ዳንኤል 2 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ዳንኤል 2:1-49

ናቡከደነፆር ያለመው ሕልም

1ናቡከደነፆር በነገሠ በሁለተኛው ዓመት ሕልም ዐለመ፤ መንፈሱ ታወከ፤ እንቅልፍም ከእርሱ ራቀ። 2ያለመውንም ሕልም እንዲነግሩት ንጉሡ ጠንቋዮችን፣ አስማተኞችን፣ መተተኞችንና ኮከብ ቈጣሪዎችን2፥2 ወይም ከለዳውያንን እንዲሁም 4፡5 እና 10 እንዲጠሩ አዘዘ፤ እነርሱም ገብተው በፊቱ ቆሙ፤ 3እርሱም፣ “አንድ ሕልም ዐለምሁ፤ ሕልሙም ምን እንደ ሆነ2፥3 ወይም ምን እንደ ነበር ለማወቅ መንፈሴ ተጨንቋል” አላቸው።

4ከዚያም ኮከብ ቈጣሪዎቹ ለንጉሡ በአረማይክ2፥4 ይህ ምዕራፍ ከዚህ ጀምሮ እስከ ም 7 ድረስ የተጻፈው በአረማይክ ነው። ቋንቋ “ንጉሥ ሆይ፤ ለዘላለም ንገሥ! ሕልምህን ለአገልጋዮችህ ንገረን፤ እኛም እንፈታልሃለን” አሉት።

5ንጉሡም ለኮከብ ቈጣሪዎቹ እንዲህ ሲል መለሰ፤ “ሕልሙንና ትርጕሙን ባትነግሩኝ አካላችሁ እንዲቈራረጥና ቤቶቻችሁም የፍርስራሽ ክምር እንዲሆኑ ወስኛለሁ፤ 6ነገር ግን ሕልሙንና ትርጕሙን ብትነግሩኝ፣ ስጦታና ሽልማት፣ ታላቅ ክብርም ከእኔ ትቀበላላችሁ፤ ሕልሙን ንገሩኝ፤ ትርጕሙንም አሳውቁኝ።”

7እነርሱም እንደ ገና፣ “ንጉሥ ሕልሙን ለአገልጋዮቹ ይንገረን፤ እኛም እንተረጕመዋለን” ብለው መለሱ።

8ንጉሡም እንዲህ ብሎ መለሰላቸው፤ “እኔ ምን ብዬ እንደ ወሰንሁ ስለምታውቁ፣ ጊዜ ለማራዘም እንደምትሞክሩ ተረድቼአለሁ፤ 9ሕልሙን ባትነግሩኝ፣ አንድ ቅጣት ይጠብቃችኋል፤ ሁኔታው ይለወጣል ብላችሁ በማሰብ የሚያሳስቱ ነገሮችንና ክፉ ሐሳቦችን ልትነግሩኝ አሲራችኋል፤ ስለዚህ ሕልሙን ንገሩኝ፤ ትርጕሙንም ልትነግሩኝ እንደምትችሉ በዚህ ዐውቃለሁ።”

10ኮከብ ቈጣሪዎቹም ለንጉሡ እንዲህ ብለው መለሱ፤ “ንጉሡ የጠየቀውን ጥያቄ ሊመልስ የሚችል ሰው በምድር ላይ አይገኝም! ማንም ንጉሥ ምንም ያህል ታላቅና ኀያል ቢሆን፣ እንዲህ ዐይነት ነገር ማንኛውንም ጠንቋይ፣ አስማተኛ ወይም ኮከብ ቈጣሪን ጠይቆ አያውቅም። 11ንጉሡ የሚጠይቀው እጅግ አስቸጋሪ ነገር ነው፤ በሰዎች መካከል ከማይኖሩት ከአማልክት በቀር ለንጉሡ የሚገልጽለት የለም።”

12ይህም ንጉሡን እጅግ አበሳጨው፤ አስቈጣውም፤ በባቢሎን ያሉ ጠቢባን ሁሉ እንዲገደሉም አዘዘ፤ 13ጠቢባን ሁሉ እንዲገደሉም ዐዋጅ ወጣ፤ ዳንኤልንና ጓደኞቹን ፈልገው እንዲገድሉ ሰዎች ተላኩ።

