1 ሳሙኤል 15 – NASV & NUB

New Amharic Standard Version

1 ሳሙኤል 15:1-35

እግዚአብሔር የሳኦልን ንጉሥነት መናቁ

1ሳሙኤል ሳኦልን እንዲህ አለው፤ “በሕዝቡ በእስራኤል ላይ ቀብቼ እንዳነግሥህ፣ እግዚአብሔር የላከው እኔን ነው፤ ስለዚህ ከእግዚአብሔር የመጣውን መልእክት አድምጥ። 2የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘እስራኤል ከግብፅ በወጣ ጊዜ፣ አማሌቃውያን በመንገድ ላይ ስለ ተቃወሙት እቀጣቸዋለሁ። 3አሁንም ሂድ፤ አማሌቃውያንን ውጋ፤ ያላቸውንም ሁሉ ፈጽመህ አጥፋ፤ አንዱንም አታስቀር፤ ወንዱንና ሴቱን፣ ልጁንና ሕፃኑን፣ የቀንድ ከብቱንና በጉን፣ ግመሉንና አህያውን ግደል።’ ”15፥3 በዚህም ሆነ በቍጥር 8፡9፡15፡18፡20 እና 21 ላይ የዕብራይስጡ ቃል አንድን ሰው ወይም ነገር ሙሉ በሙሉ በማጥፋት ለእግዚአብሔር መስጠትን የሚያሳይ ነው።

4ስለዚህ ሳኦል ሰዎቹን ጥላኢም በተባለ ቦታ ሰብስቦ ቈጠራቸው፤ እነርሱም ሁለት መቶ ሺሕ እግረኛ ወታደሮችና ከይሁዳም ዐሥር ሺሕ ሰዎች ነበሩ፤ 5ሳኦልም ወደ አማሌቅ ከተማ ሄዶ በአንዲት ሸለቆ ውስጥ አደፈጠ። 6እርሱም፣ ቄናውያንን፣ “ከእነርሱ ጋር እንዳላጠፋችሁ ከአማሌቃውያን ራቁ፤ ተለዩአቸውም፤ እስራኤላውያን ከግብፅ ምድር በወጡ ጊዜ፣ ቸርነት አድርጋችሁላቸዋልና” አላቸው። ስለዚህ ቄናውያን ከአማሌቃውያን ተለዩ።

7ከዚያም ሳኦል አማሌቃውያንን ከኤውላጥ አንሥቶ በምሥራቅ ግብፅ እስካለው እስከ ሱር ድረስ ወጋቸው። 8የአማሌቃውያንን ንጉሥ አጋግን ከነሕይወቱ ማረከው፤ ሕዝቡን ሁሉ በሰይፍ ስለት ፈጽሞ አጠፋቸው። 9ነገር ግን ሳኦልና ሰራዊቱ አጋግን፣ ምርጥ ምርጡን በግና የቀንድ ከብት፣ የሰባውን ጥጃና15፥9 ወይም ያደገ ጥጃ የዚህ ሐረግ የዕብራይስጡ ትርጕም በትክክል አይታወቅም። ጠቦት፣ መልካም የሆነውን ሁሉ ሳይገድሉ ተውት። እነዚህን ፈጽመው ለማጥፋት ፈቃደኞች አልነበሩም፤ ነገር ግን የተናቀውንና የማይጠቅመውን ሁሉ አጠፉ።

10ከዚህ በኋላ የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል ወደ ሳሙኤል መጣ፤ 11“ሳኦልን በማንገሤ ተጸጽቻለሁ፤ እኔን ከመከተል ተመልሷልና፣ ትእዛዜንም አልፈጸመምና።” ሳሙኤልም እጅግ ተጨንቆ፣ ሌሊቱን ሁሉ ወደ እግዚአብሔር ጮኸ።

12ሳሙኤልም ጧት ተነሥቶ በማለዳ ሳኦልን ለመገናኘት ሄደ፤ ነገር ግን፣ “ሳኦል ወደ ቀርሜሎስ ሄዷል፤ ለራሱ ክብር የመታሰቢያ ሐውልት በዚያ ካቆመ በኋላ ተመልሶ ወደ ጌልገላ ወርዷል” ተብሎ ተነገረው።

