1 ሳሙኤል 15 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

1 ሳሙኤል 15:1-35

እግዚአብሔር የሳኦልን ንጉሥነት መናቁ

1ሳሙኤል ሳኦልን እንዲህ አለው፤ “በሕዝቡ በእስራኤል ላይ ቀብቼ እንዳነግሥህ፣ እግዚአብሔር የላከው እኔን ነው፤ ስለዚህ ከእግዚአብሔር የመጣውን መልእክት አድምጥ። 2የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘እስራኤል ከግብፅ በወጣ ጊዜ፣ አማሌቃውያን በመንገድ ላይ ስለ ተቃወሙት እቀጣቸዋለሁ። 3አሁንም ሂድ፤ አማሌቃውያንን ውጋ፤ ያላቸውንም ሁሉ ፈጽመህ አጥፋ፤ አንዱንም አታስቀር፤ ወንዱንና ሴቱን፣ ልጁንና ሕፃኑን፣ የቀንድ ከብቱንና በጉን፣ ግመሉንና አህያውን ግደል።’ ”15፥3 በዚህም ሆነ በቍጥር 8፡9፡15፡18፡20 እና 21 ላይ የዕብራይስጡ ቃል አንድን ሰው ወይም ነገር ሙሉ በሙሉ በማጥፋት ለእግዚአብሔር መስጠትን የሚያሳይ ነው።

4ስለዚህ ሳኦል ሰዎቹን ጥላኢም በተባለ ቦታ ሰብስቦ ቈጠራቸው፤ እነርሱም ሁለት መቶ ሺሕ እግረኛ ወታደሮችና ከይሁዳም ዐሥር ሺሕ ሰዎች ነበሩ፤ 5ሳኦልም ወደ አማሌቅ ከተማ ሄዶ በአንዲት ሸለቆ ውስጥ አደፈጠ። 6እርሱም፣ ቄናውያንን፣ “ከእነርሱ ጋር እንዳላጠፋችሁ ከአማሌቃውያን ራቁ፤ ተለዩአቸውም፤ እስራኤላውያን ከግብፅ ምድር በወጡ ጊዜ፣ ቸርነት አድርጋችሁላቸዋልና” አላቸው። ስለዚህ ቄናውያን ከአማሌቃውያን ተለዩ።

7ከዚያም ሳኦል አማሌቃውያንን ከኤውላጥ አንሥቶ በምሥራቅ ግብፅ እስካለው እስከ ሱር ድረስ ወጋቸው። 8የአማሌቃውያንን ንጉሥ አጋግን ከነሕይወቱ ማረከው፤ ሕዝቡን ሁሉ በሰይፍ ስለት ፈጽሞ አጠፋቸው። 9ነገር ግን ሳኦልና ሰራዊቱ አጋግን፣ ምርጥ ምርጡን በግና የቀንድ ከብት፣ የሰባውን ጥጃና15፥9 ወይም ያደገ ጥጃ የዚህ ሐረግ የዕብራይስጡ ትርጕም በትክክል አይታወቅም። ጠቦት፣ መልካም የሆነውን ሁሉ ሳይገድሉ ተውት። እነዚህን ፈጽመው ለማጥፋት ፈቃደኞች አልነበሩም፤ ነገር ግን የተናቀውንና የማይጠቅመውን ሁሉ አጠፉ።

10ከዚህ በኋላ የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል ወደ ሳሙኤል መጣ፤ 11“ሳኦልን በማንገሤ ተጸጽቻለሁ፤ እኔን ከመከተል ተመልሷልና፣ ትእዛዜንም አልፈጸመምና።” ሳሙኤልም እጅግ ተጨንቆ፣ ሌሊቱን ሁሉ ወደ እግዚአብሔር ጮኸ።

12ሳሙኤልም ጧት ተነሥቶ በማለዳ ሳኦልን ለመገናኘት ሄደ፤ ነገር ግን፣ “ሳኦል ወደ ቀርሜሎስ ሄዷል፤ ለራሱ ክብር የመታሰቢያ ሐውልት በዚያ ካቆመ በኋላ ተመልሶ ወደ ጌልገላ ወርዷል” ተብሎ ተነገረው።

