1 ሳሙኤል 25 – NASV & PCB

New Amharic Standard Version

1 ሳሙኤል 25:1-44

ዳዊት፣ ናባልና አቢግያ

1ሳሙኤልም ሞተ፤ እስራኤል ሁሉ ተሰብስበው አለቀሱለት፤ አርማቴም ባለው ቤቱም ቀበሩት።

ከዚያም ዳዊት ተነሥቶ ወደ ማዖን ምድረ በዳ ወረደ። 2በማዖን ምድር በቀርሜሎስ ንብረት ያለው አንድ ባለጠጋ ሰው ነበረ፤ እርሱም አንድ ሺሕ ፍየሎችና በቀርሜሎስ የሚሸልታቸው ሦስት ሺሕ በጎች ነበሩት። 3የሰውየው ስም ናባል፣ የሚስቱም ስም አቢግያ ነበረ። እርሷም አስተዋይና ውብ ነበረች፤ ባሏ ግን ባለጌና ምግባረ ብልሹ ሰው ነበረ፤ እርሱም ከካሌብ ወገን ነበር።

4ዳዊት በምድረ በዳ ሳለ ናባል በጎቹን እንደሚሸልት ሰማ። 5እርሱም ዐሥር ወጣቶችን እንዲህ ሲል ላካቸው፤ “ወደ ቀርሜሎስ ወደ ናባል ውጡ፤ በስሜም ሰላምታ አቅርቡለት። 6እንዲህም በሉት፤ ‘ዕድሜህ ይርዘም! ሰላም ለአንተ ይሁን፤ ሰላም ለቤተ ሰብህና የአንተ ለሆነው ሁሉ ይሁን።

7“ ‘በዚህ ጊዜ በጎች እንደምትሸልት ሰምቻለሁ፤ እረኞችህ ከእኛ ጋር በነበሩበት ጊዜ፣ ያደረስንባቸው ጕዳት የለም፤ ቀርሜሎስ በነበሩበት ጊዜ ሁሉ፣ የጠፋባቸው አንዳች ነገር አልነበረም። 8የገዛ አገልጋዮችህን ጠይቅ፤ እነርሱም ይነግሩሃል። ስለዚህ አመጣጣችን በጥሩ ቀን በመሆኑ፣ እነዚህ ወጣቶቼ በፊትህ ሞገስ ያግኙ። እባክህን ለአገልጋዮችህና ለልጅህ ለዳዊት የምትችለውን ያህል ስጥ።’ ”

9የዳዊት ሰዎች ከዚያ እንደ ደረሱም፣ በዳዊት ስም ይህንኑ መልእክት ለናባል ከተናገሩ በኋላ ምላሹን ይጠባበቁ ጀመር።

10ናባልም ለዳዊት አገልጋዮች እንዲህ ሲል መለሰ፤ “ለመሆኑ ይህ ዳዊት ማነው? የእሴይስ ልጅ ማን ነው? በአሁኑ ጊዜ ከጌቶቻቸው የሚኰበልሉ አገልጋዮች ብዙ ናቸው። 11ታዲያ እንጀራዬንና ውሃዬን እንዲሁም በጎቼን ለሚሸልቱልኝ ሰዎች ያረድሁትን ፍሪዳ ከየት እንደ መጡ ለማይታወቁ ሰዎች የምሰጠውስ ለምንድን ነው?”

12የዳዊት ሰዎችም ወደ መጡበት ተመለሱ፤ እዚያም እንደ ደረሱ የተባሉትን ሁሉ ነገሩት። 13ዳዊትም ሰዎቹን፣ “በሉ ሁላችሁም ሰይፋችሁን ታጠቁ” አላቸው። ስለዚህ ሁሉም ሰይፋቸውን ታጠቁ፤ ዳዊትም የራሱን ታጠቀ። አራት መቶ ያህል ሰዎች ከዳዊት ጋር ሲወጡ መቶ ያህሉ ግን ጓዝ ለመጠበቅ ቀሩ።