13ሳሙኤል ባገኘው ጊዜ ሳኦል፣ “እግዚአብሔር ይባርክህ፤ የእግዚአብሔርን ትእዛዝ ፈጽሜአለሁ” አለው።

14ሳሙኤል ግን፣ “ታዲያ ይህ በጆሮዬ የምሰማው የበጎች ጩኸትና የበሬዎች ግሣት ምንድን ነው?” ሲል ጠየቀ።

15ሳኦልም፣ “ሰራዊቱ ከአማሌቃውያን ማርከው ያመጧቸው ናቸው፤ ምርጥ ምርጦቹ በጎችና በሬዎች ለእግዚአብሔር ለአምላክህ መሥዋዕት እንዲሆኑ ሳይገድሉ የተዉአቸው ናቸው፤ የቀሩትን ግን በሙሉ አጥፍተናል” ብሎ መለሰ።

16ሳሙኤልም ሳኦልን፣ “ስማ! ትናንት ማታ እግዚአብሔር የነገረኝን ልንገርህ?” አለው።

ሳኦልም፣ “ንገረኝ” ሲል መለሰለት።

17ሳሙኤልም እንዲህ አለው፤ “በዐይንህ ፊት ታናሽ የነበርህ ብትሆንም፣ የእስራኤል ነገዶች መሪ ሆነህ የለምን? እግዚአብሔርም በእስራኤል ላይ ቀብቶ አንግሦሃል። 18እግዚአብሔርም፣ ‘ሄደህ እነዚያን ኀጢአተኞቹን አማሌቃውያንን ፈጽመህ አጥፋቸው፤ ጨርሰህ እስክታጠፋቸውም ድረስ ውጋቸው’ ብሎ ልኮህ ነበር። 19ታዲያ እግዚአብሔርን ለምን አልታዘዝህም? ለምርኮውስ ተስገብግበህ በእግዚአብሔር ፊት ክፉ የሆነውን ነገር ለምን አደረግህ?”

20ሳኦልም መልሶ እንዲህ አለ፤ “እግዚአብሔርን ታዝዣለሁ፤ እግዚአብሔር በላከኝ መሠረት ሄጃለሁ፤ አማሌቃውያንን በሙሉ አጥፍቼ ንጉሣቸውን አጋግን አምጥቻለሁ። 21ሰራዊቱ ግን ከምርኮው ለእግዚአብሔር ከተለዩት መካከል፣ ምርጥ ምርጡን በግና በሬ፣ በጌልገላ ለአምላክህ ለእግዚአብሔር ይሠዉ ዘንድ ወስደዋል።”

22ሳሙኤልም እንዲህ አለ፤

“ለእግዚአብሔር ቃል በመታዘዝ ደስ የሚለውን ያህል፣ እግዚአብሔር

በሚቃጠል ቍርባንና መሥዋዕት ደስ ይለዋልን?

እነሆ! መታዘዝ ከመሥዋዕት፣

ማዳመጥም ከአውራ በግ ሥብ ይበልጣል።

23ዐመፅ እንደ ጥንቈላ ያለ ኀጢአት፣

እልኸኝነትም እንደ ጣዖት አምልኮ ያለ ክፉ ነገር ነው። አንተ የእግዚአብሔርን ቃል ስለ ናቅህ፣ እርሱም ንጉሥ እንዳትሆን ንቆሃል።”

24ከዚያም ሳኦል ሳሙኤልን እንዲህ አለው፤ “ኀጢአት ሠርቻለሁ፤ የእግዚአብሔርን ትእዛዝና የአንተን መመሪያ ጥሻለሁ፤ ሕዝቡን ፈርቼ ስለ ነበር፣ የጠየቁኝን ታዝዣለሁ። 25አሁንም፣ ኀጢአቴን ይቅር እንድትለኝ፣ ለእግዚአብሔርም እሰግድ ዘንድ አብረኸኝ እንድትመለስ እለምንሃለሁ።”