14የንጉሡ ዘበኞች አለቃ አርዮክ፣ የባቢሎንን ጠቢባን ለመግደል በመጣ ጊዜ፣ ዳንኤል በጥበብና በዘዴ አነጋገረው። 15የንጉሡን መኰንን፣ “ንጉሡ እንዲህ ዐይነት ከባድ ዐዋጅ ያወጣው ስለ ምንድን ነው?” ሲል ጠየቀው፤ አርዮክም ነገሩን ለዳንኤል ገለጠለት። 16በዚህን ጊዜ፣ ዳንኤልም ገብቶ ሕልሙን ይተረጕምለት ዘንድ ጊዜ እንዲሰጠው ንጉሡን ጠየቀው።

17ከዚህ በኋላ ዳንኤል ወደ ቤቱ ተመልሶ ለጓደኞቹ ለአናንያ፣ ለሚሳኤልና ለአዛርያ ነገሩን ገለጠላቸው። 18እርሱና ጓደኞቹ ከቀሩት የባቢሎን ጠቢባን ጋር እንዳይገደሉ፣ የሰማይ አምላክ ምሕረት ያደርግላቸውና ምስጢሩንም ይገልጥላቸው ዘንድ እንዲጸልዩ አሳሰባቸው። 19ለዳንኤልም ምስጢሩ በሌሊት በራእይ ተገለጠለት፤ ዳንኤልም የሰማይን አምላክ አመሰገነ፤ 20እንዲህም አለ፤

“ጥበብና ኀይል የእርሱ ነውና፣

የእግዚአብሔር ስም ከዘላለም እስከ ዘላለም ይባረክ።

21ጊዜንና ወቅትን ይለውጣል፤

ነገሥታትን በዙፋን ያስቀምጣል፣

ደግሞም ያወርዳቸዋል፤

ጥበብን ለጠቢባን፣

ዕውቀትንም ለሚያስተውሉ ይሰጣል።

22የጠለቀውንና የተሰወረውን ነገር ይገልጣል፤

በጨለማ ያለውን ያውቃል፤

ብርሃንም ከእርሱ ጋር ይኖራል።

23የአባቶቼ አምላክ ሆይ፤ አመሰግንሃለሁ፤

አከብርሃለሁም፤

ጥበብንና ኀይልን ሰጥተኸኛልና፤

ከአንተ የጠየቅነውን ነገር አሳውቀኸኛል፤

የንጉሡን ሕልም አሳውቀኸናል።”

ዳንኤል ሕልሙን ተረጐመ

24ዳንኤልም የባቢሎንን ጠቢባን እንዲገድል ንጉሡ ወዳዘዘው ወደ አርዮክ ሄዶ፣ “የባቢሎንን ጠቢባን አትግደል፤ ወደ ንጉሡ ውሰደኝ፤ እኔም ሕልሙን እተረጕምለታለሁ” አለው።

25አርዮክም ዳንኤልን ወዲያውኑ ወደ ንጉሡ በመውሰድ፣ “ሕልሙንና ትርጕሙን ለንጉሡ መግለጥ የሚችል ሰው ከይሁዳ ምርኮኞች መካከል አግኝቻለሁ” አለው።

26ንጉሡም ብልጣሶር የተባለውን ዳንኤልን፣ “ያየሁትን ሕልምና ትርጕሙን ልትነግረኝ ትችላለህን?” አለው።

27ዳንኤልም እንዲህ አለ፤ “አንድም ጠቢብ፣ አስማተኛ፣ ጠንቋይም ሆነ ቃላተኛ ንጉሡ የጠየቀውን ምስጢር መግለጥ የሚችል የለም፤ 28ነገር ግን ምስጢርን የሚገልጥ አምላክ በሰማይ አለ፤ እርሱም በሚመጡት ዘመናት የሚሆነውን ነገር ለንጉሥ ናቡከደነፆር ገልጧል፤ በዐልጋህ ላይ ተኝተህ ሳለ በአእምሮህ የነበረው ሕልምና ራእይ ይህ ነው፤

29“ንጉሥ ሆይ፤ ተኝተህ ሳለ፣ አእምሮህ ወደ ፊት ሊሆን ስላለው ነገር ያሰላስል ነበር፤ ምስጢርን ገላጭ የሆነውም ወደ ፊት የሚሆነውን ነገር አሳየህ። 30ይህ ምስጢር ለእኔ የተገለጠው፣ ከሰው ሁሉ ይልቅ ታላቅ ጥበብ ስላለኝ አይደለም፤ ነገር ግን ንጉሥ ሆይ፤ አንተ ትርጕሙን እንድታውቅና በአእምሮህ ታሰላስለው የነበረው ነገር ምን እንደ ሆነ ትረዳ ዘንድ ነው።