14ከአገልጋዮቹ አንዱ ለናባል ሚስት ለአቢግያ እንዲህ አላት፤ “እነሆ፤ ዳዊት ሰላምታውን እንዲያቀርቡለት ከምድረ በዳ ወደ ጌታችን መልእክተኞች ልኮ ነበር፤ እርሱ ግን የስድብ ናዳ አወረደባቸው። 15እነዚህ ሰዎች ግን እጅግ መልካም ነበሩ፤ ጕዳትም አላደረሱብንም፤ በዱር አብረናቸው በነበርንበት ጊዜም ሁሉ፣ ምንም ነገር አልጠፋብንም። 16በጎቻችንን እየጠበቅን አብረናቸው ባሳለፍነው ጊዜ ሁሉ፣ ቀንም ሆነ ሌሊት በዙሪያችን ዐጥር ሆነውን ነበር። 17አሁንም በጌታችንና በመላው ቤተ ሰቡ ላይ መከራ እያንዣበበ ስለሆነ፣ አስቢበትና የምታደርጊውን አድርጊ፤ እርሱ እንደ ሆነ እንዲህ ያለ ባለጌ ሰው ስለሆነ፣ ደፍሮ የሚነግረው አንድም ሰው የለም።”

18አቢግያም ጊዜ አላጠፋችም፤ ሁለት መቶ እንጀራ፣ ሁለት አቍማዳ የወይን ጠጅ፣ አምስት የተሰናዱ በጎች፣ አምስት መስፈሪያ25፥18 37 ሊትር ያህል ነው። የተጠበሰጠ እሸት፣ መቶ የወይን ዘለላና ዘቢብ፣ ሁለት መቶ ጥፍጥፍ የበለስ ፍሬ ወስዳ በአህዮች ላይ ጫነች። 19ከዚያም አገልጋዮቿን፣ “ቀድማችሁኝ ሂዱ፤ እኔም እከተላችኋለሁ” አለቻቸው፤ ለባሏ ለናባል ግን አልነገረችውም።

20እርሷም በአህያዋ ላይ ተቀምጣ ወደ ሸለቆው በምትወርድበት ጊዜ ዳዊትና ሰዎቹ ወደ እርሷ ወረዱ፤ እርሷም አገኘቻቸው። 21ዳዊትም እንዲህ ብሎ ነበር፤ “ምንም ነገር እንዳይጠፋበት የዚህን ሰው ሀብት በምድረ በዳ ያን ያህል መጠበቄ ለካ በከንቱ ኖሯል፤ ደግ በሠራሁ ይኸው ክፉ መለሰልኝ። 22ነገ ጧት የእርሱ ከሆነው ሁሉ አንድ ወንድ እንኳ በሕይወት ባስቀር እግዚአብሔር በዳዊት ላይ25፥22 አንዳንድ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞች ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ ዕብራይስጡ ግን በዳዊት ጠላቶች ላይ ይላል። እንዲህ ያለውን ነገር ያድርግበት፣ ከዚህም የከፋ ይጨምርበት!”

23አቢግያም ዳዊትን ባየች ጊዜ ወዲያው ከአህያዋ ወርዳ፣ በዳዊትም ፊት በግምባሯ ተደፍታ እጅ ነሣች። 24በእግሩም ላይ ወድቃ እንዲህ አለች፤ “ጌታዬ ሆይ፤ በደሉ በእኔ ላይ ብቻ ይሁን፤ እባክህ አገልጋይህ ታናግርህ፤ የምትልህንም ስማ። 25ጌታዬ፣ ያን ባለጌ ሰው ናባልን ከቁም ነገር አይቍጠረው፤ ስሙ ራሱ ጅል ማለት ስለሆነ፣ ሰውየውም ልክ እንደ ስሙ ነው፤ ጅልነትም አብሮት የኖረ ነው። እኔ አገልጋይህ ግን ጌታዬ የላካቸውን ጕልማሶች አላየኋቸውም። 26ጌታዬ ሆይ፤ ሕያው እግዚአብሔርን! በሕያው ነፍስህም እምላለሁ፤ ደም ከማፍሰስና በገዛ እጅህ ከመበቀል የጠበቀህ እግዚአብሔር ነው፤ አሁንም ጠላቶችህና ጌታዬን ሊጐዱ የሚፈልጉ ሁሉ እንደ ናባል ይሁኑ፤ 27አገልጋይህም ለጌታዬ ያመጣችው ይህ ስጦታ አንተን ለሚከተሉ ጕልማሶች ይሰጥ። 28ጌታዬ የእግዚአብሔርን ጦርነት ስለሚዋጋ እግዚአብሔርም ለጌታዬ ሥርወ መንግሥቱን በርግጥ ለዘላለም የሚያጸናለት በመሆኑ፣ እባክህ የእኔን የአገልጋይህን በደል ይቅር በል፤ በሕይወት ዘመንህም ሁሉ ክፋት አይገኝብህ። 29ማንም ሰው ሕይወትህን ለማጥፋት ቢያሳድድህ እንኳ፣ የጌታዬ ሕይወት በሕያዋን አንድነት እስራት ውስጥ በአምላክህ በእግዚአብሔር ዘንድ በሰላም ትጠበቃለች፤ የጠላቶችህን ሕይወት ግን፣ እንደ ወንጭፍ ድንጋይ ይወነጭፋል። 30እግዚአብሔር ለጌታዬ በሰጠው ተስፋ መሠረት በጎውን ነገር ሁሉ ባደረገለትና በእስራኤልም ላይ ባነገሠው ጊዜ፣ 31ጌታዬ የምታዝንበት ምክንያት ወይም የኅሊና ጸጸት አይኖርህም፤ በከንቱ ያፈሰስኸውም ደም ሆነ በገዛ እጅህ የተበቀልኸው የለምና። እግዚአብሔር በጎ ነገር ባደረገልህ ጊዜ እኔን አገልጋይህን ዐስበኝ።”

