1 ሳሙኤል 16 – NASV & PCB

New Amharic Standard Version

1 ሳሙኤል 16:1-23

ሳሙኤል ዳዊትን መቅባቱ

1እግዚአብሔር ሳሙኤልን፣ “በእስራኤል ላይ እንዳይነግሥ ለናቅሁት ለሳኦል የምታለቅስለት እስከ መቼ ነው? ወደ ቤተ ልሔሙ ሰው ወደ እሴይ ስለምልክህ፣ ዘይት በቀንድ ሞልተህ ሂድ፤ ከልጆቹ አንዱ ንጉሥ ይሆን ዘንድ መርጬዋለሁ” አለው።

2ሳሙኤል ግን፣ “ሳኦል ከሰማ ስለሚገድለኝ እንዴት መሄድ እችላለሁ?” አለ።

እግዚአብሔርም እንዲህ አለው፤ “አንዲት ጊደር ይዘህ ሂድና፣ ‘ለእግዚአብሔር ልሠዋ መጥቻለሁ’ በል። 3እሴይን ወደ መሥዋዕቱ ጥራው፤ ከዚያም የምታደርገውን አሳይሃለሁ፤ የምነግርህንም ሰው ትቀባልኛለህ።”

4ሳሙኤል እግዚአብሔር ያለውን ነገር አደረገ። ቤተ ልሔም እንደ ደረሰም፣ የከተማዪቱ ሽማግሌዎች እየተንቀጠቀጡ ሊገናኙት መጡ፣ እነርሱም “አመጣጥህ ለሰላም ነውን?” ብለው ጠየቁት።

5ሳሙኤልም፣ “አዎን፤ ለሰላም ነው፤ የመጣሁትም ለእግዚአብሔር መሥዋዕት ላቀርብ ነው፤ እናንተም ራሳችሁን ቀድሳችሁ ከእኔ ጋር ወደ መሥዋዕቱ ኑ” ሲል መለሰላቸው። ከዚያም እሴይንና ልጆቹን ቀደሳቸው፤ ወደ መሥዋዕቱም እንዲመጡ ጠራቸው።

6እዚያ በደረሱ ጊዜም፣ ሳሙኤል ኤልያብን አይቶ፣ “በርግጥ እግዚአብሔር የቀባው ሰው እነሆ፤ በእግዚአብሔር ፊት ቆሟል” ብሎ ዐሰበ።

7እግዚአብሔር ግን ሳሙኤልን፣ “መልኩን ወይም ቁመቱን አትይ፤ እኔ ንቄዋለሁና። እግዚአብሔር የሚያየው፣ ሰው እንደሚያየው አይደለም። ሰው የውጭውን ገጽታ ያያል፤ እግዚአብሔር ግን ልብን ያያል” አለው።

8ከዚያም እሴይ አሚናዳብን ጠርቶ በሳሙኤል ፊት እንዲያልፍ አደረገ፤ ሳሙኤል ግን፣ “እግዚአብሔር ይህንም አልመረጠውም” አለው። 9እሴይም ሣማን አሳለፈ፤ ሳሙኤልም፣ “እርሱንም እግዚአብሔር አልመረጠውም” አለ። 10እሴይም ሰባቱን ልጆቹን በሳሙኤል ፊት እንዲያልፉ አደረገ፤ ሳሙኤል ግን፣ “እግዚአብሔር እነዚህንም አልመረጣቸውም” አለው። 11ቀጥሎም እሴይን፣ “ልጆችህ እነዚሁ ብቻ ናቸውን?” ሲል ጠየቀው።

እሴይም፣ “የሁሉም ታናሽ ገና አልመጣም፤ ነገር ግን በጎች እየጠበቀ ነው” ብሎ መለሰ።

ሳሙኤልም፣ “በል ልከህ አስመጣው፤ እስኪመጣ ድረስ አንቀመጥምና16፥11 አንዳንድ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞች ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ ዕብራይስጡ ግን አንሰበሰብምና ይላል።” አለው።

