1 ቆሮንቶስ 12 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

1 ቆሮንቶስ 12:1-31

መንፈሳዊ ስጦታዎች

1ወንድሞች ሆይ፤ አሁን ደግሞ ስለ መንፈሳዊ ስጦታዎች ይህን እንድታውቁ እፈልጋለሁ። 2አረማውያን በነበራችሁበት ጊዜ ወዲያና ወዲህ በመነዳት ድዳ ወደ ሆኑ ጣዖታት እንደ ተወሰዳችሁ ታውቃላችሁ። 3ስለዚህ ማንም በእግዚአብሔር መንፈስ የሚናገር፣ “ኢየሱስ የተረገመ ነው” የሚል የለም፤ እንደዚሁም በመንፈስ ቅዱስ ካልሆነ በቀር፣ ማንም “ኢየሱስ ጌታ ነው” የሚል እንደሌለ እነግራችኋለሁ።

4ስጦታዎች ልዩ ልዩ ሲሆኑ፣ መንፈስ ግን አንድ ነው፤ 5አገልግሎትም ልዩ ልዩ ሲሆን፣ ጌታ ግን አንድ ነው፤ 6አሠራርም ልዩ ልዩ ሲሆን፣ ሁሉን በሁሉ የሚሠራው ግን ያው አንዱ እግዚአብሔር ነው።

7ነገር ግን መንፈስ ቅዱስን መግለጥ ለእያንዳንዱ ሰው የሚሰጠው ለጋራ ጥቅም ነው። 8ለአንዱ በመንፈስ የጥበብን ቃል መናገር ይሰጠዋል፤ ለሌላው ደግሞ በዚያው መንፈስ የዕውቀትን ቃል መናገር ይሰጠዋል፤ 9ለአንዱ በዚያው መንፈስ እምነት ይሰጠዋል፤ ለሌላው ደግሞ በዚያው በአንዱ መንፈስ የመፈወስ ስጦታዎች ይሰጠዋል፤ 10ለአንዱ ታምራትን የማድረግ፣ ለሌላው ትንቢትን የመናገር፣ ለሌላው ደግሞ መናፍስትን የመለየት፣ ለአንዱ በልዩ ልዩ ልሳን የመናገር፣ ለሌላው ደግሞ በልዩ ልዩ ልሳን12፥10 ወይም ቋንቋ፤ እንዲሁም 28 ይመ የተነገረውን የመተርጐም ስጦታ ይሰጠዋል። 11እነዚህ ሁሉ የዚያው የአንዱ መንፈስ ስጦታዎች ሲሆኑ፣ ለእያንዳንዱ ሰው እርሱ ራሱ እንደ ፈቀደ ይሰጠዋል።

አንድ አካል ብዙ ብልቶች

12አካል ብዙ ብልቶች ቢኖሩትም አንድ አካል ነው፤ ነገር ግን ብልቶች ብዙ ቢሆኑም አካል አንድ ነው። ክርስቶስም እንደዚሁ ነው። 13አይሁድ ወይም የግሪክ ሰዎች ብንሆን፣ ባሪያ ወይም ነጻ ሰዎች ብንሆን፣ እኛ ሁላችን አንድ አካል እንድንሆን በአንድ መንፈስ ተጠምቀናልና፤ ሁላችንም አንዱን መንፈስ እንድንጠጣ ተሰጥቶናል።

14አካል የተሠራው ከብዙ ብልቶች እንጂ ከአንድ ብልት አይደለም።

15እግር፣ “እኔ እጅ ስላልሆንሁ የአካል ክፍል አይደለሁም” ቢል ይህን በማለቱ የአካል ክፍል መሆኑ ይቀራልን? 16ጆሮም፣ “እኔ ዐይን ስላልሆንሁ የአካል ክፍል አይደለሁም” ቢል ይህን በማለቱ የአካል ክፍል መሆኑ ይቀራልን? 17አካል በሙሉ ዐይን ቢሆን ኖሮ፣ መስማት ከየት ይገኝ ነበር? አካል በሙሉ ጆሮ ቢሆን ኖሮ፣ ማሽተት ከየት ይገኝ ነበር? 18ነገር ግን እግዚአብሔር እንደ ወደደ እያንዳንዱን በየቦታው መድቧል። 19ሁሉም አንድ ብልት ቢሆን ኖሮ አካል ከየት ይገኝ ነበር? 20እንግዲህ ብልቶች ብዙ ናቸው፣ አካል ግን አንድ ነው።

