1 ሳሙኤል 23 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

1 ሳሙኤል 23:1-29

ዳዊት ቅዒላን መታደጉ

1ከዚህ በኋላ “እነሆ፤ ፍልስጥኤማውያን በቅዒላ ላይ ጦርነት ከፍተው፣ ዐውድማውን እየዘረፉት ነው” ብለው ለዳዊት ነገሩት። 2እርሱም፣ “እነዚህን ፍልስጥኤማውያን ሄጄ ልምታን?” ሲል እግዚአብሔርን ጠየቀ።

እግዚአብሔርም፣ “ሂድ፤ ፍልስጥኤማውያንን ምታ፤ ቅዒላንም አድናት” ብሎ መለሰለት።

3የዳዊት ሰዎች ግን፣ “እዚሁ በይሁዳ ምድር እያለን እየፈራን ነው፤ የፍልስጥኤማውያንን ሰራዊት ለመውጋት ወደ ቅዒላ የምንሄድ ከሆነማ ምን ያህል የሚያስፈራ ነው?” አሉት።

4ዳዊት እንደ ገና እግዚአብሔርን ጠየቀ፤ እግዚአብሔርም፣ “ፍልስጥኤማውያንን በእጅህ አሳልፌ ስለምሰጥ፣ ወደ ቅዒላ ውረድ” አለው። 5ስለዚህ ዳዊትና ሰዎቹ ወደ ቅዒላ ሄደው፣ ፍልስጥኤማውያንን ወጉ፤ እንስሶቻቸውን ማርከው ወሰዱ፤ በፍልስጥኤማውያን ላይ ከባድ ጕዳት አደረሱ፤ ዳዊትም የቅዒላን ሕዝብ ታደገ። 6የአቢሜሌክ ልጅ አብያታር ወደ ቅዒላ ወደ ዳዊት በሸሸ ጊዜ፣ ኤፉዱን ይዞ ወርዶ ነበር።

ሳኦል ዳዊትን ማሳደዱ

7ሳኦል የዳዊትን ወደ ቅዒላ መሄድ በሰማ ጊዜ፣ “ዳዊት መዝጊያና የብረት መወርወሪያ ወዳላት ከተማ መግባቱ፣ ራሱን በራሱ እንደ ማሰር ስለሆነ፣ ይህን ሰው እግዚአብሔር በእጄ አሳልፎ ሰጥቶኛል” አለ። 8ሳኦልም፣ ወደ ቅዒላ ወርደው ዳዊትንና ሰዎቹን እንዲከቡ፣ ሰራዊቱን በሙሉ ለጦርነት ጠራ።

9ዳዊትም ሳኦል ክፉ እንዳሰበበት ባወቀ ጊዜ፣ ካህኑን አብያታርን፣ “ኤፉዱን አምጣ” አለው። 10ከዚያም ዳዊት እንዲህ አለ፤ “የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር ሆይ፤ ሳኦል ወደ ቅዒላ መጥቶ፣ በእኔ ምክንያት ከተማዪቱን ለማጥፋት ማሰቡን ባሪያህ በትክክል ሰምቷል። 11የቅዒላ ሰዎች አሳልፈው ይሰጡኝ ይሆን? ባሪያህ እንደሰማውም ሳኦል ወደዚህ ይወርድ ይሆን? የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር ሆይ፤ ለባሪያህ እንድትነግረው እለምንሃለሁ።”

እግዚአብሔርም፣ “አዎን ይወርዳል” አለው።

12ዳዊትም እንደ ገና፣ “የቅዒላ ነዋሪዎች እኔንና ሰዎቼን ለሳኦል አሳልፈው ይሰጡናል?” ሲል ጠየቀ።

እግዚአብሔርም፣ “አዎን አሳልፈው ይሰጧችኋል” አለው።

13ስለዚህ ዳዊትና ስድስት መቶ የሚሆኑ ሰዎቹ ከቅዒላ ተነሥተው መሄድ ወደሚችሉበት ቦታ ሁሉ ሄዱ፤ ዳዊት ከቅዒላ መሸሹን በሰማ ጊዜ፣ ሳኦል ወደዚያ መሄዱን ተወ።