32ዳዊትም አቢግያን እንዲህ አላት፤ “ዛሬ እንድታገኚኝ ወደ እኔ የላከሽ፣ የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር የተመሰገነ ይሁን። 33ደም እንዳላፈስና በገዛ እጄ እንዳልበቀል ዛሬ ስለ ጠበቅሽኝ ስለ በጎ ሐሳብሽ አንቺም የተባረክሽ ሁኚ። 34ጕዳት እንዳላደርስብሽ የጠበቀኝ የእስራኤል አምላክ ሕያው እግዚአብሔርን! እንዲህ በቶሎ መጥተሽ ባታገኚኝ ኖሮ፣ እስኪነጋ ድረስ ለናባል አንድ ወንድ እንኳ ባልተረፈ ነበር።”

35ከዚያም ዳዊት ያመጣችለትን ከእጇ ተቀብሎ፣ “በሰላም ወደ ቤትሽ ሂጂ፤ እነሆ፤ ቃልሽን ሰምቻለሁ፤ የጠየቅሽኝንም ተቀብያአለሁ” አላት።

36አቢግያም ወደ ናባል በተመለሰች ጊዜ፣ እነሆ፤ በቤቱ እንደ ንጉሥ ግብዣ ትልቅ ግብዣ አድርጎ አገኘችው፤ ክፉኛም ሰክሮ ልቡ በደስታ ተሞልቶ ነበር። ስለዚህ እስኪነጋ ድረስ ምንም አልነገረችውም። 37ነግቶ የወይን ጠጁ ስካር ካለፈለት በኋላ የሆነውን ሁሉ ስትነግረው ልቡ ቀጥ አለ፤ ሰውነቱም እንደ ድንጋይ በድን ሆነ። 38ዐሥር ቀን ያህል ካለፈ በኋላ፣ እግዚአብሔር ናባልን ቀሠፈው፤ እርሱም ሞተ።

39ዳዊትም ናባል መሞቱን በሰማ ጊዜ፣ “የናባልን ስድብ የተበቀለልኝና እኔን አገልጋዩን ክፉ ከማድረግ የጠበቀኝ እግዚአብሔር ይመስገን፤ ናባል የሠራውንም ክፉ ነገር በራሱ ላይ መለሰበት” አለ።

ዳዊትም አቢግያ ሚስት ትሆነው ዘንድ በመጠየቅ መልእክት ላከባት። 40አገልጋዮቹም ወደ ቀርሜሎስ ሄደው አቢግያን፣ “ሚስት ትሆኚው ዘንድ እንድንወስድሽ ዳዊት ወደ አንቺ ልኮናል” አሏት።

41እርሷም ተነሥታ በግምባሯ በመደፋት እጅ ከነሣች በኋላ፣ “እነሆ፤ እኔ ገረድህ አንተን ለማገልገል፣ የጌታዬንም አገልጋዮች እግር ለማጠብ ዝግጁ ነኝ” አለች። 42አቢግያም ወዲያውኑ በአህያ ላይ ተቀምጣ አምስት አገልጋዮቿን በማስከተል፣ ከዳዊት መልእክተኞች ጋር ሄደች፤ ለዳዊትም ሚስት ሆነችው። 43እንዲሁም ዳዊት ኢይዝራኤላዊቷን አኪናሆምን አገባ፣ ሁለቱም ሚስቶቹ ሆኑ። 44ሳኦል ግን የዳዊት ሚስት የነበረችውን ልጁን ሜልኮልን፣ ለጋሊም ተወላጅ ለሌሳ ልጅ ለፈልጢ ሰጥቶ ነበር።

Persian Contemporary Bible

اول سموئيل 25:1-44

داوود و ابيجايل

1سموئيل وفات يافت و اسرائيلی‌ها جمع شده، برای او عزاداری كردند. سپس او را در گورستان خانوادگی‌اش در رامه دفن كردند.

