይዛቸዋል፤” 20በሌላ ስፍራ ደግሞ፣ “ጌታ የጥበበኞች ሐሳብ ከንቱ መሆኑን ያውቃል” ተብሎ ተጽፏል፤ 21እንግዲህ ማንም በሰው አይመካ። ሁሉ ነገር የእናንተ ነውና፤ 22ጳውሎስም ሆነ አጵሎስ ወይም ኬፋ3፥22 ጴጥሮስ ማለት ነው።፣ ዓለምም ሆነ ሕይወት ወይም ሞት፣ አሁን ያለውም ሆነ ወደ ፊት የሚመጣው፣ ሁሉ የእናንተ ነው፤ 23እናንተም የክርስቶስ ናችሁ፤ ክርስቶስም የእግዚአብሔር ነው።

New International Reader’s Version

1 Corinthians 3:1-23

The Church and Its Leaders

1Brothers and sisters, I couldn’t speak to you as people who live by the Holy Spirit. I had to speak to you as people who were still following the ways of the world. You aren’t growing as Christ wants you to. You are still like babies. 2The words I spoke to you were like milk, not like solid food. You weren’t ready for solid food yet. And you still aren’t ready for it. 3You are still following the ways of the world. Some of you are jealous. Some of you argue. So aren’t you following the ways of the world? Aren’t you acting like ordinary human beings? 4One of you says, “I follow Paul.” Another says, “I follow Apollos.” Aren’t you acting like ordinary human beings?

5After all, what is Apollos? And what is Paul? We are only people who serve. We helped you to believe. The Lord has given each of us our own work to do. 6I planted the seed. Apollos watered it. But God has been making it grow. 7So the one who plants is not important. The one who waters is not important. It is God who makes things grow. He is the important one. 8The one who plants and the one who waters have the same purpose. The Lord will give each of them a reward for their work. 9We work together to serve God. You are like God’s field. You are like his building.

10God has given me the grace to lay a foundation as a wise builder. Now someone else is building on it. But each one should build carefully. 11No one can lay any other foundation than what has already been laid. That foundation is Jesus Christ. 12A person may build on it using gold, silver, jewels, wood, hay or straw. 13But each person’s work will be shown for what it is. On judgment day it will be brought to light. It will be put through fire. The fire will test how good each person’s work is. 14If the building doesn’t burn up, God will give the builder a reward for the work. 15If the building burns up, the builder will lose everything. The builder will be saved, but only like one escaping through the flames.

16Don’t you know that you yourselves are God’s temple? Don’t you know that God’s Spirit lives among you? 17If anyone destroys God’s temple, God will destroy that person. God’s temple is holy. And you all together are that temple.

18Don’t fool yourselves. Suppose some of you think you are wise by the standards of the world. Then you should become “fools” so that you can become wise. 19The wisdom of this world is foolish in God’s eyes. It is written, “God catches wise people in their own evil plans.” (Job 5:13) 20It is also written, “The Lord knows that the thoughts of wise people don’t amount to anything.” (Psalm 94:11) 21So no more bragging about human leaders! All things are yours. 22That means Paul or Apollos or Peter or the world or life or death or the present or the future. All are yours. 23You are joined to Christ and belong to him. And Christ is joined to God.