1 ቆሮንቶስ 12 – NASV & NSP

New Amharic Standard Version

1 ቆሮንቶስ 12:1-31

መንፈሳዊ ስጦታዎች

1ወንድሞች ሆይ፤ አሁን ደግሞ ስለ መንፈሳዊ ስጦታዎች ይህን እንድታውቁ እፈልጋለሁ። 2አረማውያን በነበራችሁበት ጊዜ ወዲያና ወዲህ በመነዳት ድዳ ወደ ሆኑ ጣዖታት እንደ ተወሰዳችሁ ታውቃላችሁ። 3ስለዚህ ማንም በእግዚአብሔር መንፈስ የሚናገር፣ “ኢየሱስ የተረገመ ነው” የሚል የለም፤ እንደዚሁም በመንፈስ ቅዱስ ካልሆነ በቀር፣ ማንም “ኢየሱስ ጌታ ነው” የሚል እንደሌለ እነግራችኋለሁ።

4ስጦታዎች ልዩ ልዩ ሲሆኑ፣ መንፈስ ግን አንድ ነው፤ 5አገልግሎትም ልዩ ልዩ ሲሆን፣ ጌታ ግን አንድ ነው፤ 6አሠራርም ልዩ ልዩ ሲሆን፣ ሁሉን በሁሉ የሚሠራው ግን ያው አንዱ እግዚአብሔር ነው።

7ነገር ግን መንፈስ ቅዱስን መግለጥ ለእያንዳንዱ ሰው የሚሰጠው ለጋራ ጥቅም ነው። 8ለአንዱ በመንፈስ የጥበብን ቃል መናገር ይሰጠዋል፤ ለሌላው ደግሞ በዚያው መንፈስ የዕውቀትን ቃል መናገር ይሰጠዋል፤ 9ለአንዱ በዚያው መንፈስ እምነት ይሰጠዋል፤ ለሌላው ደግሞ በዚያው በአንዱ መንፈስ የመፈወስ ስጦታዎች ይሰጠዋል፤ 10ለአንዱ ታምራትን የማድረግ፣ ለሌላው ትንቢትን የመናገር፣ ለሌላው ደግሞ መናፍስትን የመለየት፣ ለአንዱ በልዩ ልዩ ልሳን የመናገር፣ ለሌላው ደግሞ በልዩ ልዩ ልሳን12፥10 ወይም ቋንቋ፤ እንዲሁም 28 ይመ የተነገረውን የመተርጐም ስጦታ ይሰጠዋል። 11እነዚህ ሁሉ የዚያው የአንዱ መንፈስ ስጦታዎች ሲሆኑ፣ ለእያንዳንዱ ሰው እርሱ ራሱ እንደ ፈቀደ ይሰጠዋል።

አንድ አካል ብዙ ብልቶች

12አካል ብዙ ብልቶች ቢኖሩትም አንድ አካል ነው፤ ነገር ግን ብልቶች ብዙ ቢሆኑም አካል አንድ ነው። ክርስቶስም እንደዚሁ ነው። 13አይሁድ ወይም የግሪክ ሰዎች ብንሆን፣ ባሪያ ወይም ነጻ ሰዎች ብንሆን፣ እኛ ሁላችን አንድ አካል እንድንሆን በአንድ መንፈስ ተጠምቀናልና፤ ሁላችንም አንዱን መንፈስ እንድንጠጣ ተሰጥቶናል።

14አካል የተሠራው ከብዙ ብልቶች እንጂ ከአንድ ብልት አይደለም።

15እግር፣ “እኔ እጅ ስላልሆንሁ የአካል ክፍል አይደለሁም” ቢል ይህን በማለቱ የአካል ክፍል መሆኑ ይቀራልን? 16ጆሮም፣ “እኔ ዐይን ስላልሆንሁ የአካል ክፍል አይደለሁም” ቢል ይህን በማለቱ የአካል ክፍል መሆኑ ይቀራልን? 17አካል በሙሉ ዐይን ቢሆን ኖሮ፣ መስማት ከየት ይገኝ ነበር? አካል በሙሉ ጆሮ ቢሆን ኖሮ፣ ማሽተት ከየት ይገኝ ነበር? 18ነገር ግን እግዚአብሔር እንደ ወደደ እያንዳንዱን በየቦታው መድቧል። 19ሁሉም አንድ ብልት ቢሆን ኖሮ አካል ከየት ይገኝ ነበር? 20እንግዲህ ብልቶች ብዙ ናቸው፣ አካል ግን አንድ ነው።

21ዐይን እጅን፣ “አታስፈልገኝም” ሊለው አይችልም፤ ራስም እግርን፣ “አታስፈልገኝም” ሊለው አይችልም። 22እንዲያውም ደካማ የሚመስሉት የአካል ብልቶች እጅግ አስፈላጊ ናቸው። 23የተናቁ ለሚመስሉን ብልቶች ይበልጥ ክብር እንሰጣቸዋለን፤ ደግሞም የምናፍርባቸውን ብልቶች ይበልጥ እንንከባከባቸዋለን፤ 24የማናፍርባቸው ብልቶቻችን ግን ይህ አያስፈልጋቸውም። እግዚአብሔር ግን የአካል ብልቶችን አንድ ላይ አገጣጥሞ ክብር ለሚጐድላቸው የበለጠ ክብር ሰጥቷቸዋል፤ 25ይህንም ያደረገው በአካል ብልቶች መካከል መለያየት ሳይኖር፣ እርስ በርሳቸው እኩል እንዲተሳሰቡ ነው። 26አንድ ብልት ቢሠቃይ፣ ብልቶች ሁሉ አብረው ይሠቃያሉ፤ አንድ ብልት ቢከብር፣ ሌሎቹም ብልቶች አብረው ደስ ይላቸዋል።