13ሳሙኤል ባገኘው ጊዜ ሳኦል፣ “እግዚአብሔር ይባርክህ፤ የእግዚአብሔርን ትእዛዝ ፈጽሜአለሁ” አለው።

14ሳሙኤል ግን፣ “ታዲያ ይህ በጆሮዬ የምሰማው የበጎች ጩኸትና የበሬዎች ግሣት ምንድን ነው?” ሲል ጠየቀ።

15ሳኦልም፣ “ሰራዊቱ ከአማሌቃውያን ማርከው ያመጧቸው ናቸው፤ ምርጥ ምርጦቹ በጎችና በሬዎች ለእግዚአብሔር ለአምላክህ መሥዋዕት እንዲሆኑ ሳይገድሉ የተዉአቸው ናቸው፤ የቀሩትን ግን በሙሉ አጥፍተናል” ብሎ መለሰ።

16ሳሙኤልም ሳኦልን፣ “ስማ! ትናንት ማታ እግዚአብሔር የነገረኝን ልንገርህ?” አለው።

ሳኦልም፣ “ንገረኝ” ሲል መለሰለት።

17ሳሙኤልም እንዲህ አለው፤ “በዐይንህ ፊት ታናሽ የነበርህ ብትሆንም፣ የእስራኤል ነገዶች መሪ ሆነህ የለምን? እግዚአብሔርም በእስራኤል ላይ ቀብቶ አንግሦሃል። 18እግዚአብሔርም፣ ‘ሄደህ እነዚያን ኀጢአተኞቹን አማሌቃውያንን ፈጽመህ አጥፋቸው፤ ጨርሰህ እስክታጠፋቸውም ድረስ ውጋቸው’ ብሎ ልኮህ ነበር። 19ታዲያ እግዚአብሔርን ለምን አልታዘዝህም? ለምርኮውስ ተስገብግበህ በእግዚአብሔር ፊት ክፉ የሆነውን ነገር ለምን አደረግህ?”

20ሳኦልም መልሶ እንዲህ አለ፤ “እግዚአብሔርን ታዝዣለሁ፤ እግዚአብሔር በላከኝ መሠረት ሄጃለሁ፤ አማሌቃውያንን በሙሉ አጥፍቼ ንጉሣቸውን አጋግን አምጥቻለሁ። 21ሰራዊቱ ግን ከምርኮው ለእግዚአብሔር ከተለዩት መካከል፣ ምርጥ ምርጡን በግና በሬ፣ በጌልገላ ለአምላክህ ለእግዚአብሔር ይሠዉ ዘንድ ወስደዋል።”

22ሳሙኤልም እንዲህ አለ፤

“ለእግዚአብሔር ቃል በመታዘዝ ደስ የሚለውን ያህል፣ እግዚአብሔር

በሚቃጠል ቍርባንና መሥዋዕት ደስ ይለዋልን?

እነሆ! መታዘዝ ከመሥዋዕት፣

ማዳመጥም ከአውራ በግ ሥብ ይበልጣል።

23ዐመፅ እንደ ጥንቈላ ያለ ኀጢአት፣

እልኸኝነትም እንደ ጣዖት አምልኮ ያለ ክፉ ነገር ነው። አንተ የእግዚአብሔርን ቃል ስለ ናቅህ፣ እርሱም ንጉሥ እንዳትሆን ንቆሃል።”

24ከዚያም ሳኦል ሳሙኤልን እንዲህ አለው፤ “ኀጢአት ሠርቻለሁ፤ የእግዚአብሔርን ትእዛዝና የአንተን መመሪያ ጥሻለሁ፤ ሕዝቡን ፈርቼ ስለ ነበር፣ የጠየቁኝን ታዝዣለሁ። 25አሁንም፣ ኀጢአቴን ይቅር እንድትለኝ፣ ለእግዚአብሔርም እሰግድ ዘንድ አብረኸኝ እንድትመለስ እለምንሃለሁ።”

26ሳሙኤል ግን፣ “ከአንተ ጋር አልመለስም፤ አንተ የእግዚአብሔርን ቃል ንቀሃል፤ እግዚአብሔርም በእስራኤል ላይ ንጉሥ እንዳትሆን ንቆሃል” አለው።

