ዳንኤል 5 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ዳንኤል 5:1-31

በግድግዳው ላይ የታየው ጽሕፈት

1ንጉሥ ቤልሻዛር ለሺሕ መኳንንቱ ታላቅ ግብዣ አደረገ፤ በሺሑም ፊት የወይን ጠጅ ይጠጣ ነበር። 2ቤልሻዛር የወይን ጠጁን እየጠጣ ሳለ፣ አባቱ5፥2 ወይም አያት፤ ወይም ቀዳሚ ዘር እንዲሁም 11፡13 እና 18 ናቡከደነፆር ከኢየሩሳሌም ቤተ መቅደስ ያመጣቸውን የወርቅና የብር መጠጫዎችን እርሱና መኳንንቱ፣ ሚስቶቹና ቍባቶቹ ይጠጡባቸው ዘንድ እንዲያመጡለት አዘዘ። 3ከዚያም በኢየሩሳሌም ከነበረው ከእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ የተወሰዱትን የወርቅ መጠጫዎች አመጡ፤ ንጉሡና መኳንንቱ፣ ሚስቶቹና ቍባቶቹም ጠጡባቸው። 4የወይን ጠጁንም እየጠጡ የወርቅና የብር፣ የናስ፣ የብረት፣ የዕንጨትና የድንጋይ አማልክትን አመሰገኑ።

5በድንገትም የሰው እጅ ጣቶች ታዩ፤ በቤተ መንግሥቱ ውስጥ በመቅረዙ ትይዩ ባለው ግድግዳ ልስን ላይ ጻፉ፤ ንጉሡም ይጽፍ የነበረውን እጅ አየ፤ 6በዚያን ጊዜ ንጉሡ በድንጋጤ ተሞላ፤ ፊቱም ተለዋወጠ፤ እጆቹና እግሮቹ ከዱት፤ ጕልበቶቹም ተብረከረኩ።

7ንጉሡም ድምፁን ከፍ አድርጎ አስማተኞችን፣ ኮከብ ቈጣሪዎችንና5፥7 ወይም ከለዳውያን፤ እንዲሁም 11 መተተኞችን እንዲያስገቡለት አዘዘ፤ ለባቢሎናውያኑ ጠቢባን እንዲህ አላቸው፤ “ይህን ጽሕፈት አንብቦ ትርጕሙን የሚነግረኝን ሐምራዊ መጐናጸፊያ አለብሰዋለሁ፤ የወርቅ ሐብልም በዐንገቱ ላይ አጠልቅለታለሁ፤ በመንግሥቴም ላይ ሦስተኛ ገዥ ይሆናል።”

8ከዚያም የንጉሡ ጠቢባን ሁሉ ገቡ፤ ነገር ግን ጽሕፈቱን ሊያነብም ሆነ ትርጕሙ ምን እንደ ሆነ ለንጉሡ ሊነግር የሚችል ማንም አልነበረም። 9ንጉሥ ቤልሻዛር ከፊት ይልቅ ፈራ፤ ፊቱም እጅግ ተለወጠ፤ መኳንንቱም ግራ ገብቷቸው ተደናገጡ።

10ንግሥቲቱም5፥10 ወይም የንጉሡ እናት የንጉሡንና የመኳንንቱን ድምፅ ሰምታ ወደ ግብዣው አዳራሽ ገባች፤ እንዲህም አለች፤ “ንጉሥ ሆይ፤ ለዘላለም ንገሥ፤ አትደንግጥ፤ ፊትህም አይለዋወጥ! 11በመንግሥትህ ውስጥ የቅዱሳን አማልክት መንፈስ ያለበት አንድ ሰው አለ፤ ይህ ሰው በአባትህ ዘመን እንደ አማልክት ጥበብና ማስተዋል፣ ዕውቀትም የሞላበት ሆኖ ተገኝቷል፤ አባትህ ንጉሥ ናቡከደነፆርም የጠንቋዮች፣ የአስማተኞች፣ የኮከብ ቈጣሪዎችና የመተተኞች አለቃ አደረገው። 12ንጉሡ ብልጣሶር ብሎ የጠራው ይህ ዳንኤል መልካም መንፈስ፣ ዕውቀትና ማስተዋል ያለው ሆኖ ተገኘ፤ ሕልምን የመተርጐም፣ ዕንቈቅልሽን የመፍታትና የተሰወረውን የመግለጥ ልዩ ችሎታም ነበረው። ስለዚህ ዳንኤልን አስጠራ፤ እርሱም የጽሕፈቱን ትርጕም ይነግርሃል።”