31“ንጉሥ ሆይ፤ በፊት ለፊትህ ግዙፍ የሆነ፣ የሚያብረቀርቅና የሚያስፈራ ታላቅ ምስል ቆሞ አየህ፤ 32የምስሉ ራስ ከንጹሕ ወርቅ፣ ደረቱና ክንዶቹ ከብር፣ ሆዱና ጭኖቹ ከናስ የተሠሩ ነበሩ፤ 33ቅልጥሞቹም ከብረት፣ እግሮቹም ከፊሉ ከብረት፣ ከፊሉም ከሸክላ የተሠሩ ነበሩ። 34ይህን በመመልከት ላይ ሳለህ፣ አንድ ድንጋይ የሰው እጅ ሳይነካው ተፈንቅሎ ወረደ፤ ከብረትና ከሸክላ የተሠሩትን የምስሉን እግሮች መታቸው፤ አደቀቃቸውም። 35ወዲያውኑም ብረቱ፣ ሸክላው፣ ናሱ፣ ብሩና ወርቁ ተሰባበሩ፤ በበጋ ወራት በዐውድማ ላይ እንደሚገኝ እብቅም ሆኑ፤ ነፋስም አንዳች ሳያስቀር ጠራረጋቸው፤ ምስሉን የመታው ድንጋይ ግን ታላቅ ተራራ ሆነ፤ ምድርንም ሞላ።

36“ሕልሙ ይህ ነበር፤ አሁን ትርጕሙን ለንጉሥ እንናገራለን። 37ንጉሥ ሆይ፤ አንተ የነገሥታት ንጉሥ ነህ፤ የሰማይ አምላክ መንግሥትንና ሥልጣንን፣ ኀይልንና ክብርን ሰጥቶሃል፤ 38የሰው ልጆችን፣ የምድር አራዊትንና የሰማይ ወፎችን በእጅህ አሳልፎ ሰጥቶሃል፤ በየትም ቦታ ቢሆኑ፣ በሁሉም ላይ ገዥ አድርጎሃል፤ እንግዲህ የወርቁ ራስ አንተ ነህ።

39“ከአንተም በኋላ ከአንተ የሚያንስ ሌላ መንግሥት ይነሣል፤ ቀጥሎም በናስ የተመሰለው ሦስተኛ መንግሥት ይነሣል፤ መላውን ምድርም ይገዛል። 40በመጨረሻም ሁሉን ነገር እንደሚቀጠቅጥና እንደሚሰብር ብረት ብርቱ የሆነ አራተኛ መንግሥት ይነሣል፤ ብረት ሁሉን ሰባብሮ እንደሚያደቅ ከእርሱ በፊት የነበሩትን መንግሥታት ሁሉ ሰባብሮ ያደቅቃቸዋል። 41እግሮቹና ጣቶቹ ከፊል ብረትና ከፊል ሸክላ ሆነው እንዳየህ፣ እንዲሁ የተከፋፈለ መንግሥት ይሆናል፤ ነገር ግን ብረትና ሸክላ ተደባልቀው እንዳየህ በከፊል የብረት ጥንካሬ ይኖረዋል። 42የእግሮቹ ጣቶች ከፊሉ ብረት ከፊሉ ሸክላ እንደ ሆኑ ሁሉ ይህም መንግሥት በከፊሉ ብርቱ በከፊሉ ደካማ ይሆናል። 43ብረትና ሸክላ ተደባልቀው እንዳየህ ሁሉ ሕዝቡም ድብልቅ ይሆናል፤ ብረትና ሸክላ እንደማይዋሃድ ሁሉ ሕዝቡም በአንድነት አይኖሩም።

44“በእነዚያ ነገሥታት ዘመን፣ የሰማይ አምላክ ፈጽሞ የማይፈርስና ለሌላም ሕዝብ የማይሰጥ መንግሥት ይመሠርታል፤ እነዚያን መንግሥታት ሁሉ ያደቅቃል፤ እስከ መጨረሻውም ያጠፋቸዋል፤ ይህ መንግሥት ራሱ ግን ለዘላለም ጸንቶ ይኖራል። 45የሰው እጅ ሳይነካው ከተራራ ተፈንቅሎ የወረደውና ብረቱን፣ ናሱን፣ ሸክላውን፣ ብሩንና ወርቁን ያደቀቀው ድንጋይ ራእይ ትርጓሜ ይህ ነው፤