27እንግዲህ እናንተም የክርስቶስ አካል ናችሁ፤ እያንዳንዳችሁም የአካሉ ብልቶች ናችሁ። 28እግዚአብሔር በቤተ ክርስቲያን ውስጥ አንደኛ ሐዋርያትን፣ ሁለተኛ ነቢያትን፣ ሦስተኛ መምህራንን፣ ቀጥሎም ታምራት አድራጊዎችን፣ የመፈወስ ስጦታዎች ያላቸውን፣ ሌሎችን የመርዳት ስጦታ ያላቸውን፣ የማስተዳደር ስጦታ ያላቸውንና በልዩ ልዩ ልሳን የመናገር ስጦታ ያላቸውን ሰዎች መድቧል። 29ሁሉ ሐዋርያት ናቸውን? ሁሉስ ነቢያት ናቸውን? ሁሉስ መምህራን ናቸውን? ሁሉስ ታምራት ያደርጋሉን? 30ሁሉስ የመፈወስ ስጦታዎች አላቸውን? ሁሉስ በልሳኖች ይናገራሉን12፥30 ወይም፣ በሌሎች ቋንቋዎች? ሁሉስ ይተረጕማሉን? 31ነገር ግን ከሁሉ የሚበልጠውን ስጦታ በብርቱ ፈልጉ።12፥31 ወይም፣ እናንተ ግን ከሁሉ የሚበልጠውን ስጦታ በብርቱ እየፈለጋችሁ ነው

ፍቅር

ደግሞም ከሁሉ የሚበልጠውን መንገድ አሳያችኋለሁ።

New Serbian Translation

1. Коринћанима 12:1-31

О даровима Светога Духа

1Не желим, браћо, да будете у незнању по питању духовних дарова. 2Знате да сте, као бивши многобошци, били заведени, те сте служили немим идолима. 3Зато вам обзнањујем: нико ко је вођен Божијим Духом, не може да каже: „Проклет био Исус.“ Исто тако, нико не може да каже: „Исус је Господ“, ако није вођен Светим Духом.

4Дарови су различити, али је исти Дух. 5Има и различитих служби, али је исти Господ. 6Има разлике и у деловањима, али је исти Бог који кроз њих делује у свакоме.

7А Дух на свакоме показује своје дејство ради заједничке користи. 8Једноме Дух даје дар мудрог саветовања, док другоме исти Дух даје дар саопштавања посебног знања. 9Једноме Дух даје дар вере, док другоме исти Дух даје дар исцељивања. 10Једноме Дух даје дар да чини чуда, а другоме дар пророштва. Некоме даје дар разликовања духова, некоме да говори другим језицима, а некоме да тумачи те језике. 11Све ово чини један те исти Дух, који по својој вољи додељује дар сваком појединцу.

Једно тело – многи удови

12Наиме, као што у телу има много удова, а сви ти удови, иако их је много, чине једно тело, тако је и са Христом. 13Јер, по Духу смо сви ми крштени у једно тело. Било Јевреји или Грци, било робови или слободни, сви смо напојени једним Духом. 14Јер један уд не чини тело, него многи. 15Ако нога каже: „Пошто нисам рука, не припадам телу“, зар ипак не припада телу? 16И ако ухо каже: „Пошто нисам око, не припадам телу“, зар ипак не припада телу? 17Ако би цело тело било око, где би био слух? Или ако би цело тело било ухо, где би било чуло мириса? 18А Бог је поставио сваки део тела онако како је он хтео. 19Где би било тело да су сви они само један део тела? 20Но, ствари стоје овако: има много делова тела, али је тело једно.

21Око не може да каже руци: „Не требаш ми!“, нити глава ногама: „Не требате ми!“ 22Шта више, и наизглед слаби делови тела су неопходни. 23Па чак и са деловима тела који нам се чине мање вредним поступамо с пуним уважавањем. И са стидним деловима тела поступамо с већом пристојношћу, 24која није потребна другим деловима тела. Бог је, наиме, тако саставио тело, да је неугледнијим деловима тела дао посебну част, 25да не буде поделе у телу, него да се делови тела једнако брину једни за друге. 26Ако један део тела пати, пате и сви остали; ако се једном делу тела указује част, са њим се радују и сви остали.

27Дакле, ви сте тело Христово и делови тела појединачно. 28А Бог је у Цркви поставио прво апостоле, друго пророке, треће учитеље; затим чудотворце, исцелитеље, помагаче, оне са даром управљања, те оне са даром говорења других језика. 29Јесу ли сви апостоли? Јесу ли сви пророци? Јесу ли сви учитељи? Јесу ли сви чудотворци? 30Зар сви поседују дар исцељивања? Зар сви говоре другим језицима? Зар сви тумаче језике? 31Ревносно тежите за вишим даровима!

Ја ћу вам, пак, показати најбољи пут.