1 ሳሙኤል 5 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

1 ሳሙኤል 5:1-12

ታቦቱ ወደ አሽዶድና ወደ አቃሮን ተወሰደ

1ፍልስጥኤማውያን የእግዚአብሔርን ታቦት ከማረኩ በኋላ፣ ከአቤንኤዘር ወደ አሽዶድ ወሰዱት። 2ከዚያም ወደ ዳጎን ቤተ ጣዖት አግብተው፣ በዳጎን አጠገብ አኖሩት። 3የአሽዶድም ሰዎች በማግስቱም ማለዳ ተነሥተው ሲመለከቱ እነሆ፣ ዳጎን በእግዚአብሔር ታቦት ፊት መሬት ላይ በግንባሩ ተደፍቶ አገኙት። ከዚያም አንሥተው ወደ ቦታው መለሱት። 4በሚቀጥለው ቀን ጧት ተነሥተው ሲመለከቱ፣ ዳጎን በእግዚአብሔር ታቦት ፊት፣ መሬት ላይ በግንባሩ ተደፍቶ ነበር፤ ራሱና እጆቹ ተሰባብረው በደጃፉ ላይ የወደቁ ሲሆን፣ የቀረው ሌላው አካሉ ብቻ ነበር። 5የዳጎን ካህናትም ሆኑ ሌሎች በአሽዶድ ወዳለው የዳጎን ቤተ ጣዖት የሚገቡ ሁሉ እስከ ዛሬ ድረስ እግራቸው ደጃፉን እንዳይረግጥ ተራምደው የሚያልፉት በዚሁ ምክንያት ነው።

6የእግዚአብሔር እጅ በአሽዶድ ሕዝብና በአካባቢዋ ላይ ጠነከረ፤ እርሱም ጥፋት አመጣባቸው፤ በዕባጭም መታቸው5፥6 ዕብራይስጡ ከዚህ ጋር ይስማማል፤ የሰብዓ ሊቃናት የቩልጊት ትርጕም ግን በምድራቸው ላይ ዐይጥ መታየት ጀመረ፤ እንዲሁም ሞትና ጥፋት በከተማዪቱ ዙሪያ ነበር ይላል።7የአሽዶድ ሰዎች ይህን ባዩ ጊዜ፣ “እጁ በእኛና በአምላካችን በዳጎን ላይ ጠንክሯልና የእስራኤል አምላክ ታቦት በእኛ ዘንድ መቈየት የለበትም” አሉ። 8ከዚህ በኋላ የፍልስጥኤማውያንን ገዦች በሙሉ ጠርተው፣ “የእስራኤልን አምላክ ታቦት ምን እናድርገው?” ሲሉ ጠየቁ።

እነርሱም፣ “የእስራኤልን አምላክ ታቦት ወደ ጌት ውሰዱት” አሏቸው። ስለዚህ የእስራኤልን አምላክ ታቦት ወሰዱት።

9ነገር ግን ታቦቱን ወደዚያ ከወሰዱት በኋላ የእግዚአብሔር እጅ በከተማዪቱ ላይ ሆነ፤ ታላቅ መሸበርም አመጣባቸው፤ ሕፃን ሽማግሌ ሳይል ሕዝቡን በዕባጭ መታ5፥9 ወይም ብልታቸውን አሳበጠባቸው10ስለዚህ የእግዚአብሔርን ታቦት ወደ አቃሮን ሰደዱት።

የእግዚአብሔር ታቦት እዚያ ሲገባም፣ የአቃሮን ሕዝብ፣ “የእስራኤልን አምላክ ታቦት ያመጡብን እኛንና ሕዝባችንን ለማስፈጀት ነው” በማለት ጮኹ። 11የእግዚአብሔር እጅ በርትቶባቸው ስለ ነበር፣ ሞት ከተማዪቱን እጅግ አስደንግጧት ነበርና ሕዝቡ የፍልስጥኤማውያንን ገዦች በሙሉ ጠርተው፣ “የእስራኤልን አምላክ ታቦት ከዚህ አርቁልን፤ ወደ ገዛ ስፍራው ይመለስ፤ አለዚያ እኛንም ሕዝባችንንም ይፈጃል” አሉ። 12ያልሞቱትን ደግሞ ዕባጩ ያሠቃያቸው ስለ ነበር፣ የከተማዪቱ ጩኸት እስከ ሰማይ ወጣ።