“ታላቁ አምላክ ወደ ፊት የሚሆነውን ለንጉሡ አሳይቶታል፤ ሕልሙ እውነት ነው፤ ትርጓሜውም የታመነ ነው።”

46ከዚያም ንጉሥ ናቡከደነፆር በግንባሩ ተደፍቶ ለዳንኤል ሰገደለት፤ አከበረውም፤ መሥዋዕትና ዕጣንም እንዲያቀርቡለት አዘዘ። 47ንጉሡም ዳንኤልን፣ “ይህን ምስጢር ልትገልጥ ችለሃልና፣ በእውነት አምላካችሁ የአማልክት አምላክና የነገሥታት ጌታ፣ ምስጢርንም ገላጭ ነው” አለው።

48ንጉሡም ዳንኤልን በከፍተኛ ሥልጣን ላይ አስቀመጠው፤ እጅግ ብዙ ስጦታዎችንም ሰጠው፤ የመላው ባቢሎን አውራጃ ገዥ አደረገው፤ በባቢሎን ጠቢባን ሁሉ ላይም አለቃ አድርጎ ሾመው። 49ከዚህም በላይ በዳንኤል አሳሳቢነት ንጉሡ ሲድራቅን፣ ሚሳቅንና አብደናጎን የባቢሎን አውራጃ አስተዳዳሪዎች አድርጎ ሾማቸው፤ ዳንኤል ግን በቤተ መንግሥት ተቀመጠ።

Thai New Contemporary Bible

ดาเนียล 2:1-49

เนบูคัดเนสซาร์ทรงฝัน

1ในปีที่สองแห่งรัชกาล เนบูคัดเนสซาร์ทรงฝัน แล้วทุกข์พระทัยมากจนบรรทมไม่หลับ 2จึงรับสั่งให้นักเล่นอาคม นักเวทมนตร์ พ่อมดหมอผี และพวกโหราจารย์2:2 หรือชาวเคลเดียเช่นเดียวกับข้อ 4,5 และ 10มาทูลให้ทรงทราบว่าทรงฝันเรื่องอะไร เมื่อพวกเขามาเข้าเฝ้า 3กษัตริย์ตรัสกับเขาว่า “เราฝันไป ทำให้เราทุกข์ใจมาก เราอยากรู้ว่าฝันนั้นหมายถึงอะไร”

4พวกโหราจารย์จึงกราบทูลเป็นภาษาอารเมค2:4 เนื้อความของต้นฉบับตั้งแต่ตอนนี้จนถึงบทที่ 7 เป็นภาษาอารเมคว่า “ขอฝ่าพระบาทจงทรงพระเจริญ! โปรดเล่าความฝันมาเถิด พวกข้าพระบาทจะทูลทำนายถวาย”

5กษัตริย์ตรัสตอบเหล่าโหราจารย์ว่า “เราตั้งใจแน่วแน่แล้วว่า หากพวกเจ้าบอกเราไม่ได้ว่าเราฝันอะไรและหมายความว่าอะไร เราจะสับพวกเจ้าเป็นชิ้นๆ และทำลายบ้านเรือนของเจ้าให้กลายเป็นกองขยะ 6แต่หากเจ้าเล่าความฝันและทำนายได้ เจ้าจะได้รับรางวัลและเกียรติยศยิ่งใหญ่ ฉะนั้นจงเล่าความฝันและแก้ฝันให้เราเถิด”

7พวกเขาทูลอีกว่า “ขอฝ่าพระบาททรงเล่าความฝันให้ผู้รับใช้ฟังเถิด แล้วข้าพระบาททั้งหลายจะทำนายฝันถวาย”

8กษัตริย์จึงตรัสว่า “เราแน่ใจว่าพวกเจ้าพยายามถ่วงเวลา เพราะพวกเจ้ารู้อยู่ว่าเราตัดสินใจเด็ดขาดแล้ว 9หากพวกเจ้าไม่บอกว่าเราฝันอะไรก็มีโทษทัณฑ์สถานเดียว พวกเจ้าสมรู้ร่วมคิดกันพูดล่อหลอกเราเพราะหวังว่าเราจะเปลี่ยนใจ จงเล่าความฝันมาสิ เราจะได้รู้ว่าเจ้าแก้ฝันให้เราได้”