در اين هنگام، داوود به صحرای معون رفت. 2‏-4در آنجا مرد ثروتمندی از خاندان كاليب به نام نابال زندگی می‌كرد. او املاكی در كرمل داشت و صاحب سه هزار گوسفند و هزار بز بود. همسر او ابيجايل نام داشت و زنی زيبا و باهوش بود، اما خود او خسيس و بداخلاق بود.

يک روز وقتی نابال در كرمل مشغول چيدن پشم گوسفندانش بود، 5داوود ده نفر از افراد خود را نزد او فرستاد تا سلامش را به وی برسانند و چنين بگويند: 6«خدا تو و خانواده‌ات را كامياب سازد و اموالت را بركت دهد. 7شنيده‌ام مشغول چيدن پشم گوسفندانت هستی. ما به چوپانان تو كه در اين مدت در ميان ما بوده‌اند آزاری نرسانده‌ايم و نگذاشته‌ايم حتی يكی از گوسفندانت كه در كرمل هستند، گم شود. 8از چوپانان خود بپرس كه ما راست می‌گوييم يا نه. پس حال كه افرادم را نزد تو می‌فرستم، خواهش می‌كنم لطفی در حق آنها بكن و در اين عيد هر چه از دستت برآيد به غلامانت و به دوستت داوود، بده.»

9افراد داوود پيغام را به نابال رساندند و منتظر پاسخ ماندند. 10نابال گفت: «اين داوود ديگر كيست؟ در اين روزها نوكرانی كه از نزد اربابان فرار می‌كنند، زياد شده‌اند. 11می‌خواهيد نان و آب و گوشت را از دهان كارگرانم بگيرم و به شما كه معلوم نيست از كجا آمده‌ايد، بدهم؟»

12افراد داوود نزد او برگشتند و آنچه را كه نابال گفته بود برايش تعريف كردند. 13داوود در حالی که شمشير خود را به كمر می‌بست، به افرادش دستور داد كه شمشيرهای خود را بردارند. چهارصد نفر شمشير به دست همراه داوود به راه افتادند و دويست نفر نزد اثاثيه ماندند.

14در اين موقع يكی از نوكران نابال نزد ابيجايل رفت و به او گفت: «داوود، افراد خود را از صحرا نزد ارباب ما فرستاد تا سلامش را به او برسانند، ولی ارباب ما به آنها اهانت نمود. 15‏-16در صورتی كه افراد داوود با ما رفتار خوبی داشته‌اند و هرگز آزارشان به ما نرسيده است، بلكه شب و روز برای ما و گوسفندانمان چون حصار بوده‌اند و تا وقتی كه در صحرا نزد آنها بوديم حتی يک گوسفند از گلهٔ ما دزديده نشد. 17بهتر است تا دير نشده فكری به حال ارباب و خانواده‌اش بكنی، چون جانشان در خطر است. ارباب به قدری بداخلاق است كه نمی‌شود با او حرف زد.»

18آنگاه ابيجايل با عجله دويست نان، دو مشک شراب، پنج گوسفند كباب شده، هفده كيلو غلهٔ برشته و صد نان كشمشی و دويست نان انجيری برداشته، آنها را روی چند الاغ گذاشت 19و به نوكران خود گفت: «شما جلوتر برويد و من هم به دنبال شما خواهم آمد.» ولی در اين مورد چيزی به شوهرش نگفت.

20ابيجايل بر الاغ خود سوار شد و به راه افتاد. وقتی در كوه به سر يک پيچ رسيد، داوود و افرادش را ديد كه به طرف او می‌آيند.

21داوود پيش خود چنين فكر كرده بود: «من در حق اين مرد بسيار خوبی كردم. گله‌های او را محافظت نمودم و نگذاشتم چيزی از آنها دزديده شود، اما او اين خوبی مرا با بدی جبران كرد. 22لعنت بر من اگر تا فردا صبح يكی از افراد او را زنده بگذارم!»