27ሳሙኤል ለመሄድ ዘወር ባለ ጊዜ፣ ሳኦል የልብሱን ጫፍ ያዘ፤ ተቀደደም። 28ሳሙኤልም እንዲህ አለው፤ “እግዚአብሔር የእስራኤልን መንግሥት ዛሬ ከአንተ ቀዶታል፤ ከአንተም ለሚሻል ለጎረቤትህ አሳልፎ ሰጥቶታል። 29የእስራኤል ክብር የሆነው እግዚአብሔር አይዋሽም፤ አይጸጸትምም፤ እርሱ ይጸጸት ዘንድ ሰው አይደለምና።”

30ሳኦልም መልሶ፣ “ኀጢአት ሠርቻለሁ፤ ነገር ግን በሕዝቤ አለቆች ፊትና በእስራኤል ፊት አክብረኝ፤ ለአምላክህ ለእግዚአብሔር እሰግድ ዘንድ እባክህ አብረኸኝ ተመለስ” አለው። 31ስለዚህ ሳሙኤል አብሮት ተመለሰ፤ ሳኦልም ለእግዚአብሔር ሰገደ።

32ከዚያም ሳሙኤል፣ “የአማሌቃውያንን ንጉሥ አጋግን አምጡልኝ” አለ።

አጋግም፣ “በውኑ ሞት እንዲህ መራራ ነውን?” በማለት እየተንቀጠቀጠ መጣ።

33ሳሙኤልም፣

“ሰይፍህ ሴቶችን ልጅ አልባ እንዳደረገቻቸው፣

እናትህም በሴቶች መካከል ልጅ አልባ ትሆናለች”

ሲል አጋግን ጌልገላ ላይ በእግዚአብሔር ፊት ቈራረጠው።

34ከዚያም ሳሙኤል ወደ አርማቴም ሄደ። ሳኦል ግን ወደ ቤቱ ወደ ሳኦል ጊብዓ ወጣ። 35ሳሙኤል ለሳኦል ቢያለቅስለትም እንኳ እስከ ሞተበት ዕለት ድረስ ዳግመኛ ሊያየው አልሄደም፤ እግዚአብሔርም ሳኦልን በእስራኤል ላይ በማንገሡ ተጸጸተ።

Thai New Contemporary Bible

1ซามูเอล 15:1-35

ซาอูลถูกถอดจากการเป็นกษัตริย์

1ซามูเอลกล่าวกับซาอูลว่า “องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงใช้ข้าพเจ้ามาเจิมตั้งท่านเป็นกษัตริย์แห่งอิสราเอลประชากรของพระองค์ ฉะนั้นบัดนี้จงฟังพระดำรัสจากองค์พระผู้เป็นเจ้า 2องค์พระผู้เป็นเจ้าผู้ทรงฤทธิ์ตรัสว่า ‘เราจะลงโทษชาวอามาเลขที่ดักเล่นงานอิสราเอลตอนที่ออกมาจากอียิปต์ 3บัดนี้จงออกไปโจมตีชาวอามาเลขและทำลายล้าง15:3 คำนี้ในภาษาฮีบรูหมายถึงสิ่งของหรือบุคคลที่ถวายแด่องค์พระผู้เป็นเจ้าแล้วไม่อาจเรียกคืนได้ มักจะต้องทำลายให้หมดสิ้นไป เช่นเดียวกับข้อ 8,9,15,18,20 และ 21ทุกสิ่งที่เขามีให้หมดสิ้น ไม่ว่าผู้ชาย ผู้หญิง เด็ก ทารก วัว แกะ อูฐ และลา อย่าไว้ชีวิตเลย’”

4ซาอูลจึงระดมพลและตรวจพลที่เทลาอิม มีกำลังทหารราบสองแสนคนสมทบกับกำลังพลจากยูดาห์หนึ่งหมื่นคน 5ซาอูลยกทัพไปยังเมืองของชาวอามาเลขและซุ่มอยู่ในหุบเขา 6เขากล่าวกับชาวเคไนต์ว่า “จงออกไปจากหมู่บ้านของชาวอามาเลข ท่านจะได้ไม่ถูกทำลายล้างไปพร้อมกับพวกเขา เนื่องจากท่านได้เมตตาชาวอิสราเอลตอนที่พวกเขาออกมาจากอียิปต์” ดังนั้นคนเคไนต์จึงย้ายออกจากชาวอามาเลขไป