10โหราจารย์ทั้งหลายทูลว่า “ไม่มีใครในโลกนี้สามารถทำอย่างที่ฝ่าพระบาทประสงค์ได้! ไม่มีกษัตริย์องค์ใดจะถามเช่นนี้จากผู้เล่นอาคม นักเวทมนตร์ หรือโหราจารย์ได้ ไม่ว่ากษัตริย์องค์นั้นจะยิ่งใหญ่เกรียงไกรเพียงใด 11สิ่งที่ฝ่าพระบาทให้ทำนี้ยากเกินวิสัยมนุษย์จะทำได้ มีแต่เทพเจ้าเท่านั้นจะบอกได้และเทพเจ้าก็ไม่ได้อยู่ในหมู่มนุษย์”

12เมื่อได้ยินเช่นนี้ กษัตริย์ทรงพระพิโรธยิ่งนักและตรัสสั่งให้ประหารชีวิตปราชญ์ทั้งหมดในกรุงบาบิโลน 13ดังนั้นจึงมีพระราชกฤษฎีกาออกมาให้ประหารชีวิตพวกนักปราชญ์ แล้วก็มีคนไปตามตัวดาเนียลกับเพื่อนเพื่อนำตัวไปประหาร

14เมื่ออารีโอคผู้บัญชาการทหารรักษาพระองค์ออกไปเพื่อประหารปราชญ์ของบาบิโลน ดาเนียลจึงเจรจากับเขาด้วยสติปัญญาและปฏิภาณ 15ดาเนียลถามเขาว่า “เหตุใดกษัตริย์ทรงออกพระราชกฤษฎีการุนแรงถึงเพียงนี้?” อารีโอคก็อธิบายให้ฟัง 16ดาเนียลจึงเข้าเฝ้ากษัตริย์เพื่อทูลขอเวลา เพื่อจะทูลความหมายของความฝันให้ทรงทราบ

17จากนั้นดาเนียลกลับไปบ้านและเล่าเรื่องให้ฮานันยาห์ มิชาเอล กับอาซาริยาห์ผู้เป็นเพื่อนฟัง 18แล้วเร่งเร้าให้พวกเขาอธิษฐานขอต่อพระเจ้าแห่งฟ้าสวรรค์ที่จะทรงกรุณาในเรื่องล้ำลึกนี้ด้วย เพื่อดาเนียลกับเพื่อนๆ จะไม่ถูกประหารไปพร้อมกับปราชญ์คนอื่นๆ ในบาบิโลน 19คืนนั้นพระเจ้าทรงสำแดงความล้ำลึกนี้แก่ดาเนียลในนิมิต ดาเนียลจึงสรรเสริญพระเจ้าแห่งฟ้าสวรรค์ 20และกล่าวว่า

“สรรเสริญพระนามของพระเจ้าชั่วนิจนิรันดร์

สติปัญญาและฤทธิ์อำนาจเป็นของพระองค์

21พระองค์ทรงเปลี่ยนแปลงวาระเวลาและฤดูกาล

ทรงแต่งตั้งและถอดถอนกษัตริย์

พระองค์ประทานสติปัญญาแก่ผู้เฉลียวฉลาด

และประทานความรู้แก่ผู้ที่ฉลาดหลักแหลม

22พระองค์ทรงเผยสิ่งที่ลึกซึ้งและซ่อนเร้นอยู่

ทรงทราบสิ่งที่แฝงอยู่ในความมืด

และความสว่างอยู่กับพระองค์

23ข้าแต่พระเจ้าของบรรพบุรุษของข้าพระองค์ ข้าพระองค์ขอบพระคุณและสรรเสริญพระองค์

พระองค์ประทานสติปัญญาและฤทธิ์อำนาจแก่ข้าพระองค์

พระองค์ทรงทำให้ข้าพระองค์ทราบสิ่งที่ทูลขอจากพระองค์

ทรงทำให้ข้าพระองค์ทั้งหลายทราบความฝันของกษัตริย์”

