1 ቆሮንቶስ 11 – NASV & NIRV

New Amharic Standard Version

1 ቆሮንቶስ 11:1-34

1እኔ የክርስቶስን ምሳሌ እንደምከተል እናንተም የእኔን ተከተሉ።

ሥርዐት ያለው አምልኮ

2በሁሉም ነገር ስለምታስቡልኝና ከእኔ የተቀበላችሁትን ትምህርት11፥2 ወይም ወግ አጥብቃችሁ ስለ ያዛችሁ አመሰግናችኋለሁ።

3ነገር ግን ይህን እንድታውቁ እወድዳለሁ፤ የወንድ ሁሉ ራስ ክርስቶስ ነው፤ የሴትም ራስ ወንድ ነው፤ የክርስቶስም ራስ እግዚአብሔር ነው። 4ራሱን ተከናንቦ የሚጸልይ ወይም ትንቢት የሚናገር ማንኛውም ወንድ የእርሱን ራስ ያዋርዳል፤ 5ራሷን ሳትሸፍን የምትጸልይ ወይም ትንቢት የምትናገር ማንኛዋም ሴት የእርሷን ራስ ታዋርዳለች፤ ጠጕሯን እንደ ተላጨች ይቈጠራልና። 6ሴት ራሷን የማትሸፍን ከሆነ፣ ጠጕሯን ትቈረጥ፤ ጠጕሯን መቈረጥ ወይም መላጨት የሚያሳፍር መስሎ ከታያት ግን ራሷን ትሸፈን።

7ወንድ ራሱን መከናነብ የለበትም፤11፥4-7 ወይም የራሱን ጠጕር አስረዝሞ የሚጸልይ ወይም ትንቢት የሚናገር ማንኛውም ወንድ ራሱ የሆነውን ያዋርዳል፤ 5 ራሷን ሳትከናነብ የምትጸልይ ወይም ትንቢት የምትናገር ማንኛዋም ሴት ራሷ የሆነውን ታዋርዳለች፤ እንዲህ ያለችው ሴት ጠጕራቸውን ከተላጩ ሴቶች አንዷን ትመስላለችና። ሴት ራሷን የማትከናነብ ከሆነ፣ ጠጕሯን ታሳጥር፤ ጠጕሯን መቈረጥ ወይም መላጨት የሚያሳፍር ስለሆነ ግን እንደ ገና ታሳድገው። 7 ወንድ ጠጕሩን ማስረዘም የለበትም፤ ወንድ የእግዚአብሔር ምሳሌና ክብር ነውና፤ ሴት ግን የወንድ ክብር ናት፤ 8ምክንያቱም ሴት ከወንድ ተገኘች እንጂ ወንድ ከሴት አልተገኘም። 9ደግሞም ሴት ለወንድ ተፈጠረች እንጂ ወንድ ለሴት አልተፈጠረም። 10በዚህ ምክንያት፣ በመላእክትም ምክንያት፣ ሴት በሥልጣን ሥር መሆኗን የሚያሳይ ምልክት በራሷ ላይ ታድርግ።

11በጌታ ዘንድ ግን ሴት ያለ ወንድ፣ ወንድም ያለ ሴት አይሆንም። 12ሴት ከወንድ እንደ ተገኘች ሁሉ፣ ወንድም ከሴት ይወለዳልና፤ ነገር ግን የሁሉም መገኛ እግዚአብሔር ነው።

13እስቲ እናንተ ፍረዱ፤ ሴት ራሷን ሳትሸፍን ወደ እግዚአብሔር መጸለይ ይገባታልን? 14ወንድ ጠጕሩን ቢያስረዝም ነውር እንደሚሆንበት ተፈጥሮ እንኳ አያስተምራችሁምን? 15ሴት ግን ጠጕሯን ብታስረዝም ክብሯ አይደለምን? ረዥም ጠጕር የተሰጣት መጐናጸፊያ እንዲሆናት ነውና። 16እንግዲህ ማንም በዚህ ጕዳይ ላይ መከራከር ቢፈልግ፣ እኛም ሆንን የእግዚአብሔር አብያተ ክርስቲያናት ከዚህ የተለየ ልማድ የለንም።

