1 ሳሙኤል 28 – NASV & NIVUK

New Amharic Standard Version

1 ሳሙኤል 28:1-25

ሳኦልና የዓይንዶር ነዋሪዋ ሙታን ጠሪ

1በዚያን ዘመን ፍልስጥኤማውያን፣ እስራኤልን ለመውጋት ሰራዊታቸውን ሰበሰቡ። አንኩስም ዳዊትን፣ “አንተና ሰዎችህ አብራችሁኝ ለጦርነት መውጣት እንዳለባችሁ ዕወቁ” አለው።

2ዳዊትም፣ “አገልጋይህ ምን እንደሚያደርግ ያን ጊዜ አንተው ራስህ ታያለህ” አለው።

አንኩስም፣ “መልካም፤ በዘመኔ ሁሉ የራሴ የክብር ዘብ አደርግሃለሁ” ሲል መለሰለት።

3በዚህ ጊዜ ሳሙኤል ሞቶ ነበር፤ እስራኤላውያንም ሁሉ በገዛ ከተማው በአርማቴም አልቅሰው ቀበሩት። ሳኦል ሙታን ሳቢዎችንና መናፍስት ጠሪዎችን ከምድሪቱ አባርሯቸው ነበር።

4ፍልስጥኤማውያን ተሰብስበው በመምጣት በሱነም ሲሰፍሩ፣ ሳኦል ደግሞ እስራኤላውያንን ሁሉ ሰብስቦ በጊልቦዓ ተራራ ላይ ሰፈረ። 5ሳኦል የፍልስጥኤማውያንን ሰራዊት ባየ ጊዜ ፈራ፤ ልቡም እጅግ ተሸበረ። 6እርሱም እግዚአብሔርን ጠየቀ፤ እግዚአብሔር ግን በሕልምም ሆነ በኡሪም ወይም በነቢያት አልመለሰለትም። 7ሳኦልም አገልጋዮቹን፣ “እስቲ ሙታን ሳቢ ሴት ፈልጉልኝና ሄጄ ልጠይቃት” አላቸው።

እነርሱም፣ “እነሆ፤ ሙታን የምትስብ ሴት በዓይንዶር አለች” አሉት።

8ስለዚህ ሳኦል ሌላ ልብስ በመልበስ መልኩን ለውጦ ከሁለት ሰዎች ጋር በሌሊት ወደ ሴቲቱ ሄደ። እርሱም፣ “እባክሽ፣ መናፍስትን ጠይቂልኝ፤ የምነግርሽንም ሰው አስነሺልኝ” አላት።

9ሴትየዋ ግን፣ “እነሆ፤ ሳኦል ሙታን ሳቢዎችንና መናፍስት ጠሪዎችን ከምድሪቱ እንዴት እንዳጠፋና ያደረገባቸውን ታውቃለህ፤ ታዲያ፣ ታስገድለኝ ዘንድ በሕይወቴ ላይ ወጥመድ የዘረጋኸው ለምንድን ነው?” አለችው።

10ሳኦልም፣ “ሕያው እግዚአብሔርን! በዚህ ነገር ቅጣት አያገኝሽም” ሲል በእግዚአብሔር ስም ማለላት።

11ሴትዮዋም፣ “ማንን ላስነሣልህ?” ብላ ጠየቀችው።

እርሱም፣ “ሳሙኤልን አስነሺልኝ” አላት።

12ሴትዮዋም ሳሙኤልን ባየችው ጊዜ በታላቅ ድምፅ ጮኸች፤ ሳኦልንም፣ “አንተ ሳኦል ሆነህ ሳለ፣ ለምን አታለልኸኝ?” አለችው።

13ንጉሡም፣ “አትፍሪ፤ ለመሆኑ ምን እያየሽ ነው?” አላት።

ሴትዮዋም፣ “አንድ መንፈስ28፥13 ወይም መናፍስት ወይም አማልክት ከምድር ሲወጣ አያለሁ” አለችው።

14እርሱም፣ “መልኩ ምን ይመስላል?” ሲል ጠየቃት።

እርሷም፣ “ካባ የለበሰ አንድ ሽማግሌ ሰው እየወጣ ነው” አለችው።

ሳኦልም ሴትየዋ ያየችው ሳሙኤል መሆኑን ዐወቀ፤ በመሬትም ላይ ተደፍቶ እጅ ነሣ።

15ሳሙኤልም ሳኦልን፣ “አስነሥተህ የምታውከኝ ለምንድን ነው?” አለው።

ሳኦልም፣ “እጅግ ተጨንቄአለሁ፤ ፍልስጥኤማውያን እየወጉኝ ነው፤ እግዚአብሔርም ከእኔ ርቋል፤ በነቢያትም ሆነ በሕልም አልመለሰልኝም፤ ስለዚህ ምን ማድረግ እንደሚገባኝ እንድትነግረኝ ጠራሁህ” አለው።

16ሳሙኤልም እንዲህ አለ፤ “ታዲያ እግዚአብሔር ከራቀህ፣ ጠላትም ከሆነህ ለምን ትጠይቀኛለህ? 17እግዚአብሔር በእኔ የተናገረውን አድርጓል፤ እግዚአብሔር መንግሥትህን ከእጅህ ነጥቆ ለጎረቤትህ ለዳዊት ሰጥቶታል። 18ለእግዚአብሔር ስላልታዘዝህ፣ ታላቅ ቍጣውንም በአማሌቃውያን ላይ ስላልፈጸምህ እግዚአብሔር ዛሬ ይህን አድርጎብሃል። 19እግዚአብሔር አንተንና እስራኤልን ለፍልስጥኤማውያን አሳልፎ ይሰጣል፤ አንተና ልጆችህም ነገ ከእኔ ጋር ትሆናላችሁ፤ እንዲሁም እግዚአብሔር የእስራኤልን ሰራዊት ለፍልስጥኤማውያን አሳልፎ ይሰጣል።”