ดาเนียลทำนายฝัน

24แล้วดาเนียลไปพบอารีโอคซึ่งกษัตริย์ทรงใช้ให้ไปประหารชีวิตเหล่านักปราชญ์ของบาบิโลน ดาเนียลกล่าวกับเขาว่า “อย่าประหารเหล่านักปราชญ์ของบาบิโลนเลย โปรดนำข้าพเจ้าไปเข้าเฝ้ากษัตริย์เพื่อทำนายฝันถวาย”

25อารีโอคจึงพาดาเนียลไปเข้าเฝ้าทันทีและทูลว่า “ข้าพระบาทพบชายผู้หนึ่งในหมู่เชลยที่มาจากยูดาห์ซึ่งสามารถกราบทูลว่าความฝันนั้นหมายความว่าอะไร”

26กษัตริย์ตรัสถามดาเนียล (หรือที่เรียกกันว่า เบลเทชัสซาร์) ว่า “เจ้าสามารถเล่าสิ่งที่เราฝันและแก้ฝันให้ได้หรือ?”

27ดาเนียลทูลตอบว่า “ไม่มีปราชญ์ นักเวทมนตร์ นักเล่นคาถาอาคม และโหรคนใดสามารถทูลความล้ำลึกที่ฝ่าพระบาทตรัสถามนั้นได้ 28แต่มีพระเจ้าองค์หนึ่งในฟ้าสวรรค์ผู้ทรงเปิดเผยสิ่งล้ำลึก และได้ทรงสำแดงให้กษัตริย์เนบูคัดเนสซาร์เห็นสิ่งที่จะเกิดขึ้นในอนาคต ความฝันและนิมิตซึ่งผ่านเข้ามาในพระดำริขณะฝ่าพระบาทบรรทมอยู่บนพระแท่นมีดังนี้

29“ข้าแต่กษัตริย์ ขณะฝ่าพระบาทบรรทมอยู่และทรงดำริถึงสิ่งต่าง ๆที่จะเกิดขึ้น พระเจ้าผู้ทรงเปิดเผยความล้ำลึกก็ทรงแสดงให้ฝ่าพระบาททราบถึงสิ่งที่จะเกิดขึ้น 30ที่พระเจ้าทรงโปรดให้ความล้ำลึกนี้ประจักษ์แจ้งแก่ข้าพระบาท ไม่ใช่เพราะข้าพระบาทมีสติปัญญามากกว่าคนอื่นๆ แต่เพื่อฝ่าพระบาทจะทรงทราบความหมายและเข้าใจสิ่งที่เข้ามาในพระดำริ

31“ข้าแต่กษัตริย์ ฝ่าพระบาทได้ทอดพระเนตรเห็นรูปปั้นมหึมาตั้งอยู่ต่อหน้าเปล่งประกายเจิดจ้า มีลักษณะน่าครั่นคร้าม 32ศีรษะของรูปปั้นนั้นทำด้วยทองคำบริสุทธิ์ หน้าอกและแขนทำด้วยเงิน ท้องและต้นขาทำด้วยทองสัมฤทธิ์ 33ขาทำด้วยเหล็ก เท้าเป็นเหล็กปนดินเหนียว 34ขณะฝ่าพระบาททอดพระเนตรอยู่นั้น ก็มีหินก้อนหนึ่งถูกสกัดออกมา แต่ไม่ใช่ด้วยมือของมนุษย์ หินนั้นกระแทกเท้าของรูปปั้นซึ่งทำด้วยเหล็กปนดินเหนียวแตกกระจาย 35แล้วเหล็ก ดินเหนียว ทองสัมฤทธิ์ เงิน และทองคำ ก็แหลกเป็นชิ้นๆ และกลายเป็นเหมือนแกลบที่ลานนวดข้าวในฤดูร้อน ซึ่งลมพัดปลิวหายไปไม่เหลือร่องรอยไว้เลย แต่หินที่กระแทกรูปปั้นกลับกลายเป็นภูเขามหึมาปกคลุมทั่วโลก

36“นั่นคือความฝัน บัดนี้ข้าพระบาทขอทูลความหมายให้ทรงทราบ 37ฝ่าพระบาททรงเป็นจอมกษัตริย์ พระเจ้าแห่งฟ้าสวรรค์ได้ประทานบารมี อำนาจ ความเกรียงไกร และเกียรติแก่ฝ่าพระบาท 38พระองค์ทรงมอบมนุษยชาติ สัตว์ป่าในท้องทุ่ง และนกในอากาศไว้ในพระหัตถ์ของฝ่าพระบาท พระเจ้าทรงให้ฝ่าพระบาทครอบครองสิ่งเหล่านั้นไม่ว่าจะอยู่ที่ไหน ฝ่าพระบาทคือศีรษะที่ทำด้วยทองคำนั้น