7จากนั้นซาอูลก็โจมตีชาวอามาเลขตั้งแต่เมืองฮาวีลาห์ ตลอดทางถึงเมืองชูร์ฟากตะวันออกของอียิปต์ 8ซาอูลจับกุมอากักกษัตริย์ของชาวอามาเลข ส่วนคนอื่นๆ ถูกทำลายล้างด้วยคมดาบทั้งหมด 9แต่ซาอูลกับทหารได้ไว้ชีวิตอากัก และเก็บแกะ วัว ลูกแกะ และลูกวัวที่อ้วนท้วน15:9 หรือวัวผู้ที่โตเต็มที่แล้วในภาษาฮีบรูวลีนี้มีความหมายไม่ชัดเจนซึ่งดีที่สุดเอาไว้ เขาไม่อยากทำลายล้างสิ่งเหล่านี้ให้หมดสิ้น แต่ทำลายล้างเฉพาะสิ่งที่ไร้ค่าหรือไร้คุณภาพให้หมดสิ้นไป

10แล้วองค์พระผู้เป็นเจ้าจึงมีพระดำรัสมาถึงซามูเอลว่า 11“เราเสียใจที่ได้แต่งตั้งซาอูลเป็นกษัตริย์ เพราะเขาละทิ้งเรา ไม่ทำตามคำสั่งของเรา” ซามูเอลทุกข์ใจมากและคร่ำครวญต่อองค์พระผู้เป็นเจ้าตลอดคืน

12เช้าตรู่วันรุ่งขึ้นเขาออกไปหาซาอูล แต่มีคนบอกว่า “ซาอูลได้ไปที่คารเมลเพื่อสร้างอนุสาวรีย์เพื่อเป็นเกียรติแก่ตัวเอง และจากนั้นก็ไปที่กิลกาล”

13เมื่อซามูเอลมาถึง ซาอูลกล่าวว่า “ขอองค์พระผู้เป็นเจ้าทรงอวยพรท่าน ข้าพเจ้าได้ปฏิบัติตามพระบัญชาขององค์พระผู้เป็นเจ้าเรียบร้อยแล้ว”

14แต่ซามูเอลถามว่า “ถ้าอย่างนั้นเสียงร้องของแกะและวัวที่เราได้ยินนี้หมายถึงอะไร?”

15ซาอูลตอบว่า “พวกทหารได้ยึดสิ่งเหล่านั้นมาจากคนอามาเลข พวกเขาเก็บแกะและวัวที่ดีที่สุดไว้เพื่อถวายแด่พระยาห์เวห์พระเจ้าของท่าน แต่พวกเราได้ทำลายล้างสิ่งอื่นๆ จนหมด”

16ซามูเอลจึงกล่าวกับซาอูลว่า “หยุดเถอะ! จงฟังพระดำรัสขององค์พระผู้เป็นเจ้าที่มีมาถึงเราเมื่อคืนนี้”

ซาอูลตรัสว่า “จงบอกเถิด”

17ซามูเอลกล่าวว่า “แม้ท่านเคยคิดว่าตัวเองเล็กน้อยมาก แต่ท่านก็ได้เป็นผู้นำของเผ่าต่างๆ ของอิสราเอลไม่ใช่หรือ? องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงเจิมตั้งท่านเป็นกษัตริย์ปกครองอิสราเอล 18และพระองค์ทรงมอบหมายให้ท่านไปทำงานและตรัสว่า ‘จงออกไปสู้รบทำลายล้างชาวอามาเลขผู้ชั่วร้ายให้หมดสิ้น’ 19เหตุใดท่านจึงไม่เชื่อฟังองค์พระผู้เป็นเจ้า? ทำไมท่านจึงยึดของเชลยและทำสิ่งที่ชั่วในสายพระเนตรขององค์พระผู้เป็นเจ้า?”

20ซาอูลตรัสว่า “แต่ข้าพเจ้าได้เชื่อฟังองค์พระผู้เป็นเจ้าและทำงานตามที่องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงมอบหมาย ข้าพเจ้าได้นำตัวกษัตริย์อากักมา และได้ทำลายล้างชาวอามาเลขทั้งหมด 21แต่พวกทหารยึดแกะและวัวที่ดีที่สุดซึ่งเป็นของที่ต้องทำลายถวายแด่พระเจ้า มาถวายเป็นเครื่องบูชาแด่พระยาห์เวห์พระเจ้าของท่านที่กิลกาล”

22แต่ซามูเอลโต้ตอบว่า

องค์พระผู้เป็นเจ้าพอพระทัยในเครื่องเผาบูชาและเครื่องสัตวบูชา

ยิ่งกว่าการเชื่อฟังพระสุรเสียงขององค์พระผู้เป็นเจ้าหรือ?