የጌታ እራት

11፥23-25 ተጓ ምብ – ማቴ 26፥26-28ማር 14፥22-24ሉቃ 22፥17-20

17ነገር ግን በምትሰበሰቡበት ጊዜ ለሚጐዳ እንጂ ለሚጠቅም ስላልሆነ፣ ይህን ትእዛዝ ስሰጥ እያመሰገንኋችሁ አይደለም። 18ከሁሉ አስቀድሞ በቤተ ክርስቲያን በምትሰበሰቡበት ጊዜ በመካከላችሁ መለያየት እንዳለ ሰምቻለሁ፤ ይህም ሊሆን እንደሚችል በከፊል አምናለሁ። 19ከእናንተ መካከል እውነተኞቹ ተለይተው ይታወቁ ዘንድ፣ ይህ መለያየት በመካከላችሁ መኖሩ የግድ ነው። 20በምትሰበሰቡበት ጊዜ የምትበሉት የጌታን እራት አይደለም፤ 21በምትበሉበት ጊዜ አንዱ ሌላውን ሳይጠብቅ ምግቡን ይበላልና፤ አንዱ እየተራበ ሌላው ይሰክራል። 22ለመሆኑ የምትበሉበትና የምትጠጡበት ቤት የላችሁምን? ወይስ የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን በመናቅ፣ ምንም የሌላቸውን ታሳፍራላችሁን? እንግዲህ ምን ልበላችሁ? በዚህ ነገር ላመስግናችሁን? ፈጽሞ አላመሰግናችሁም።

23እኔ ከጌታ የተቀበልሁትን ለእናንተ አስተላልፌአለሁና፤ ጌታ ኢየሱስ ዐልፎ በተሰጠባት ሌሊት እንጀራን አንሥቶ 24ከባረከ በኋላ ቈርሶ፣ “ይህ ስለ እናንተ የሚሆን ሥጋዬ ነው፤ ለመታሰቢያዬም አድርጉት” አለ። 25እንዲሁም ከእራት በኋላ ጽዋውን አንሥቶ፣ “ይህ ጽዋ በደሜ የሚሆን አዲስ ኪዳን ነው፤ ስለዚህ ከጽዋው በምትጠጡበት ጊዜ ይህን ለመታሰቢያዬ አድርጉት” አለ። 26ይህን እንጀራ በምትበሉበት ጊዜ፣ ይህንም ጽዋ በምትጠጡበት ጊዜ ሁሉ ጌታ እስከሚመጣ ድረስ ሞቱን ትናገራላችሁ።

27እንግዲህ ማንም ሳይገባው፣ ይህን እንጀራ ቢበላ ወይም የጌታን ጽዋ ቢጠጣ፣ የጌታ ሥጋና ደም ባለ ዕዳ ይሆናል። 28ማንም ሰው ከዚህ እንጀራ ከመብላቱና ከዚህ ጽዋ ከመጠጣቱ በፊት፣ ራሱን ይመርምር፤ 29ምክንያቱም ማንም የጌታን ሥጋ ሳይገባው11፥29 ሳይለይ ወይም ሳይገነዘብ ማለት ነው። ቢበላና ቢጠጣ ፍርድ የሚያመጣበትን ይበላል፤ ይጠጣልም። 30ከእናንተ መካከል ብዙዎች የደከሙትና የታመሙት፣ አንዳንዶችም ያንቀላፉት በዚህ ምክንያት ነው። 31ራሳችንን ብንመረምር ግን ባልተፈረደብን ነበር። 32ነገር ግን ጌታ በሚፈርድብን ጊዜ እንገሠጻለን፤ ይኸውም ከዓለም ጋር አብረን እንዳንኰነን ነው።