12ስለዚህ ልኮ አስመጣው፤ እርሱም ደም ግባት ያለው፣ ዐይኑ የሚያምርና መልከ መልካም ነበረ።

እግዚአብሔርም፣ “የመረጥሁት ይህ ነውና ተነሥተህ ቅባው” አለው።

13ሳሙኤልም የዘይቱን ቀንድ ወስዶ በወንድሞቹ ፊት ቀባው። ከዚያ ቀን ጀምሮ የእግዚአብሔር መንፈስ በዳዊት ላይ በኀይል መጣ፤ ሳሙኤልም ወደ አርማቴም ሄደ።

ዳዊት ሳኦልን ማገልገሉ

14የእግዚአብሔር መንፈስ ከሳኦል ስለ ራቀ፤ ከእግዚአብሔር ዘንድ የታዘዘ ክፉ16፥14 በዚህ እንዲሁም በቍጥር 15፡16 እና 23 ላይ ጐጂ መንፈስ ያሠቃየው ነበር።

15የሳኦል አገልጋዮችም እንዲህ አሉት፤ “እነሆ፤ ከእግዚአብሔር ዘንድ የታዘዘ ክፉ መንፈስ እያሠቃየህ ነው። 16እንግዲህ በገና መደርደር የሚችል ሰው እንዲፈልጉ፣ ጌታችን በፊቱ የሚቆሙትን አገልጋዮቹን ይዘዝ፤ ከዚያም ከእግዚአብሔር የታዘዘው ክፉ መንፈስ ባንተ ላይ በሚመጣ ጊዜ በገና ይደረድርልሃል፤ ደኅናም ትሆናለህ።”

17ስለዚህ ሳኦል አገልጋዮቹን፣ “መልካም አድርጎ በገና መደርደር የሚችል ሰው ፈልጋችሁ አምጡልኝ” አላቸው።

18ከአገልጋዮቹም አንዱ፣ “መልካም አድርጎ በገና መደርደር የሚችለውን የቤተ ልሔሙን የእሴይን ልጅ አይቻለሁ፣ እርሱም ጀግናና ተዋጊ ነው፤ በአነጋገሩ አስተዋይና የደስ ደስ ያለው ነው፤ እግዚአብሔርም ከእርሱ ጋር ነው” ብሎ መለሰ።

19ከዚያም ሳኦል፣ “ከበጎች ጋር ያለውን ልጅህን ዳዊትን ላክልኝ” ሲል መልክተኞችን ወደ እሴይ ላከ። 20እሴይም እንጀራና በወይን ጠጅ የተሞላ አቍማዳ በአህያ አስጭኖ፣ የፍየል ጠቦትም አስይዞ ልጁን ዳዊትን ወደ ሳኦል ላከው።

21ዳዊት ወደ ሳኦል መጥቶ አገልግሎቱን ጀመረ፤ ሳኦልም እጅግ ወደደው፣ እርሱም የሳኦል ጋሻ ጃግሬ ሆነ። 22ከዚያም ሳኦል፣ “ዳዊትን ወድጄዋለሁና ከእኔ ዘንድ ሆኖ እንዲያገለግለኝ ፍቀድልኝ” ብሎ ወደ እሴይ ላከ።

23ክፉው መንፈስ ከእግዚአብሔር ዘንድ በሳኦል ላይ በሚመጣበት ጊዜ፣ ዳዊት በገናውን ይዞ ይደረድር ነበር፤ ሳኦልም ይሻለው ነበር፤ ክፉውም መንፈስ ከእርሱ ይርቅ ነበር።

Persian Contemporary Bible

اول سموئيل 16:1-23

داوود به پادشاهی انتخاب می‌شود

1سرانجام خداوند به سموئيل فرمود: «بيش از اين برای شائول عزا نگير، چون من او را از سلطنت اسرائيل بركنار كرده‌ام. حال، يک ظرف روغن زيتون بردار و به خانهٔ يسی بيت‌لحمی برو، زيرا يكی از پسران او را برگزيده‌ام تا پادشاه اسرائيل باشد.»

2ولی سموئيل پرسيد: «چطور می‌توانم اين كار را بكنم؟ اگر شائول بشنود مرا می‌كشد!»