26ሳሙኤል ግን፣ “ከአንተ ጋር አልመለስም፤ አንተ የእግዚአብሔርን ቃል ንቀሃል፤ እግዚአብሔርም በእስራኤል ላይ ንጉሥ እንዳትሆን ንቆሃል” አለው።

27ሳሙኤል ለመሄድ ዘወር ባለ ጊዜ፣ ሳኦል የልብሱን ጫፍ ያዘ፤ ተቀደደም። 28ሳሙኤልም እንዲህ አለው፤ “እግዚአብሔር የእስራኤልን መንግሥት ዛሬ ከአንተ ቀዶታል፤ ከአንተም ለሚሻል ለጎረቤትህ አሳልፎ ሰጥቶታል። 29የእስራኤል ክብር የሆነው እግዚአብሔር አይዋሽም፤ አይጸጸትምም፤ እርሱ ይጸጸት ዘንድ ሰው አይደለምና።”

30ሳኦልም መልሶ፣ “ኀጢአት ሠርቻለሁ፤ ነገር ግን በሕዝቤ አለቆች ፊትና በእስራኤል ፊት አክብረኝ፤ ለአምላክህ ለእግዚአብሔር እሰግድ ዘንድ እባክህ አብረኸኝ ተመለስ” አለው። 31ስለዚህ ሳሙኤል አብሮት ተመለሰ፤ ሳኦልም ለእግዚአብሔር ሰገደ።

32ከዚያም ሳሙኤል፣ “የአማሌቃውያንን ንጉሥ አጋግን አምጡልኝ” አለ።

አጋግም፣ “በውኑ ሞት እንዲህ መራራ ነውን?” በማለት እየተንቀጠቀጠ መጣ።

33ሳሙኤልም፣

“ሰይፍህ ሴቶችን ልጅ አልባ እንዳደረገቻቸው፣

እናትህም በሴቶች መካከል ልጅ አልባ ትሆናለች”

ሲል አጋግን ጌልገላ ላይ በእግዚአብሔር ፊት ቈራረጠው።

34ከዚያም ሳሙኤል ወደ አርማቴም ሄደ። ሳኦል ግን ወደ ቤቱ ወደ ሳኦል ጊብዓ ወጣ። 35ሳሙኤል ለሳኦል ቢያለቅስለትም እንኳ እስከ ሞተበት ዕለት ድረስ ዳግመኛ ሊያየው አልሄደም፤ እግዚአብሔርም ሳኦልን በእስራኤል ላይ በማንገሡ ተጸጸተ።

Swedish Contemporary Bible

1 Samuelsboken 15:1-35

Saul tar krigsbyte mot Herrens vilja

1Samuel sa till Saul: ”Det var mig som Herren sände att smörja dig till kung över Israel, så lyssna nu vad Herren säger! 2Så säger härskarornas Herre: ’Jag ska straffa Amalek för det de gjorde mot Israel då de anföll dem på vägen från Egypten.15:2 Se 2 Mos 17:8-16. 3Gå nu och vig hela Amaleks folk och allt de har åt förintelse. Utrota män, kvinnor, barn, ungdomar, oxar, får, kameler och åsnor!’ ” 4Saul mobiliserade sin armé och mönstrade dem i Telaim. Han hade 200 000 soldater och dessutom 10 000 man från Juda.

5När Saul kom till Amaleks stad, lade han sig i bakhåll i dalen. 6Sedan skickade han bud till keniterna att dra sig bort och överge amalekiterna. ”Jag vill inte utrota er tillsammans med dem. Ni var ju vänliga mot Israels folk, när de kom från Egypten”, sa han. Keniterna drog sig då bort därifrån. 7Sedan slog Saul amalekiterna ända från Havila och ner till Shur, öster om Egypten. 8Han tillfångatog Agag, amalekiternas kung, men vigde alla andra åt förintelse och högg ner dem med svärd. 9Saul och hans män skonade alltså Agag, men också det bästa av fåren och oxarna och de fetaste lammen, kort sagt allt som var värdefullt. De ville inte viga det åt förintelse, utan gjorde det bara med det som var svagt och värdelöst.