13ዳንኤልንም ወደ ንጉሡ አቀረቡት፤ ንጉሡም እንዲህ አለው፤ “ንጉሡ አባቴ ከይሁዳ ማርኮ ካመጣቸው መካከል አንዱ የሆንኸው ዳንኤል አንተ ነህን? 14የአማልክት መንፈስ በውስጥህ እንዳለ፣ ዕውቀት፣ ማስተዋልና ልዩ ጥበብ እንዳለህ ሰምቻለሁ። 15ይህን ጽሕፈት አንብበው ትርጕሙ ምን እንደ ሆነ ይነግሩኝ ዘንድ ጠቢባንና አስማተኞች በፊቴ ቀርበው ነበር፤ ነገር ግን ሊገልጡት አልቻሉም። 16አንተ ግን መተርጐምና አስቸጋሪ የሆነውን ነገር መፍታት እንደምትችል ሰምቻለሁ። ይህን ጽሕፈት አንብበህ ትርጕሙን ብትነግረኝ፣ ሐምራዊ መጐናጸፊያ ያለብሱሃል፤ የወርቅ ሐብል በዐንገትህ ያጠልቁልሃል፤ የመንግሥት ሦስተኛ ገዥም ትደረጋለህ።”

17ዳንኤልም ለንጉሡ እንዲህ ሲል መለሰ፤ “ስጦታዎችህን ለራስህ አድርግ፤ ሽልማቶችህንም ለሌላ ሰው ስጥ፤ ይሁን እንጂ ጽሕፈቱን ለንጉሡ አነብባለሁ፤ ትርጕሙ ምን እንደ ሆነም እነግረዋለሁ።

18“ንጉሥ ሆይ፤ ልዑል አምላክ ለአባትህ ለናቡከደነፆር ገናናነትንና ታላቅነትን፣ ክብርንና ግርማን ሰጠው። 19ከሰጠው ታላቅ ሥልጣን የተነሣ ሕዝቦችና መንግሥታት፣ ልዩ ልዩ ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎችም ሁሉ ተንቀጠቀጡለት፤ ፈሩትም። ንጉሡም ሊገድል የፈለገውን ይገድል፣ ሊያድን የፈለገውን ያድን፣ ሊሾም የፈለገውን ይሾም፣ ሊያዋርድ የፈለገውንም ያዋርድ ነበር። 20ነገር ግን ልቡ በትዕቢት በጸናና በእብሪት በተሞላ ጊዜ ከዙፋኑ ተወገደ፤ ክብሩም ተገፈፈ። 21ከሰው መካከል ተሰደደ፤ የእንስሳም አእምሮ ተሰጠው፤ ከዱር አህዮች ጋር ኖረ፤ እንደ ከብትም ሣር በላ፤ ልዑል አምላክ በሰዎች መንግሥታት ላይ እንደሚገዛና እነርሱንም ለወደደው እንደሚሰጥ እስኪያውቅ ድረስ ሰውነቱ በሰማይ ጠል ረሰረሰ።

22“ቤልሻዛር ሆይ፤ አንተ ልጁ5፥22 ወይም ዘሩ ወይም ምትክ ሆነህ ይህን ሁሉ ብታውቅም፣ ራስህን ዝቅ አላደረግህም፤ 23ይልቁንም በሰማይ አምላክ ላይ በመታበይ፣ ራስህን ከፍ ከፍ አደረግህ፤ የመቅደሱን መጠጫዎች አስመጣህ፤ አንተና መኳንንትህ፣ ሚስቶችህና ቍባቶችህም የወይን ጠጅ ጠጣችሁባቸው፤ ማየት፣ መስማት፣ ማስተዋልም የማይችሉትን የብርና የወርቅ፣ የናስና የብረት፣ የዕንጨትና የድንጋይ አማልክትን አመሰገንህ። ሕይወትህንና መንገድህን ሁሉ በእጁ የያዘውን አምላክ ግን አላከበርህም። 24ስለዚህ እርሱ ጽሕፈቱን የጻፈውን እጅ ላከ።