39“หลังจากฝ่าพระบาทแล้ว จะมีอีกอาณาจักรหนึ่งรุ่งเรืองขึ้นมาแต่ด้อยกว่าของฝ่าพระบาท จากนั้นเป็นอาณาจักรที่สามคือทองสัมฤทธิ์ซึ่งจะปกครองทั่วโลก 40ท้ายสุดคืออาณาจักรที่สี่ซึ่งแข็งแกร่งเหมือนเหล็ก เหล็กฟาดฟันทุกสิ่งให้ย่อยยับ อาณาจักรนั้นจะบดขยี้อาณาจักรอื่นๆ ทั้งปวงให้ยับเยิน เหมือนเหล็กที่ทำให้สิ่งอื่นๆ แหลกลาญ 41ตามที่ฝ่าพระบาทเห็นว่าเท้าและนิ้วเท้าเป็นดินเหนียวปนเหล็ก แสดงว่าอาณาจักรนี้แยกออกเป็นส่วนๆ แต่ก็จะมีกำลังแข็งแกร่งเหมือนเหล็กอยู่บ้าง ตามที่ฝ่าพระบาทเห็นเป็นเหล็กปนดินเหนียว 42ดังที่นิ้วเท้าเป็นดินเหนียวปนเหล็ก อาณาจักรนี้ก็จะมีส่วนที่แข็งแกร่งและส่วนที่เปราะบาง 43และตามที่ฝ่าพระบาททรงเห็นเหล็กปนกับดินเหนียว ประชาชนก็จะผสมผสานแต่ไม่รวมเป็นหนึ่งเดียวกัน ซึ่งก็ไม่ต่างจากเหล็กผสมดินเหนียว

44“ในยุคของกษัตริย์เหล่านั้น พระเจ้าแห่งฟ้าสวรรค์จะทรงตั้งอาณาจักรหนึ่งซึ่งไม่มีใครทำลายล้างได้ ทั้งจะไม่ตกเป็นของชนชาติอื่น อาณาจักรนี้จะบดขยี้อาณาจักรอื่นๆ ทั้งปวงจนราบคาบ อาณาจักรนี้จะยั่งยืนมั่นคงตลอดกาล 45นี่คือความหมายของนิมิตเรื่องหินที่ถูกสกัดจากภูเขา ซึ่งไม่ใช่ด้วยมือมนุษย์ หินซึ่งกระแทกเหล็ก ทองสัมฤทธิ์ ดินเหนียว เงิน และทองคำให้แตกกระจาย

“พระเจ้าผู้ยิ่งใหญ่ทรงสำแดงให้ฝ่าพระบาททราบถึงสิ่งที่จะเกิดขึ้นในอนาคต ความฝันนี้เป็นความจริงและการตีความนี้ก็เชื่อถือได้”

46แล้วกษัตริย์เนบูคัดเนสซาร์ก็ทรงทรุดองค์ลงกราบดาเนียล และรับสั่งให้นำเครื่องบูชากับเครื่องหอมมาถวายดาเนียล 47กษัตริย์ตรัสกับดาเนียลว่า “พระเจ้าของท่านทรงเป็นพระเจ้าเหนือพระทั้งหลายแน่นอน ทรงเป็นจอมราชันและทรงเป็นผู้เปิดเผยความล้ำลึกทั้งมวล เพราะท่านสามารถเปิดเผยความล้ำลึกนี้ได้”

48แล้วกษัตริย์ทรงแต่งตั้งดาเนียลให้ดำรงตำแหน่งสูง และประทานบำเหน็จรางวัลมากมาย ทรงตั้งให้ปกครองบาบิโลนทั้งมณฑลและให้ดูแลปราชญ์ทั้งปวงของบาบิโลน 49ยิ่งกว่านั้นกษัตริย์ทรงแต่งตั้งชัดรัค เมชาค และอาเบดเนโกให้เป็นผู้บริหารมณฑลบาบิโลนตามที่ดาเนียลทูลขอ ส่วนดาเนียลเองอยู่ที่ราชสำนัก