خداوند پاسخ داد: «گوساله‌ای با خود ببر و بگو آمده‌ای تا برای خداوند قربانی كنی. 3بعد يسی را به قربانگاه دعوت كن، آنگاه به تو نشان خواهم داد كه كدام يک از پسرانش را بايد برای پادشاهی تدهين كنی.»

4سموئيل طبق دستور خداوند عمل كرد. وقتی به بيت‌لحم رسيد، بزرگان شهر با ترس و لرز به استقبالش آمدند و پرسيدند: «چه اتفاقی افتاده است؟»

5سموئيل جواب داد: «نترسيد، هيچ اتفاق بدی نيفتاده است. آمده‌ام تا برای خداوند قربانی كنم. خود را تقديس كنيد و همراه من برای قربانی كردن بياييد.» او به يسی و پسرانش نيز دستور داد خود را تقديس كنند و به قربانگاه بيايند.

6وقتی پسران يسی آمدند، سموئيل چشمش به الياب افتاد و فكر كرد او همان كسی است كه خداوند برگزيده است. 7اما خداوند به سموئيل فرمود: «به چهرهٔ او و بلندی قدش نگاه نكن، زيرا او آن كسی نيست كه من در نظر گرفته‌ام. من مثل انسان قضاوت نمی‌كنم. انسان به ظاهر نگاه می‌كند، اما من به دل.»

8پس يسی ابيناداب را نزد سموئيل خواند. خداوند فرمود: «او نيز شخص مورد نظر نيست.» 9بعد يسی شمعا را احضار نمود، اما خداوند فرمود: «اين هم آنكه من می‌خواهم نيست.» 10‏-11به همين ترتيب يسی هفت پسرش را احضار نمود و همه رد شدند.

سموئيل به يسی گفت: «خداوند هيچيک از اينها را برنگزيده است. آيا تمام پسرانت اينها هستند؟»

يسی پاسخ داد: «يكی ديگر هم دارم كه از همه كوچكتر است. اما او در صحرا مشغول چرانيدن گوسفندان است.»

سموئيل گفت: «فوری كسی را بفرست تا او را بياورد چون تا او نيايد ما سر سفره نخواهيم نشست.»

12پس يسی فرستاد و او را آوردند. او پسری شاداب و خوش‌قيافه بود و چشمانی زيبا داشت. خداوند فرمود: «اين همان كسی است كه من برگزيده‌ام. او را تدهين كن.» 13سموئيل ظرف روغن زيتون را كه با خود آورده بود برداشت و بر سر داوود كه در ميان برادرانش ايستاده بود، ريخت. روح خداوند بر او نازل شد و از آن روز به بعد بر او قرار داشت. سپس سموئيل به خانهٔ خود در رامه بازگشت.

داوود در خدمت شائول

14روح خداوند از شائول دور شد و به جای آن روح پليد از جانب خداوند او را سخت عذاب می‌داد. 15‏-16بعضی از افراد شائول به او گفتند: «اگر اجازه دهی، نوازنده‌ای كه در نواختن چنگ ماهر باشد پيدا كنيم تا هر وقت روح پليد تو را آزار می‌دهد، برايت چنگ بنوازد و تو را آرامش دهد.»

17شائول گفت: «بسيار خوب، نوازندهٔ ماهری پيدا كنيد و نزد من بياوريد.»

18يكی از افرادش گفت: «پسر يسی بيت‌لحمی خيلی خوب می‌نوازد. در ضمن جوانی است شجاع و جنگاور. او خوش‌بيان و خوش‌قيافه است، و خداوند با او می‌باشد.»

19شائول قاصدانی به خانهٔ يسی فرستاد تا داوود چوپان را نزد وی ببرند. 20يسی يک بار الاغ نان و يک مشک شراب و يک بزغاله همراه داوود نزد شائول فرستاد.

21شائول وقتی چشمش به داوود افتاد از او خوشش آمد و داوود يكی از محافظان مخصوص شائول شد. 22پس شائول برای يسی پيغام فرستاده، گفت: «بگذار داوود پيش من بماند، چون از او خوشم آمده است.»

23هر وقت آن روح پليد از جانب خدا شائول را آزار می‌داد، داوود برايش چنگ می‌نواخت و روح بد از او دور می‌شد و او احساس آرامش می‌كرد.