Herren förkastar Saul

10Då kom Herrens ord till Samuel: 11”Jag ångrar att jag gjorde Saul till kung, för han har än en gång vänt sig bort från mig och vägrat att lyda mig.” Samuel blev djupt skakad och han ropade och bad till Herren hela natten. 12Tidigt nästa morgon gick han ut för att leta efter Saul, men fick höra att han hade gått till berget Karmel för att resa ett monument över sig själv och att han därefter hade fortsatt till Gilgal.

13När Samuel kom, hälsade Saul och sa: ”Herren välsigne dig! Nu har jag verkställt Herrens befallning!”

14”Vad är det då för ett bräkande av får och bölande av oxar jag hör?” frågade Samuel. 15”Mina soldater räddade det bästa av amalekiternas får och oxar”, erkände Saul, ”men det var för att offra dem till Herren, din Gud. Allt annat har vi vigt åt förintelse.”

16Då sa Samuel till Saul: ”Sluta! Hör nu vad Herren sa till mig i natt!” ”Vad sa han?” undrade Saul.

17Samuel svarade: ”När du själv inte tyckte att du var något, blev du ledare för Israels stammar och Herren smorde dig till kung över Israel. 18Och han gav dig ett uppdrag och sa till dig: ’Gå och vig de syndiga amalekiterna åt förintelse. Strid mot dem tills du utplånat dem alla!’ 19Varför lydde du inte Herren? Varför kastade du dig över krigsbytet och gjorde det som är ont i Herrens ögon?”

20”Men jag har lytt Herren”, svarade Saul. ”Jag gick dit han sa till mig att gå. Jag tog med mig kung Agag, men jag vigde alla de andra åt förintelse. 21Och mina trupper behöll fåren och oxarna, det allra bästa av det som skulle vigas åt förintelse, för att offra det till Herren.”

22Samuel svarade:

”Gläder sig Herren lika mycket åt brännoffer och slaktoffer

som att man hör Herrens röst?

Nej, lydnad är bättre än offer,

och att lyssna till honom är bättre

än att offra baggars fett åt honom.

23Upproriskhet är en lika stor synd som spådom,

och övermod lika avigt som att tillbe avgudar.

Du har förkastat Herrens ord,

och han har förkastat dig som kung.”

Saul ber om nåd

24”Jag har syndat”, sa Saul till Samuel. ”Jag var olydig mot Herrens befallning och handlade inte efter dina ord, för jag var rädd för folket och gjorde vad de krävde. 25Förlåt nu min synd och följ med mig tillbaka, så att jag kan tillbe Herren!” 26Men Samuel svarade: ”Jag kommer inte tillbaka med dig. Eftersom du har förkastat Herrens befallning, har han också förkastat dig som kung över Israel.” 27När Samuel sedan vände sig om för att gå, grep Saul tag i hans mantel, men då revs manteln sönder. 28”Se”, sa Samuel, ”Herren har ryckt Israels rike ifrån dig i dag och gett det till en av dina landsmän, till en som är bättre än du. 29Han som är Israels härlighet ljuger inte och inte heller ångrar han sig, för han är inte en människa.”

30Då sa Saul: ”Jag har syndat, men hedra mig åtminstone inför mitt folks äldste och Israel genom att gå med mig och tillbe Herren, din Gud!” 31Samuel gick då med honom och Saul tillbad Herren.

32Sedan sa Samuel: ”För hit amalekiternas kung Agag!” Agag kom darrande15:32 Det hebreiska ordets betydelse är osäker och kan tolkas på olika sätt: darrande, med vacklande steg, eller leende, självsäkert, eller i bojor. Kanske hoppades han att de skulle låta honom få leva, eller att döden skulle bli snabb. Enligt Septuaginta: Hur bitter är inte döden! fram men tänkte ändå: ”Dödens bitterhet är borta.” 33Men Samuel sa:

”På samma sätt som ditt svärd har gjort många mödrar barnlösa,

ska din mor nu bli barnlös.”

Och Samuel dödade honom inför Herren i Gilgal.

34Sedan gick Samuel hem till Rama och Saul återvände till Sauls Giva. 35Efter den dagen träffade Samuel aldrig Saul mer, men han tänkte ofta med sorg på honom och Herren sörjde över att han hade gjort Saul till kung över Israel.