20ሳሙኤል ከተናገረው ቃል የተነሣ፣ ሳኦል በፍርሀት ተውጦ ወዲያውኑ በቁመቱ ሙሉ መሬት ላይ ወደቀ፤ ቀኑንና ሌሊቱን ሁሉ እህል ስላልቀመሰ ጕልበቱ ዝሎ ነበር።

21ሴትየዋ ወደ ሳኦል መጥታ እጅግ መደንገጡን ባየች ጊዜ እንዲህ አለችው፤ “እነሆ፤ አገልጋይህ ቃልህን ሰምቻለሁ፤ በነፍሴም ቈርጬ የነገርኸኝን ፈጽሜአለሁ። 22አሁንም እባክህ አገልጋይህ የምትልህን ስማ፤ ብርታት አግኝተህ መሄድ እንድትችል፣ ጥቂት ምግብ ላቅርብልህና ብላ።”

23እርሱም፣ “አልበላም” በማለት እንቢ አለ።

ነገር ግን የራሱ ሰዎች ከሴትየዋ ጋር ሆነው አጥበቀው ስለ ለመኑት ቃላቸውን ሰማ፤ ከመሬትም ተነሥቶ በዐልጋ ላይ ተቀመጠ።

24ሴትዮዋም በቤቷ የሠባ ጥጃ ስለ ነበራት፣ ፈጥና ዐረደችው፤ ዱቄት ወስዳ ለወሰች፣ እርሾ የሌለው እንጀራም ጋገረች። 25ከዚያም ለሳኦልና ለሰዎቹ አቀረበችላቸው፤ እነርሱም በሉ፤ በዚያም ሌሊት ተነሥተው ሄዱ።

New International Version – UK

1 Samuel 28:1-25

1In those days the Philistines gathered their forces to fight against Israel. Achish said to David, ‘You must understand that you and your men will accompany me in the army.’

2David said, ‘Then you will see for yourself what your servant can do.’

Achish replied, ‘Very well, I will make you my bodyguard for life.’

Saul and the medium at Endor

3Now Samuel was dead, and all Israel had mourned for him and buried him in his own town of Ramah. Saul had expelled the mediums and spiritists from the land.

4The Philistines assembled and came and set up camp at Shunem, while Saul gathered all Israel and set up camp at Gilboa. 5When Saul saw the Philistine army, he was afraid; terror filled his heart. 6He enquired of the Lord, but the Lord did not answer him by dreams or Urim or prophets. 7Saul then said to his attendants, ‘Find me a woman who is a medium, so that I may go and enquire of her.’

‘There is one in Endor,’ they said.

8So Saul disguised himself, putting on other clothes, and at night he and two men went to the woman. ‘Consult a spirit for me,’ he said, ‘and bring up for me the one I name.’

9But the woman said to him, ‘Surely you know what Saul has done. He has cut off the mediums and spiritists from the land. Why have you set a trap for my life to bring about my death?’

10Saul swore to her by the Lord, ‘As surely as the Lord lives, you will not be punished for this.’

11Then the woman asked, ‘Whom shall I bring up for you?’

‘Bring up Samuel,’ he said.

12When the woman saw Samuel, she cried out at the top of her voice and said to Saul, ‘Why have you deceived me? You are Saul!’

13The king said to her, ‘Don’t be afraid. What do you see?’

The woman said, ‘I see a ghostly figure28:13 Or see spirits; or see gods coming up out of the earth.’

14‘What does he look like?’ he asked.

‘An old man wearing a robe is coming up,’ she said.

Then Saul knew it was Samuel, and he bowed down and prostrated himself with his face to the ground.

15Samuel said to Saul, ‘Why have you disturbed me by bringing me up?’

‘I am in great distress,’ Saul said. ‘The Philistines are fighting against me, and God has departed from me. He no longer answers me, either by prophets or by dreams. So I have called on you to tell me what to do.’

16Samuel said, ‘Why do you consult me, now that the Lord has departed from you and become your enemy? 17The Lord has done what he predicted through me. The Lord has torn the kingdom out of your hands and given it to one of your neighbours – to David. 18Because you did not obey the Lord or carry out his fierce wrath against the Amalekites, the Lord has done this to you today. 19The Lord will deliver both Israel and you into the hands of the Philistines, and tomorrow you and your sons will be with me. The Lord will also give the army of Israel into the hands of the Philistines.’

20Immediately Saul fell full length on the ground, filled with fear because of Samuel’s words. His strength was gone, for he had eaten nothing all that day and all that night.

21When the woman came to Saul and saw that he was greatly shaken, she said, ‘Look, your servant has obeyed you. I took my life in my hands and did what you told me to do. 22Now please listen to your servant and let me give you some food so that you may eat and have the strength to go on your way.’

23He refused and said, ‘I will not eat.’

But his men joined the woman in urging him, and he listened to them. He got up from the ground and sat on the couch.

24The woman had a fattened calf at the house, which she slaughtered at once. She took some flour, kneaded it and baked bread without yeast. 25Then she set it before Saul and his men, and they ate. That same night they got up and left.