14ዳዊት በምድረ በዳ ባሉ ምሽጎችና በዚፍ ምድረ በዳ ኰረብታዎች ተቀመጠ፤ ሳኦልም በየዕለቱ ይከታተለው ነበር፤ ነገር ግን እግዚአብሔር ዳዊትን አሳልፎ አልሰጠውም።

15ዳዊት በዚፍ ምድረ በዳ ሖሬሽ በተባለ ቦታ ሳለ፣ ሳኦል ሊገድለው መምጣቱን አየ። 16የሳኦል ልጅ ዮናታንም ዳዊት ወዳለበት ወደ ሖሬሽ ሄዶ፣ በእግዚአብሔር ስም አበረታታው፤ 17እርሱም፣ “አትፍራ፤ አባቴ ሳኦል እጁን በአንተ ላይ አያሳርፍም፤ በእስራኤል ላይ ትነግሣለህ፤ እኔም ካንተ ቀጥዬ ሁለተኛ ሰው እሆናለሁ፤ ይህንም አባቴ ሳኦል እንኳ ያውቀዋል” አለው። 18ሁለቱም በእግዚአብሔር ፊት ቃል ኪዳን አደረጉ። ከዚያም ዮናታን ወደ ቤቱ ሄደ፤ ዳዊት ግን እዚያው ሖሬሽ ተቀመጠ።

19የዚፍ ሰዎች ወደ ጊብዓ ወደ ሳኦል ወጥተው እንዲህ አሉ፤ “እነሆ፤ ዳዊት ከየሴሞን በስተ ደቡብ በኤኬላ ኰረብታ ላይ በሖሬሽ ምሽጎች ውስጥ በመካከላችን ተደብቆ የለምን? 20አሁንም ንጉሥ ሆይ፤ አንተ ደስ ባለህ ጊዜ ና እንጂ፣ እርሱን ለንጉሡ አሳልፎ ለመስጠት እኛ አለን።”

21ሳኦል እንዲህ ሲል መለሰ፤ “ለእኔ ስለ ተቈረቈራችሁ እግዚአብሔር ይባርካችሁ፤ 22አሁንም ሂዱና አጣሩ ዘወትር የት እንደ ሆነና በዚያ ያየውን ሰው ለይታችሁ ዕወቁ፤ እጅግ ተንኰለኛ መሆኑን ሰምቻለሁና። 23የሚደበቅባቸውን ቦታዎች ሁሉ ካያችሁ በኋላ ግልጽ መረጃ ይዛችሁ ወደ እኔ ኑ፤ እኔም አብሬችሁ እሄዳለሁ፤ ብቻ በዚያ አገር ይገኝ እንጂ በይሁዳ ነገዶች ሁሉ መካከል ከገባበት ጕድጓድ ገብቼ አወጣዋለሁ።”

24ስለዚህ ሰዎቹ ለመሄድ ተነሥተው ከሳኦል በፊት ወደ ዚፍ ሄዱ፤ በዚህ ጊዜ ዳዊትና ሰዎቹ ከየሴሞን በስተ ደቡብ በዓረባ ውስጥ ባለው በማዖን ምድረ በዳ ነበሩ።

25ሳኦልና ሰዎቹም ዳዊትን ሊፈልጉት ሄዱ፤ እርሱም ይህን በሰማ ጊዜ፣ ወደ ዐለቱ ወርዶ በማዖን ምድረ በዳ ተቀመጠ። ሳኦልም ይህን እንደ ሰማ፣ ዳዊትን በማሳደድ ወደ ማዖን ምድረ በዳ ዘልቆ ገባ።