25“የተጻፈውም ጽሕፈት፣

‘ማኔ፣ ማኔ፣ ቴቄል፣ ፋሬስ’5፥25 በአረማይክ ኢፋርሲን (ይኸውም ፋርሲንና ማለት ነው።) ይላል።

26“የቃሉም ትርጕም ይህ ነው፤

‘ማኔ’5፥26 ማኔ ማለት የተቍጠረ ወይም ምናን (ራሱን የቻለ አንድ የገንዘብ ክፍል) ማለት እግዚአብሔር የመንግሥትህን ዘመን ቈጠረው፤ ወደ ፍጻሜም አደረሰው ማለት ነው።

27‘ቴቄል’5፥27 ቴቄል ማለት የተመዘነ ወይም ሰቅል ሊሆን ይችላል። ማለት በሚዛን ተመዘንህ፤ ቀለህም ተገኘህ፣ ማለት ነው።

28‘ፋሬስ’5፥28 ፋሬስ የፋርሲን ነጠላ ቁጥር ሲሆን ተከፈለ ወይም ፐርሺያ ወይም የሰቅል እኩሌታ ማለት ሊሆን ይችላል። ማለት መንግሥትህ ተከፈለ፣ ለሜዶናውያንና ለፋርስ ሰዎች ተሰጠ ማለት ነው።”

29ከዚህ በኋላ በቤልሻዛር ትእዛዝ ዳንኤልን ሐምራዊ መጐናጸፊያ አለበሱት፣ የወርቅ ሐብል በዐንገቱ ላይ አጠለቁለት፤ የመንግሥቱም ሦስተኛ ገዥ ሆኖ ተሾመ።

30በዚያኑ ሌሊት የባቢሎናውያን5፥30 ወይም ከለዳውያን ንጉሥ ቤልሻዛር ተገደለ፤ 31የስድሳ ሁለት ዓመት ዕድሜ የነበረው ሜዶናዊው ዳርዮስም መንግሥቱን ወሰደ።

Thai New Contemporary Bible

ดาเนียล 5:1-31

ข้อความบนผนัง

1กษัตริย์เบลชัสซาร์ทรงจัดงานเลี้ยงใหญ่ประทานแก่ขุนนางผู้ใหญ่หนึ่งพันคน และทรงเสวยเหล้าองุ่นร่วมกับเขา 2ขณะเสวยอยู่ก็รับสั่งให้นำภาชนะเงินและทองคำซึ่งเนบูคัดเนสซาร์ราชบิดา5:2 หรือบรรพบุรุษเช่นเดียวกับข้อ 11,13 และ 18ได้ยึดมาจากพระวิหารในเยรูซาเล็มนั้นมาให้กษัตริย์ ขุนนาง มเหสี และเหล่านางสนมใส่เหล้าองุ่น 3พวกเขาจึงนำภาชนะทองคำซึ่งริบมาจากพระวิหารของพระเจ้าในเยรูซาเล็มมาให้กษัตริย์ ขุนนาง มเหสี และเหล่านางสนมใส่เหล้าองุ่นดื่ม 4พวกเขาดื่มพร้อมทั้งสรรเสริญเทพเจ้าที่ทำจากทองคำ เงิน ทองสัมฤทธิ์ เหล็ก ไม้ และหิน

5ทันใดนั้นมีนิ้วมือมนุษย์ปรากฏขึ้นและเขียนบนผนังใกล้คันประทีปในพระราชวัง กษัตริย์ทอดพระเนตรดูมือนั้นเขียนไป 6พระพักตร์ของพระองค์ก็ซีดเผือด ทรงตกพระทัยจนเข่าสั่นกระทบกัน แข้งขาอ่อนหมดเรี่ยวหมดแรง

7พระองค์ตรัสเรียกให้นำตัวนักเวทมนตร์ โหราจารย์5:7 หรือชาวเคลเดียเช่นเดียวกับข้อ 11 และหมอดูฤกษ์ยามทั้งหลายมา และตรัสแก่ปราชญ์ของบาบิโลนเหล่านี้ว่า “ผู้ใดก็ตามอ่านข้อความนี้แล้วบอกเราได้ว่ามีความหมายว่าอะไร เราจะให้ผู้นั้นสวมชุดสีม่วงกับสร้อยคอทองคำ และให้ครองอำนาจเป็นที่สามในราชอาณาจักร”

