1 ቆሮንቶስ 2 – NASV & CRO

New Amharic Standard Version

1 ቆሮንቶስ 2:1-16

1ወንድሞች ሆይ፤ ወደ እናንተ በመጣሁ ጊዜ፣ የእግዚአብሔርን ምስጢር2፥1 አንዳንድ ቅጆች ስለ እግዚአብሔር ይላሉ በረቀቀ የንግግር ችሎታ ወይም በላቀ ጥበብ ልገልጥላችሁ አልመጣሁም። 2በመካከላችሁ ሳለሁ ኢየሱስ ክርስቶስን ያውም የተሰቀለውን፣ እርሱን ብቻ እንጂ ሌላ እንዳላውቅ ወስኜ ነበርና። 3ወደ እናንተ የመጣሁት በድካምና በፍርሀት፣ እንዲሁም በብዙ መንቀጥቀጥ ነበር። 4ቃሌም ስብከቴም የመንፈስን ኀይል በመግለጥ እንጂ፣ በሚያባብል የጥበብ ቃል አልነበረም፤ 5ይኸውም እምነታችሁ በእግዚአብሔር ኀይል እንጂ በሰው ጥበብ ላይ እንዳይመሠረት ነው።

ከመንፈስ የተገኘ ጥበብ

6በበሰሉ ሰዎች መካከል ግን ጥበብን እንናገራለን፤ ይሁን እንጂ የዚህችን ዓለም ጥበብ ወይም የሚጠፉትን የዚህችን ዓለም ገዦች ጥበብ አይደለም። 7ነገር ግን ተሰውሮ የነበረውን የእግዚአብሔርን ምስጢር ጥበብ ነው፤ ይህም ጥበብ እግዚአብሔር ከዘመናት በፊት ለክብራችን አስቀድሞ የወሰነው ነው። 8ከዚህ ዓለም ገዦች አንዳቸውም ይህን ጥበብ አልተረዱትም፤ ቢረዱትማ ኖሮ የክብርን ጌታ ባልሰቀሉት ነበር። 9ይሁን እንጂ፣ እንደ ተጻፈው፣

“ዐይን ያላየውን፣

ጆሮ ያልሰማውን፣

የሰውም ልብ ያላሰበውን፣

እግዚአብሔር ለሚወድዱት አዘጋጅቷል፤”

10እግዚአብሔር ግን ይህን በመንፈሱ አማካይነት ለእኛ ገልጦልናል።

መንፈስም የእግዚአብሔርን ጥልቅ ነገር እንኳ ሳይቀር ሁሉን ይመረምራል። 11በውስጡ ካለው ከራሱ መንፈስ በስተቀር ከሰው መካከል የአንድን ሰው ሐሳብ የሚያውቅ ማን አለ? እንደዚሁም ከእግዚአብሔር መንፈስ በስተቀር፣ የእግዚአብሔርን ሐሳብ የሚያውቅ ማንም የለም። 12ከእግዚአብሔር የሆነውን መንፈስ እንጂ፣ የዓለምን መንፈስ አልተቀበልንምና፤ ይህም እግዚአብሔር በነጻ የሰጠንን እናውቅ ዘንድ ነው። 13እኛ የምንናገረው ይህን ነው፤ ከሰው ጥበብ በተማርነው ቃል ሳይሆን፣ ከመንፈስ በተማርነው ቃል እንናገራለን፤ መንፈሳዊ እውነትንም የምንገልጸው በመንፈሳዊ ቃል ነው።2፥13 ወይም መንፈሳዊ እውነትንም ለመንፈሳዊ ሰው እንገልጻለን 14መንፈሳዊ ያልሆነ ሰው ከእግዚአብሔር መንፈስ የሆነውን ነገር ሊቀበል አይችልም፤ ምክንያቱም እንዲህ ያለው ነገር ለእርሱ ሞኝነት ነው፤ በመንፈስም የሚመረመር ስለሆነ፣ ሊረዳው አይችልም። 15መንፈሳዊ ሰው ግን ሁሉንም ነገር ይመረምራል፤ ራሱ ግን በማንም አይመረመርም።

16“ያስተምረው ዘንድ፣

የጌታን ልብ ማን ዐወቀው?”

እኛ ግን የክርስቶስ ልብ አለን።

Knijga O Kristu

1 Korinćanima 2:1-16

1Draga braćo i sestre, kad sam prvi put došao k vama, nisam se služio uzvišenim ni dubokoumnim riječima da vam navijestim Božju poruku. 2Jer odlučio sam među vama ne znati ništa drugo osim Isusa Krista, i to raspetoga. 3Došao sam k vama slab—bojažljivo i drhteći. 4Moj govor i propovijedanje nisu se zasnivali na mudrim i uvjerljivim riječima, nego na djelovanju Svetoga Duha među vama, 5zato da svoju vjeru ne temeljite na ljudskoj mudrosti, nego na Božjoj sili.

6Doduše, kad smo sa zrelim kršćanima, navješćujemo mudrost—ali ne mudrost ovoga svijeta ni takvu mudrost koja bi se svidjela vladarima ovoga svijeta koji su ionako osuđeni na propast. 7Navješćujemo tajnu, skrivenu Božju mudrost koju je Bog namijenio našoj dobrobiti još prije postanka svijeta. 8Vladari ovoga svijeta nisu ju razumjeli—jer da jesu, ne bi raspeli našega Gospodina slave. 9Upravo je to značenje ulomka iz Svetoga pisma:

“Ono što oko još nije vidjelo,

što uho još nije čulo

niti um može zamisliti,

to je Bog pripravio

onima koji ga ljube.”2:9 Izaija 64:3.

10Ali mi to znamo jer nam je Bog otkrio svojim Duhom koji proniče sve, pa tako i Božje dubine. 11Tko može znati misli nekog čovjeka osim njegova vlastitoga čovječjeg duha u njemu? Tako ni Božje misli ne može znati nitko osim Božjega Duha. 12I tog nam je Božjeg Duha (a ne duha svijeta) Bog dao da bismo mogli znati čime nas je obdario. 13Govoreći vam o tomu, ne služimo se riječima ljudske mudrosti, nego riječima koje nam daje Sveti Duh—služeći se riječima Duha da bismo objasnili duhovne istine. 14Ali čovjek tjelesne naravi ne može razumjeti spoznaje koje daje Božji Duh. Njemu se one čine ludošću jer ih valja prosuđivati Duhom. 15Čovjek koji ima Duha može sve prosuđivati, ali drugi nisu kadri prosuđivati njega.

16“Jer tko poznaje Gospodnje misli?

Tko će njemu dati savjet?”2:16 Izaija 40:13.

Ali mi imamo Kristov um.