1 ሳሙኤል 5 – NASV & NUB

New Amharic Standard Version

1 ሳሙኤል 5:1-12

ታቦቱ ወደ አሽዶድና ወደ አቃሮን ተወሰደ

1ፍልስጥኤማውያን የእግዚአብሔርን ታቦት ከማረኩ በኋላ፣ ከአቤንኤዘር ወደ አሽዶድ ወሰዱት። 2ከዚያም ወደ ዳጎን ቤተ ጣዖት አግብተው፣ በዳጎን አጠገብ አኖሩት። 3የአሽዶድም ሰዎች በማግስቱም ማለዳ ተነሥተው ሲመለከቱ እነሆ፣ ዳጎን በእግዚአብሔር ታቦት ፊት መሬት ላይ በግንባሩ ተደፍቶ አገኙት። ከዚያም አንሥተው ወደ ቦታው መለሱት። 4በሚቀጥለው ቀን ጧት ተነሥተው ሲመለከቱ፣ ዳጎን በእግዚአብሔር ታቦት ፊት፣ መሬት ላይ በግንባሩ ተደፍቶ ነበር፤ ራሱና እጆቹ ተሰባብረው በደጃፉ ላይ የወደቁ ሲሆን፣ የቀረው ሌላው አካሉ ብቻ ነበር። 5የዳጎን ካህናትም ሆኑ ሌሎች በአሽዶድ ወዳለው የዳጎን ቤተ ጣዖት የሚገቡ ሁሉ እስከ ዛሬ ድረስ እግራቸው ደጃፉን እንዳይረግጥ ተራምደው የሚያልፉት በዚሁ ምክንያት ነው።

6የእግዚአብሔር እጅ በአሽዶድ ሕዝብና በአካባቢዋ ላይ ጠነከረ፤ እርሱም ጥፋት አመጣባቸው፤ በዕባጭም መታቸው5፥6 ዕብራይስጡ ከዚህ ጋር ይስማማል፤ የሰብዓ ሊቃናት የቩልጊት ትርጕም ግን በምድራቸው ላይ ዐይጥ መታየት ጀመረ፤ እንዲሁም ሞትና ጥፋት በከተማዪቱ ዙሪያ ነበር ይላል።7የአሽዶድ ሰዎች ይህን ባዩ ጊዜ፣ “እጁ በእኛና በአምላካችን በዳጎን ላይ ጠንክሯልና የእስራኤል አምላክ ታቦት በእኛ ዘንድ መቈየት የለበትም” አሉ። 8ከዚህ በኋላ የፍልስጥኤማውያንን ገዦች በሙሉ ጠርተው፣ “የእስራኤልን አምላክ ታቦት ምን እናድርገው?” ሲሉ ጠየቁ።

እነርሱም፣ “የእስራኤልን አምላክ ታቦት ወደ ጌት ውሰዱት” አሏቸው። ስለዚህ የእስራኤልን አምላክ ታቦት ወሰዱት።

9ነገር ግን ታቦቱን ወደዚያ ከወሰዱት በኋላ የእግዚአብሔር እጅ በከተማዪቱ ላይ ሆነ፤ ታላቅ መሸበርም አመጣባቸው፤ ሕፃን ሽማግሌ ሳይል ሕዝቡን በዕባጭ መታ5፥9 ወይም ብልታቸውን አሳበጠባቸው10ስለዚህ የእግዚአብሔርን ታቦት ወደ አቃሮን ሰደዱት።

የእግዚአብሔር ታቦት እዚያ ሲገባም፣ የአቃሮን ሕዝብ፣ “የእስራኤልን አምላክ ታቦት ያመጡብን እኛንና ሕዝባችንን ለማስፈጀት ነው” በማለት ጮኹ። 11የእግዚአብሔር እጅ በርትቶባቸው ስለ ነበር፣ ሞት ከተማዪቱን እጅግ አስደንግጧት ነበርና ሕዝቡ የፍልስጥኤማውያንን ገዦች በሙሉ ጠርተው፣ “የእስራኤልን አምላክ ታቦት ከዚህ አርቁልን፤ ወደ ገዛ ስፍራው ይመለስ፤ አለዚያ እኛንም ሕዝባችንንም ይፈጃል” አሉ። 12ያልሞቱትን ደግሞ ዕባጩ ያሠቃያቸው ስለ ነበር፣ የከተማዪቱ ጩኸት እስከ ሰማይ ወጣ።

Swedish Contemporary Bible

1 Samuelsboken 5:1-12

Herren straffar filistéerna

1Filistéerna förde sedan Guds ark från slagfältet i Even Haeser till Ashdod 2och ställde den i Dagons tempel bredvid guden Dagon. 3Men när folket i staden nästa morgon steg upp, hade Dagon fallit ner framför Herrens ark med ansiktet mot marken. De satte då upp honom igen på hans plats, 4men när de steg upp morgonen därpå, låg Dagon igen framför Herrens ark. Hans huvud och händer hade slagits av och låg vid tröskeln, medan kroppen låg för sig. 5Det är därför som varken Dagons präster eller någon annan ens idag vill trampa på tröskeln till Dagons tempel i Ashdod.

6Herrens hand vilade tungt över invånarna i Ashdod och de närliggande byarna: han ställde till förödelse bland dem och slog dem med bölder. 7Och när folket förstod vad som höll på att hända, utropade de: ”Vi kan inte behålla Israels Guds ark här längre! Hans hand vilar tungt över oss och vår gud Dagon.” 8De kallade dit filistéernas alla hövdingar och frågade dem vad de skulle göra med arken. Hövdingarna svarade att man skulle föra Israels Guds ark till Gat. Så fördes den till Gat. 9Men när arken anlände dit, vilade Herrens hand över den staden och stor panik uppstod. Han slog alla, både ung och gammal, och de drabbades av bölder.

10De förde därefter arken vidare till Ekron, men när Ekrons invånare såg den komma, utropade de: ”De för hit Israels Guds ark för att döda oss!” 11Sedan kallade de dit filistéernas alla hövdingar och sa till dem att föra tillbaka Israels Guds ark till dess rätta plats, för att inte hela staden skulle dö. Dödsskräcken hade nämligen redan drabbat hela staden, så tung vilade Herrens hand över den. 12De som inte dog fick svåra bölder och gråt och klagan steg mot himlen.