33ስለዚህ ወንድሞቼ ሆይ፤ ለመብላት በምትሰበሰቡበት ጊዜ እርስ በርሳችሁ ተጠባበቁ። 34በምትሰበሰቡበት ጊዜ ለፍርድ እንዳይሆንባችሁ፣ ማንም የራበው ሰው ቢኖር በቤቱ ይብላ።

ስለ ቀረው ነገር ደግሞ በምመጣበት ጊዜ እደነግጋለሁ።

New International Reader’s Version

1 Corinthians 11:1-34

1Follow my example, just as I follow the example of Christ.

Proper Worship

2I praise you for being faithful in remembering me. I also praise you for staying true to the teachings of the past. You have stayed true to them, just as I gave them to you. 3But I want you to know that the head of every man is Christ. The head of the woman is the man. And the head of Christ is God. 4Every man who prays or prophesies with his head covered brings shame on his head. 5But every woman who prays or prophesies with her head uncovered brings shame on her head. It is the same as having her head shaved. 6What if a woman does not cover her head? She might as well have her hair cut off. But it is shameful for her to cut her hair or shave her head. So she should cover her head.

7A man should not cover his head. He is the likeness and glory of God. But woman is the glory of man. 8Man did not come from woman. Woman came from man. 9Also, man was not created for woman. Woman was created for man. 10That’s why a woman should have authority over her own head. She should have this because of the angels. 11But here is how things are for those who belong to the Lord. Woman is not independent of man. And man is not independent of woman. 12Woman came from man, and man is born from woman. But everything comes from God.

13You be the judge. Is it proper for a woman to pray to God without covering her head? 14Suppose a man has long hair. Doesn’t the very nature of things teach you that it is shameful? 15And suppose a woman has long hair. Doesn’t the very nature of things teach you that it is her glory? Long hair is given to her as a covering. 16If anyone wants to argue about this, we don’t have any other practice. And God’s churches don’t either.

Celebrating the Lord’s Supper in the Right Way

17In the following matters, I don’t praise you. Your meetings do more harm than good. 18First, here is what people are telling me. When you come together as a church, you take sides. And in some ways I believe it. 19Do you really think you need to take sides? You probably think God favors one side over the other! 20So when you come together, it is not the Lord’s Supper you eat. 21As you eat, some of you go ahead and eat your own private meals. Because of this, one person stays hungry and another gets drunk. 22Don’t you have homes to eat and drink in? You are shaming those in the church who have nothing. Do you think so little of God’s church that you do this? What should I say to you? Should I praise you? Certainly not about the Lord’s Supper!

23I passed on to you what I received from the Lord. On the night the Lord Jesus was handed over to his enemies, he took bread. 24When he had given thanks, he broke it. He said, “This is my body. It is given for you. Every time you eat it, do it in memory of me.” 25In the same way, after supper he took the cup. He said, “This cup is the new covenant in my blood. Every time you drink it, do it in memory of me.” 26You eat the bread and drink the cup. When you do this, you are announcing the Lord’s death until he comes again.

27Eat the bread or drink the cup of the Lord in the right way. Don’t do it in a way that isn’t worthy of him. If you do, you will be guilty. You’ll be guilty of sinning against the body and blood of the Lord. 28Everyone should take a careful look at themselves before they eat the bread and drink from the cup. 29Whoever eats and drinks must recognize the body of Christ. If they don’t, judgment will come upon them. 30That is why many of you are weak and sick. That is why a number of you have died. 31We should think more carefully about what we are doing. Then we would not be found guilty for this. 32When the Lord judges us in this way, he corrects us. Then in the end we will not be judged along with the rest of the world.

33My brothers and sisters, when you come together to eat, you should all eat together. 34Anyone who is hungry should eat something at home. Then when you come together, you will not be judged.

When I come, I will give you more directions.