8แล้วปราชญ์ทั้งปวงของกษัตริย์ก็มาเข้าเฝ้า แต่ไม่มีใครสามารถอ่านข้อความที่เขียนไว้ หรือทูลให้กษัตริย์ทรงทราบว่าหมายความว่าอะไร 9ดังนั้นกษัตริย์เบลชัสซาร์จึงยิ่งตกพระทัย และพระพักตร์ยิ่งขาวซีด ขุนนางทั้งปวงก็ว้าวุ่นใจ

10พระราชินี5:10 หรือพระชนนีทรงได้ยินพระสุรเสียงของกษัตริย์และเสียงเหล่าขุนนาง ก็เสด็จเข้ามาในท้องพระโรงซึ่งมีงานเลี้ยงนั้น พระนางตรัสว่า “ข้าแต่กษัตริย์ ขอจงทรงพระเจริญ! อย่าตกพระทัยจนพระพักตร์ซีดเลย! 11มีชายผู้หนึ่งในราชอาณาจักรซึ่งมีวิญญาณของเทพเจ้าศักดิ์สิทธิ์สถิตด้วยในรัชสมัยของพระราชบิดา เราพบว่าชายคนนี้มีสติปัญญา ไหวพริบ และความหยั่งรู้เสมอเหมือนเทพเจ้า กษัตริย์เนบูคัดเนสซาร์ราชบิดาของพระองค์จึงทรงแต่งตั้งเขาให้เป็นหัวหน้านักเล่นอาคม นักเวทมนตร์ โหราจารย์ และหมอดูฤกษ์ยามทั้งปวง 12ดาเนียลผู้นี้ซึ่งกษัตริย์ตรัสเรียกว่าเบลเทชัสซาร์เป็นผู้มีปัญญาเฉียบแหลม มีความรู้ความเข้าใจ และยังสามารถทำนายฝันแก้ปริศนาและปัญหายุ่งยากทั้งหลาย ขอให้ตามตัวดาเนียลมาเถิด เขาจะสามารถกราบทูลว่าข้อความนี้หมายความว่าอะไร”

13ดาเนียลจึงถูกนำตัวมาเข้าเฝ้า กษัตริย์ตรัสกับเขาว่า “เจ้าคือดาเนียลเชลยที่ราชบิดาของเรานำตัวมาจากยูดาห์หรือ? 14เราได้ยินมาว่าวิญญาณของเทพเจ้าอยู่ในตัวเจ้า และเจ้ามีความหยั่งรู้ ไหวพริบ และสติปัญญาล้ำเลิศ 15เราได้เรียกบรรดาปราชญ์และนักเล่นอาคมให้มาอ่านข้อความนี้และแจ้งความหมายแก่เรา แต่พวกเขาอธิบายความไม่ได้ 16เราได้ยินมาว่าเจ้าสามารถอธิบายความและแก้ปริศนาอันซับซ้อนซ่อนเงื่อนได้ หากเจ้าสามารถอ่านข้อความนี้และบอกความหมายแก่เราได้ เราจะให้เจ้าสวมชุดสีม่วงและสวมสร้อยคอทองคำ แล้วแต่งตั้งให้เจ้าครองอำนาจเป็นที่สามในราชอาณาจักร”

17ดาเนียลจึงทูลกษัตริย์ว่า “ขอทรงเก็บของประทานไว้และปูนบำเหน็จแก่ผู้อื่นเถิด อย่างไรก็ดีข้าพระบาทจะอ่านข้อความถวายฝ่าพระบาทและทูลความหมายให้ทรงทราบ