การเชื่อฟังนั้นดียิ่งกว่าเครื่องบูชา

การสดับฟังก็ดีกว่าการถวายไขมันของแกะผู้

23เพราะการละเมิดฝ่าฝืนก็เป็นเหมือนบาปจากการเล่นไสยศาสตร์

และความหยิ่งทะนงก็เหมือนบาปจากการกราบไหว้รูปเคารพ

เนื่องจากท่านได้ละเลยพระดำรัสขององค์พระผู้เป็นเจ้า

พระองค์จึงทรงถอดท่านออกจากตำแหน่งกษัตริย์”

24แล้วซาอูลจึงกล่าวกับซามูเอลว่า “ข้าพเจ้าได้ทำบาปแล้ว ข้าพเจ้าได้ละเมิดพระบัญชาขององค์พระผู้เป็นเจ้าและคำสั่งของท่าน ข้าพเจ้ากลัวประชาชน จึงยอมทำตามพวกเขา 25โปรดอภัยบาปของข้าพเจ้าเถิด และขอกลับไปพร้อมกับข้าพเจ้า เพื่อข้าพเจ้าจะได้นมัสการองค์พระผู้เป็นเจ้า”

26แต่ซามูเอลตอบว่า “เราจะไม่กลับไปกับท่าน ท่านได้ทอดทิ้งพระดำรัสขององค์พระผู้เป็นเจ้าองค์พระผู้เป็นเจ้าทรงถอดท่านออกจากตำแหน่งกษัตริย์แห่งอิสราเอลแล้ว!”

27ขณะที่ซามูเอลจะกลับออกไป ซาอูลก็ดึงชายเสื้อคลุมของเขาไว้ ทำให้เสื้อขาด 28ซามูเอลกล่าวกับซาอูลว่า “ในวันนี้องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงฉีกอาณาจักรอิสราเอลจากท่าน และประทานให้ผู้อื่นซึ่งดีกว่าท่าน 29พระองค์ผู้ทรงเป็นเกียรติสิริแห่งอิสราเอลไม่ได้ตรัสมุสาหรือเปลี่ยนพระทัย เพราะพระองค์ไม่ใช่มนุษย์ที่จะเปลี่ยนใจ”

30ซาอูลตรัสว่า “ข้าพเจ้าได้ทำบาปแล้ว แต่ขอได้โปรดให้เกียรติข้าพเจ้าต่อหน้าบรรดาผู้อาวุโสของประชากรและต่อหน้าชาวอิสราเอล กลับไปกับข้าพเจ้าเถิด เพื่อข้าพเจ้าจะได้นมัสการพระยาห์เวห์พระเจ้าของท่าน” 31ซามูเอลจึงยอมกลับไปด้วย และซาอูลก็นมัสการองค์พระผู้เป็นเจ้า

32แล้วซามูเอลสั่งว่า “นำตัวอากักกษัตริย์ของอามาเลขมาหาเราสิ”

อากักก็ยิ้มย่องผ่องใสออกมา และ15:32 หรือตัวสั่นเทาออกมา แต่นึกในใจว่า “เคราะห์หามยามร้ายผ่านไปแล้ว เราคงรอดแน่ๆ”

33แต่ซามูเอลกล่าวว่า

“ดาบของท่านทำให้มารดาหลายคนสูญเสียบุตรไปฉันใด

มารดาของท่านจะสูญเสียบุตรฉันนั้น”

แล้วซามูเอลก็ประหารอากักต่อหน้าองค์พระผู้เป็นเจ้าที่กิลกาล

34จากนั้นซามูเอลจึงกลับไปรามาห์ ส่วนซาอูลก็กลับไปกิเบอาห์ที่พำนักของตน 35ตั้งแต่นั้นมาซามูเอลไม่เคยพบกับซาอูลอีกเลยจนกระทั่งสิ้นชีวิต เขาทุกข์โศกเนื่องด้วยซาอูลอยู่เสมอและองค์พระผู้เป็นเจ้าก็เสียพระทัยที่ได้ทรงตั้งซาอูลเป็นกษัตริย์แห่งอิสราเอล