21ዐይን እጅን፣ “አታስፈልገኝም” ሊለው አይችልም፤ ራስም እግርን፣ “አታስፈልገኝም” ሊለው አይችልም። 22እንዲያውም ደካማ የሚመስሉት የአካል ብልቶች እጅግ አስፈላጊ ናቸው። 23የተናቁ ለሚመስሉን ብልቶች ይበልጥ ክብር እንሰጣቸዋለን፤ ደግሞም የምናፍርባቸውን ብልቶች ይበልጥ እንንከባከባቸዋለን፤ 24የማናፍርባቸው ብልቶቻችን ግን ይህ አያስፈልጋቸውም። እግዚአብሔር ግን የአካል ብልቶችን አንድ ላይ አገጣጥሞ ክብር ለሚጐድላቸው የበለጠ ክብር ሰጥቷቸዋል፤ 25ይህንም ያደረገው በአካል ብልቶች መካከል መለያየት ሳይኖር፣ እርስ በርሳቸው እኩል እንዲተሳሰቡ ነው። 26አንድ ብልት ቢሠቃይ፣ ብልቶች ሁሉ አብረው ይሠቃያሉ፤ አንድ ብልት ቢከብር፣ ሌሎቹም ብልቶች አብረው ደስ ይላቸዋል።

27እንግዲህ እናንተም የክርስቶስ አካል ናችሁ፤ እያንዳንዳችሁም የአካሉ ብልቶች ናችሁ። 28እግዚአብሔር በቤተ ክርስቲያን ውስጥ አንደኛ ሐዋርያትን፣ ሁለተኛ ነቢያትን፣ ሦስተኛ መምህራንን፣ ቀጥሎም ታምራት አድራጊዎችን፣ የመፈወስ ስጦታዎች ያላቸውን፣ ሌሎችን የመርዳት ስጦታ ያላቸውን፣ የማስተዳደር ስጦታ ያላቸውንና በልዩ ልዩ ልሳን የመናገር ስጦታ ያላቸውን ሰዎች መድቧል። 29ሁሉ ሐዋርያት ናቸውን? ሁሉስ ነቢያት ናቸውን? ሁሉስ መምህራን ናቸውን? ሁሉስ ታምራት ያደርጋሉን? 30ሁሉስ የመፈወስ ስጦታዎች አላቸውን? ሁሉስ በልሳኖች ይናገራሉን12፥30 ወይም፣ በሌሎች ቋንቋዎች? ሁሉስ ይተረጕማሉን? 31ነገር ግን ከሁሉ የሚበልጠውን ስጦታ በብርቱ ፈልጉ።12፥31 ወይም፣ እናንተ ግን ከሁሉ የሚበልጠውን ስጦታ በብርቱ እየፈለጋችሁ ነው

ፍቅር

ደግሞም ከሁሉ የሚበልጠውን መንገድ አሳያችኋለሁ።

Thai New Contemporary Bible

1โครินธ์ 12:1-31

ของประทานฝ่ายวิญญาณ

1พี่น้องทั้งหลาย ข้าพเจ้าไม่อยากให้ท่านไม่รู้เรื่องเกี่ยวกับของประทานฝ่ายจิตวิญญาณ 2ท่านก็รู้อยู่ว่าเมื่อท่านยังไม่เชื่อพระเจ้า ท่านได้ถูกชักจูงโดยทางหนึ่งทางใดให้หลงผิดไปพึ่งรูปเคารพที่พูดไม่ได้ 3ฉะนั้นข้าพเจ้าขอบอกท่านว่าไม่มีใครที่กล่าวโดยพระวิญญาณของพระเจ้าจะพูดว่า “ขอให้พระเยซูถูกแช่ง” และไม่มีใครสามารถพูดได้ว่า “พระเยซูทรงเป็นองค์พระผู้เป็นเจ้า” นอกจากผู้ที่กล่าวโดยพระวิญญาณบริสุทธิ์

4ของประทานมีหลายชนิด แต่พระวิญญาณองค์เดียวกันเป็นผู้ประทาน 5งานรับใช้มีหลายประเภท แต่รับใช้องค์พระผู้เป็นเจ้าองค์เดียวกัน 6การงานมีต่างๆ กัน แต่พระเจ้าองค์เดียวกันทรงกระทำการทั้งหมดในคนทั้งปวง

7การสำแดงของพระวิญญาณมีแก่แต่ละคนเพื่อประโยชน์ร่วมกัน 8คนหนึ่งได้รับถ้อยคำแห่งสติปัญญาโดยพระวิญญาณ ส่วนอีกคนหนึ่งได้รับถ้อยคำแห่งความรู้โดยพระวิญญาณองค์เดียวกัน 9อีกคนได้รับของประทานแห่งความเชื่อโดยพระวิญญาณองค์เดียวกัน ส่วนอีกคนมีของประทานในการรักษาโรคโดยพระวิญญาณองค์เดียวกันนั้น 10คนหนึ่งได้รับฤทธิ์เดชอันอัศจรรย์ อีกคนเผยพระวจนะได้ คนหนึ่งสังเกตแยกแยะวิญญาณต่างๆ ได้ ส่วนอีกคนสามารถพูดภาษาแปลกๆ12:10 หรือภาษาต่างๆทั้งสองแห่งในข้อนี้ เช่นเดียวกับข้อ 28 และอีกคนแปลภาษาแปลกๆได้ 11ทั้งหมดนี้ล้วนเป็นการงานของพระวิญญาณองค์เดียวกัน และพระองค์ประทานสิ่งเหล่านี้ให้แก่แต่ละคนตามที่ทรงกำหนดไว้