18“ข้าแต่กษัตริย์ พระเจ้าสูงสุดได้ประทานราชอำนาจ ความยิ่งใหญ่ และเกียรติบารมีแก่เนบูคัดเนสซาร์ราชบิดาของฝ่าพระบาท 19เนื่องจากฐานะสูงส่งที่พระเจ้าประทานให้พระองค์ มวลประชาชาติและคนทุกภาษาจึงยำเกรงครั่นคร้ามพระองค์ ผู้ที่กษัตริย์ประสงค์ให้ประหารก็จะถูกประหาร ผู้ที่ทรงประสงค์ให้ไว้ชีวิตก็จะรอดชีวิต ทรงให้ยศถาบรรดาศักดิ์หรือถอดถอนผู้ใดตามแต่ชอบพระทัย 20แต่เมื่อพระทัยของพระองค์เย่อหยิ่งและกำเริบเสิบสาน พระเจ้าจึงทรงปลดพระองค์ออกจากราชบัลลังก์และริบเอาเกียรติบารมีของพระองค์ไป 21พระองค์ทรงถูกขับไล่จากมวลมนุษย์และได้รับความคิดจิตใจแบบสัตว์ ทรงใช้ชีวิตอยู่กับลาป่า กินหญ้าเหมือนวัว กายตากน้ำค้าง จนกระทั่งทรงเรียนรู้ว่าพระเจ้าสูงสุดทรงครอบครองเหนืออาณาจักรของมนุษย์ทั้งปวง และทรงตั้งผู้ใดก็ได้ตามแต่ชอบพระทัยให้ครองอาณาจักร

22“ข้าแต่เบลชัสซาร์ แต่ฝ่าพระบาทผู้เป็นโอรส5:22 หรือลูกหลานหรือผู้สืบเชื้อสายทรงทราบเรื่องทั้งหมดนี้ แต่ก็ไม่ได้ถ่อมพระทัยลง 23กลับยกองค์ลบหลู่องค์พระผู้เป็นเจ้าแห่งฟ้าสวรรค์ ทรงให้นำภาชนะจากพระวิหารของพระเจ้ามาให้ฝ่าพระบาท ขุนนาง มเหสี และเหล่านางสนมใส่เหล้าองุ่นดื่ม ทรงยกย่องสรรเสริญเทพเจ้าที่ทำจากเงิน ทอง ทองสัมฤทธิ์ เหล็ก ไม้ และหิน ซึ่งมองอะไรไม่เห็น ฟังอะไรไม่ได้ยิน และไม่เข้าใจ ฝ่าพระบาทไม่ได้เทิดพระเกียรติพระเจ้าผู้กุมชีวิตและวิถีทางทั้งปวงของฝ่าพระบาทไว้ในพระหัตถ์ 24ฉะนั้นพระเจ้าจึงทรงส่งมือมาเขียนข้อความนั้น

25“ข้อความนั้นเขียนไว้ว่า

เมเน เมเน เทเคล ปาร์ซิน5:25 ภาษาอารเมคว่าอูปาร์ซิน(ซึ่งก็คือและปาร์ซิน)

26“ความหมายนั้นก็คือ

เมเน5:26 หมายถึงนับหรือมินา (เป็นหน่วยของเงินตรา) หมายความว่า พระเจ้าได้ทรงนับวันเวลาแห่งรัชกาลของฝ่าพระบาทไว้และนำมาถึงจุดจบ

27เทเคล5:27 หมายถึงชั่งหรือเชเขล (เป็นหน่วยของเงินตรา) หมายความว่า ฝ่าพระบาทถูกชั่งบนตราชั่งและเบากว่าที่กำหนด

28เปเรส5:28 เป็นรูปเอกพจน์ของปาร์ซินแปลว่าแบ่งแยกหรือเปอร์เซียหรือครึ่งมินาหรือครึ่งเชเขลก็ได้ หมายความว่า ราชอาณาจักรของฝ่าพระบาทถูกแบ่งแยก และยกให้ชาวมีเดียและเปอร์เซีย”

29แล้วเบลชัสซาร์รับสั่งให้ดาเนียลสวมชุดสีม่วงและสร้อยคอทองคำ แล้วแต่งตั้งให้เป็นผู้ครอบครองอันดับที่สามของราชอาณาจักร

30ในคืนวันนั้นเองกษัตริย์เบลชัสซาร์ของชาวบาบิโลน5:30 หรือชาวเคลเดียก็ถูกปลงพระชนม์ 31และดาริอัสแห่งมีเดียทรงยึดอาณาจักรบาบิโลนได้ ขณะนั้นดาริอัสทรงมีพระชนมายุ 62 พรรษา