Thai New Contemporary Bible

1ซามูเอล 5:1-12

หีบพันธสัญญาในอัชโดดและเอโครน

1หลังจากชาวฟีลิสเตียยึดหีบพันธสัญญาของพระเจ้าแล้ว พวกเขาก็นำหีบจากเอเบนเอเซอร์ไปที่เมืองอัชโดด 2จากนั้นพวกเขานำไปไว้ที่วิหารของพระดาโกน ตั้งไว้ใกล้เทวรูปดาโกน 3เช้าวันรุ่งขึ้น ชาวเมืองอัชโดดพบว่าพระดาโกนล้มลง หน้าคว่ำหมอบลงกับพื้นตรงหน้าหีบพันธสัญญาขององค์พระผู้เป็นเจ้า! พวกเขาจึงตั้งเทวรูปนั้นขึ้นมาใหม่ 4เช้าวันต่อมาก็เป็นเช่นเดิมอีก พระดาโกนคว่ำหน้าหมอบอยู่ตรงหน้าหีบพันธสัญญาขององค์พระผู้เป็นเจ้า! ศีรษะและแขนหักทิ้งอยู่ตรงธรณีประตู เหลือแต่ลำตัว 5ตั้งแต่นั้นมาทั้งปุโรหิตของพระดาโกนและผู้ที่เข้าสู่วิหารของพระดาโกนที่อัชโดดจะไม่ก้าวเหยียบธรณีประตู

6พระหัตถ์ขององค์พระผู้เป็นเจ้าทรงลงโทษชาวเมืองอัชโดดและละแวกใกล้เคียงอย่างหนัก พระองค์ทรงนำภัยพิบัติมายังพวกเขาและลงโทษพวกเขาด้วยฝีระบาด5:6 ฉบับ LXX. และ Vulg. ว่าฝีระบาดและหนูปรากฏในดินแดนของเขา ความตายและความพินาศเกิดขึ้นทั่วเมืองนั้น 7เมื่อชาวอัชโดดตระหนักถึงเหตุการณ์ที่เกิดขึ้นก็ร้องกันว่า “เราจะเก็บหีบพันธสัญญาของพระเจ้าแห่งอิสราเอลไว้ที่นี่ต่อไปไม่ได้ เพราะพระหัตถ์ของพระองค์ทรงลงโทษเราและพระดาโกนเทพเจ้าของเราอย่างหนัก” 8ฉะนั้นพวกเขาจึงเชิญเจ้านายทั้งปวงของฟีลิสเตียมาหารือกันว่า “จะทำอย่างไรกับหีบพันธสัญญาของพระเจ้าแห่งอิสราเอล?”

บรรดาเจ้านายเสนอว่า “ให้ย้ายหีบพันธสัญญาของพระเจ้าแห่งอิสราเอลไปยังเมืองกัท” ดังนั้นพวกเขาจึงย้ายหีบพันธสัญญาของพระเจ้าแห่งอิสราเอลไป

9แต่เมื่อหีบพันธสัญญาย้ายมา พระหัตถ์ขององค์พระผู้เป็นเจ้าเล่นงานเมืองนั้นปั่นป่วนวุ่นวายไปทั้งเมือง พระเจ้าทรงลงโทษชาวเมืองนั้น ทั้งเด็กและผู้ใหญ่ด้วยฝีระบาด5:9 หรือด้วยฝีระบาดที่ขาหนีบ 10พวกเขาจึงส่งหีบพันธสัญญาของพระเจ้าไปยังเอโครน

แต่ขณะที่หีบพันธสัญญากำลังเข้าสู่เมืองเอโครน ชาวเมืองก็ร้องกันว่า “พวกเขาเอาหีบพันธสัญญาของพระเจ้าแห่งอิสราเอลมาฆ่าเราและประชากรของเราแล้ว” 11ฉะนั้นพวกเขาจึงเชิญเจ้านายทั้งปวงของฟีลิสเตียมาประชุมอีก และกล่าวว่า “ขอให้อัญเชิญหีบพันธสัญญาของพระเจ้าแห่งอิสราเอลกลับสู่ภูมิลำเนา มิฉะนั้นหีบนั้น5:11 หรือพระองค์จะฆ่าเราและประชาชนของเรา” เพราะว่าพระหัตถ์ของพระเจ้าทรงลงโทษเมืองนั้นอย่างหนัก ความตายทำให้คนทั้งเมืองหวาดผวา 12ผู้ที่ไม่เสียชีวิตก็เป็นฝีทรมานมากและเสียงร่ำไห้ระงมขึ้นไปถึงฟ้าสวรรค์