23وقتی ابيجايل داوود را ديد فوری از الاغ پياده شد و به او تعظيم نمود. 24او به پاهای داوود افتاده، گفت: «سرور من، تمام اين تقصيرات را به گردن من بگذاريد، ولی اجازه بفرماييد بگويم قضيه از چه قرار است: 25نابال آدم بداخلاقی است. پس خواهش می‌كنم به حرفهايی كه زده است توجه نكنيد. همانگونه كه از اسمش هم پيداست او شخص نادانی است. متأسفانه من از آمدن افراد شما مطلع نشدم. 26سرور من، خداوند نمی‌خواهد دست شما به خون دشمنانتان آلوده شود و خودتان از آنها انتقام بگيريد، به حيات خداوند و به جان شما قسم كه همهٔ دشمنان و بدخواهانتان مانند نابال هلاک خواهند شد. 27حال، خواهش می‌كنم اين هديهٔ كنيزتان را كه برای افرادتان آورده است، قبول فرماييد 28و مرا ببخشيد. خداوند، شما و فرزندانتان را بر تخت سلطنت خواهد نشاند، چون برای اوست كه می‌جنگيد، و در تمام طول عمرتان هيچ بدی به شما نخواهد رسيد. 29هر وقت كسی بخواهد به شما حمله كند و شما را بكشد، خداوند، خدايتان جان شما را حفظ خواهد كرد، همانطور كه گنج گرانبها را حفظ می‌كنند و دشمنانتان را دور خواهد انداخت، همانگونه كه سنگها را در فلاخن گذاشته، می‌اندازند. 30وقتی خداوند تمام وعده‌های خوب خود را در حق شما انجام دهد و شما را به سلطنت اسرائيل برساند، 31آنگاه از اينكه بی‌سبب دستتان را به خون آلوده نكرديد و انتقام نكشيديد، پشيمان نخواهيد شد. هنگامی كه خداوند به شما توفيق دهد، كنيزتان را نيز به ياد آوريد.»

32داوود به ابيجايل پاسخ داد: «متبارک باد خداوند، خدای اسرائيل كه امروز تو را نزد من فرستاد! 33خدا تو را بركت دهد كه چنين حكمتی داری و نگذاشتی دستهايم به خون مردم آلوده شود و با دستهای خود انتقام بگيرم. 34زيرا به حيات خداوند، خدای اسرائيل كه نگذاشت به تو آسيبی برسانم قسم كه اگر تو نزد من نمی‌آمدی تا فردا صبح كسی را از افراد نابال زنده نمی‌گذاشتم.»

35آنگاه داوود هدايای او را قبول كرد و به او گفت: «با خيال راحت به خانه‌ات برگرد، چون مطابق خواهش تو عمل خواهم كرد.»

36وقتی ابيجايل به خانه رسيد ديد كه شوهرش يک مهمانی شاهانه ترتيب داده و خودش هم سرمست از باده است. پس چيزی به او نگفت. 37صبح روز بعد كه مستی از سر نابال پريده بود، زنش همه وقايع را برای او تعريف كرد. آنگاه نابال از شدت ناراحتی سكته كرد 38و بعد از ده روز خداوند بلايی به جانش فرستاد و او مرد.

39داوود وقتی شنيد نابال مرده است، گفت: «خدا خود انتقام مرا از نابال گرفت و نگذاشت خدمتگزارش دستش به خون آلوده شود. سپاس بر خداوند كه نابال را به سزای عمل بدش رسانيد.»

آنگاه داوود قاصدانی نزد ابيجايل فرستاد تا او را برای وی خواستگاری كنند. 40چون قاصدان به كرمل رسيدند قصد خود را به ابيجايل گفتند. 41ابيجايل تعظيم كرده، جواب داد: «من كنيز او هستم و آماده‌ام تا پاهای خدمتگزارانش را بشويم.» 42او فوری از جا برخاست و پنج كنيزش را با خود برداشته، سوار بر الاغ شد و همراه قاصدان نزد داوود رفت و زن او شد.

43داوود زن ديگری نيز به نام اخينوعم يزرعيلی داشت. 44در ضمن شائول دخترش ميكال را كه زن داوود بود به مردی به نام فلطئيل (پسر لايش) از اهالی جليم داده بود.