26ሳኦል በተራራው በአንዱ በኩል ሆኖ ሲያሳድድ፣ ዳዊትና ሰዎቹ ደግሞ በተራራው በሌላ በኩል ከሳኦል ለማምለጥ ይጣደፉ ነበር። ሳኦልና ወታደሮቹ ዳዊትንና ሰዎቹን ከብበው ለመያዝ ተቃርበው ሳሉ፣ 27አንድ መልእክተኛ ወደ ሳኦል መጥቶ፣ “ፍልስጥኤማውያን አገሩን ወረውታልና ቶሎ ድረስ!” አለው። 28ከዚያም ሳኦል ዳዊትን ማሳደዱን ትቶ፣ ከፍልስጥኤማውያን ጋር ሊዋጋ ሄደ። ከዚህ የተነሣም የዚያን ቦታ ስም “የመለያያ ዐለት” ብለው ጠሩት። 29ዳዊትም ከዚያ ወደ ላይ ወጥቶ በዐይንጋዲ ምሽጎች ተቀመጠ።

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

撒母耳記上 23:1-29

大衛營救基伊拉

1一天,大衛得知非利士人正在攻打基伊拉,搶掠麥場, 2便求問耶和華:「我可以去攻打非利士人嗎?」耶和華答道:「你可以去攻打非利士人,營救基伊拉。」 3大衛的部下卻對他說:「我們在猶大這裡尚且膽戰心驚,何況去基伊拉攻打非利士軍隊呢!」 4大衛再求問耶和華,耶和華答道:「到基伊拉去吧,我一定把非利士人交在你手裡。」 5於是,大衛和部下到基伊拉去攻打非利士人,大敗敵人,奪取了他們的牲畜,救出基伊拉人。

6亞希米勒的兒子祭司亞比亞他基伊拉投奔大衛時,把以弗得也帶了去。 7掃羅得知大衛基伊拉,就說:「這一次是上帝把他交在我手中了,因為他竟然自投網羅,進入有門有閂的城。」 8掃羅召集全軍準備攻打基伊拉,圍困大衛和他的部下。 9大衛知道了掃羅的計謀,便吩咐祭司亞比亞他把以弗得帶來, 10然後說:「耶和華,以色列的上帝啊,僕人聽說掃羅要來毀滅基伊拉,因為我在這裡。 11基伊拉的人會不會把我交給掃羅呢?掃羅是不是像我聽說的那樣要來這裡呢?耶和華,以色列的上帝啊,求你告訴我。」耶和華說:「掃羅一定會來。」 12大衛又問耶和華:「基伊拉的人會不會把我和我的部下交給掃羅呢?」耶和華說:「他們一定會。」 13於是,大衛率領自己的六百部下離開基伊拉,到處流浪。掃羅得知大衛已經離開基伊拉,就不去了。

14大衛住在曠野的堡壘或西弗曠野的山區。掃羅天天搜捕大衛,但上帝沒有把大衛交在他的手中。 15大衛西弗曠野的何利沙得知掃羅要來殺他。 16掃羅的兒子約拿單何利沙大衛,鼓勵大衛堅定地信靠上帝。 17他對大衛說:「不要害怕,我父親害不了你。你將做以色列的王,我將做你的宰相。我父親也明白這一點。」 18二人在耶和華面前立了約。之後,大衛仍留在何利沙約拿單則回家去了。

19西弗人去基比亞掃羅,說:「大衛就躲在我們那裡,在曠野南面哈基拉山上何利沙的堡壘裡。 20王啊,你隨時都可以下來,我們一定把他交在王的手裡。」 21掃羅說:「願耶和華賜福給你們!因為你們體恤我。 22我聽說他非常狡猾,你們再回去弄清楚他的行蹤,誰在那裡見過他, 23查明他的藏身之處,回來如實告訴我,然後我會與你們同去。如果他在猶大境內,我要搜遍千家萬戶,找到他。」 24於是,西弗人先回去了。當時大衛和他的部下在曠野南面的亞拉巴,即瑪雲曠野。 25大衛聽說掃羅和手下正在搜尋他,便率領部下前往瑪雲曠野的磐石,住在那裡。掃羅得知後,便去瑪雲曠野追趕大衛26掃羅在山這邊走,大衛和他的部下在山那邊走,急急忙忙地躲避掃羅掃羅和他的手下四面包圍過來,眼看就要抓住他們了。 27這時,掃羅的信使前來稟報,說非利士人前來犯境,請王速回。 28掃羅只好放棄追趕大衛,回師迎戰非利士人。因此,那地方叫「脫險岩」。 29後來,大衛從那裡轉移到隱·基底的堡壘裡。