หลายส่วนในกายเดียวกัน

12กายนั้นเป็นกายเดียวแม้จะประกอบด้วยอวัยวะหลายส่วน และแม้อวัยวะทั้งหมดจะมีหลายส่วนก็ประกอบกันเป็นกายเดียว พระคริสต์ก็เช่นกัน 13เพราะเราทั้งหมดก็รับบัพติศมาโดย12:13 หรือด้วยหรือในพระวิญญาณองค์เดียวเข้าเป็นกายเดียวกัน ไม่ว่าเราจะเป็นยิวหรือกรีก เป็นทาสหรือเป็นไท และเราทั้งหมดก็ได้รับพระวิญญาณองค์เดียวกัน

14กายนั้นไม่ได้ประกอบด้วยอวัยวะเดียว แต่ประกอบด้วยหลายอวัยวะ 15หากเท้าจะพูดว่า “เพราะฉันไม่ใช่มือ ฉันจึงไม่ได้เป็นของร่างกายนั้น” นั่นไม่ใช่เหตุผลที่ทำให้เท้าเลิกเป็นอวัยวะของร่างกายนั้น 16และหากหูจะพูดว่า “เพราะฉันไม่ใช่ตา ฉันจึงไม่ได้เป็นของร่างกายนั้น” นั่นไม่ใช่เหตุผลที่ทำให้หูเลิกเป็นอวัยวะของร่างกายนั้น 17หากทั้งร่างกายเป็นตา การได้ยินจะอยู่ที่ไหน? หากทั้งร่างกายเป็นหู การได้กลิ่นจะอยู่ที่ไหน? 18แต่ที่จริงพระเจ้าทรงจัดอวัยวะต่างๆ ทุกๆ ส่วนไว้ในร่างกายตามที่ทรงประสงค์ 19ถ้าทั้งหมดเป็นอวัยวะเดียว ร่างกายจะมีที่ไหน? 20เช่นนั้นแหละมีหลายอวัยวะแต่เป็นกายเดียวกัน

21ตาไม่อาจพูดกับมือว่า “ฉันไม่ต้องการเธอ!” และศีรษะไม่อาจพูดกับเท้าว่า “ฉันไม่ต้องการเธอ!” 22ในทางตรงกันข้ามอวัยวะต่างๆ ที่ดูเหมือนว่าอ่อนแอกว่าก็เสียไม่ได้ 23และอวัยวะที่เราคิดว่าไม่ค่อยมีเกียรติ เรายังให้เกียรติเป็นพิเศษ และอวัยวะที่ไม่น่าดู เราก็ดูแลเป็นพิเศษ 24ส่วนอวัยวะที่น่าดูอยู่แล้วไม่ต้องดูแลเป็นพิเศษ แต่พระเจ้าทรงรวมอวัยวะต่างๆ ของร่างกายเข้าด้วยกัน และอวัยวะที่ไร้เกียรตินั้นพระองค์ทรงให้เกียรติมากขึ้น 25เพื่อจะไม่มีการแตกแยกกันในร่างกาย แต่เพื่อให้อวัยวะต่างๆ ห่วงใยกันอย่างเท่าเทียมกัน 26ถ้าอวัยวะหนึ่งเจ็บ ทุกส่วนก็พลอยเจ็บด้วย ถ้าอวัยวะหนึ่งมีเกียรติ ทุกส่วนก็ร่วมชื่นชมยินดีด้วย

27ท่านทั้งหลายเป็นกายของพระคริสต์ พวกท่านแต่ละคนเป็นส่วนหนึ่งของกายนั้น 28และในคริสตจักร พระเจ้าได้ทรงแต่งตั้งอัครทูตเป็นอันดับแรก อันดับที่สองคือผู้เผยพระวจนะ อันดับที่สามคือผู้สอน จากนั้นคือผู้ทำการอัศจรรย์ ผู้มีของประทานในการรักษาโรค ผู้สามารถช่วยเหลือผู้อื่น ผู้มีของประทานในการบริหารงาน และผู้พูดภาษาแปลกๆ 29ทุกคนเป็นอัครทูตหรือ? ทุกคนเป็นผู้เผยพระวจนะหรือ? ทุกคนเป็นผู้สอนหรือ? ทุกคนทำการอัศจรรย์หรือ? 30ทุกคนมีของประทานในการรักษาโรคหรือ? ทุกคนพูดภาษาแปลกๆ12:30 หรือภาษาอื่นๆหรือ? ทุกคนแปลได้หรือ? 31แต่ให้เราใฝ่หา12:31 หรือแต่ท่านกำลังกระตือรือร้นใฝ่หาของประทานที่ยิ่งใหญ่กว่านี้

ความรัก

และบัดนี้ข้าพเจ้าจะสำแดงหนทางที่ดีเยี่ยมที่สุดแก่ท่าน