ዳንኤል 10 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ዳንኤል 10:1-21

ዳንኤል በራእይ ያየው ሰው

1የፋርስ ንጉሥ ቂሮስ በነገሠ በሦስተኛው ዓመት፣ ብልጣሶር ለተባለው ዳንኤል ራእይ ታየው። መልእክቱ እውነት ነው፤ ስለ ታላቅ ጦርነትም የሚገልጽ ነበረ10፥1 ወይም እውነትና ከባድ ሸክም ነበር። መልእክቱንም ይገነዘብ ዘንድ በራእይ ማስተዋል ተሰጠው።

2በዚያን ጊዜ እኔ ዳንኤል ለሦስት ሳምንት አለቀስሁ፤ 3ሦስቱም ሳምንት እስኪፈጸም ድረስ ምርጥ ምግብ አልበላሁም፤ ሥጋም ሆነ የወይን ጠጅ ወደ አፌ አልገባም፤ ቅባትም አልተቀባሁም።

4በመጀመሪያው ወር በሃያ አራተኛው ቀን፣ በታላቁ በጤግሮስ ወንዝ ዳር ቆሜ፣ 5ቀና ብዬ ስመለከት፣ በፊቴ በፍታ የለበሰና በወገቡም ላይ ምርጥ የወርቅ ቀበቶ የታጠቀ አንድ ሰው አየሁ። 6አካሉ እንደ ዕንቍ፣ ፊቱ እንደ መብረቅ፣ ዐይኖቹ እንደሚንበለበል ፋና፣ ክንዶቹና እግሮቹ እንደ ጋለ ናስ የሚያብረቀርቁ፣ ድምፁም እንደ ብዙ ሕዝብ ድምፅ ነበር።

7ራእዩን ያየሁት እኔ ዳንኤል ብቻ ነበርሁ፤ ከእኔ ጋር የነበሩት ሰዎች አላዩም፤ ነገር ግን ታላቅ ፍርሀት ስለ ወደቀባቸው ሸሽተው ተደበቁ። 8ስለዚህ ይህን ታላቅ ራእይ እያየሁ ብቻዬን ቀረሁ፤ ምንም ጕልበት አልነበረኝም፤ መልኬ እጅጉን ገረጣ፤ ኀይልም አጣሁ። 9ከዚያም የቃሉን ድምፅ ሰማሁ፤ የቃሉንም ድምፅ በሰማሁ ጊዜ፣ በግንባሬ በምድር ላይ ተደፍቼ በከባድ እንቅልፍ ተዋጥሁ።

10እነሆም፣ አንድ እጅ ዳሰሰኝ፤ እየተንቀጠቀጥሁም በእጄና በጕልበቴ አቆመኝ፤ 11እርሱም፣ “እጅግ የተወደድህ ዳንኤል ሆይ፤ አሁን ወዳንተ ተልኬአለሁና፣ የምነግርህን አስተውል፤ ቀጥ ብለህም ቁም” አለኝ። ይህን ሲለኝም፣ እየተንቀጠቀጥሁ ተነሥቼ ቆምሁ።

12ደግሞም እንዲህ አለኝ፤ “ዳንኤል ሆይ፤ አትፍራ፣ ማስተዋልን ለማግኘትና በአምላክህም ፊት ራስህን ለማዋረድ ከወሰንህበት ከመጀመሪያው ቀን አንሥቶ ቃልህ ተሰምቷል፤ እኔም የቃልህን መልስ ይዤ መጥቻለሁ። 13ነገር ግን የፋርስ መንግሥት አለቃ ሃያ አንድ ቀን ተቋቋመኝ፤ ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ የሆነው ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ፤ እኔም በዚያ ከፋርስ ንጉሥ ጋር ተውሁት። 14ራእዩ ሊፈጸም ገና ብዙ ዘመን ስለሚቀረው፣ ወደ ፊት በሕዝብህ ላይ የሚሆነውን ልገልጽልህ አሁን ወደ አንተ መጥቻለሁ።”

15ይህን እየተናገረኝ ሳለ፣ ፊቴን ወደ ምድር አቀረቀርሁ፤ የምናገረውንም ዐጣሁ። 16ከዚያም የሰው ልጅ የሚመስል10፥16 አብዛኛዎቹ ማሶሬቲክ የጥንት ቅጆች እንዲሁ ሲሆኑ፣ ከማሶሬቴክ አንድ የጥንት ቅጅ፣ የሙት ባሕር ጥቅልሎችና ሰብዓ ሊቃናት ግን ከዚያም የሰው እጅ የሚመስል ነገር ይላሉ። ከንፈሮቼን ዳሰሰ፤ እኔም አፌን ከፈትሁ፤ መናገርም ጀመርሁ፤ በፊቴ የነበረውንም እንዲህ አልሁት፤ “ጌታዬ ሆይ፤ ከራእዩ የተነሣ ተሠቃይቻለሁ፤ ኀይልም ዐጣሁ። 17ጌታዬ ሆይ፤ ጕልበቴ ከዳኝ፤ መተንፈስም አቅቶኛል፤ እኔ አገልጋይህ ከአንተ ጋር መነጋገር እንዴት እችላለሁ?”

18እንደ ገናም፣ ሰው የሚመስለው ዳሰሰኝ፤ አበረታኝም። 19እርሱም፣ “እጅግ የተወደድህ ሰው ሆይ፤ አትፍራ፤ ሰላም ለአንተ ይሁን፤ በርታ፤ ጽና” አለኝ።

እየተናገረኝም ሳለ፣ በረታሁና፣ “ጌታዬ ሆይ፤ አበርትተኸኛልና ተናገር” አልሁት።

20እርሱም እንዲህ አለኝ፤ “ለምን ወደ አንተ እንደ መጣሁ ታውቃለህ? የፋርስን አለቃ ለመውጋት በቶሎ እመለሳለሁ፤ እኔም ስሄድ የግሪክ አለቃ ይመጣል። 21አስቀድሜ ግን በእውነት መጽሐፍ ውስጥ የተጻፈውን እነግርሃለሁ፤ ከእነዚህ አለቆች ጋር ለመዋጋት ከአለቃችሁ ከሚካኤል በስተቀር የሚረዳኝ የለም።”

Thai New Contemporary Bible

ดาเนียล 10:1-21

ดาเนียลเห็นผู้หนึ่งในนิมิต

1ในปีที่สามของรัชกาลกษัตริย์ไซรัสแห่งเปอร์เซีย พระเจ้าทรงสำแดงเรื่องหนึ่งแก่ดาเนียล (ซึ่งได้ชื่อว่าเบลเทชัสซาร์) เป็นเรื่องจริงและเป็นเรื่องสงครามใหญ่10:1 หรือและเข้าใจยากมาก เขาได้รับความเข้าใจเนื้อความนี้โดยทางนิมิต

2ครั้งนั้นข้าพเจ้าดาเนียลเป็นทุกข์อยู่ตลอดสามสัปดาห์ 3ข้าพเจ้าไม่รับประทานอาหารชั้นดีหรือเนื้อ และไม่ได้แตะต้องเหล้าองุ่นหรือใช้เครื่องชโลมกายใดๆ จนกระทั่งล่วงสามสัปดาห์นั้นไปแล้ว

4ในวันที่ยี่สิบสี่ของเดือนที่หนึ่ง ขณะที่ข้าพเจ้ายืนอยู่ริมฝั่งแม่น้ำไทกริสซึ่งเป็นแม่น้ำใหญ่ 5ข้าพเจ้าเงยหน้ามองเห็นชายผู้หนึ่งอยู่ตรงหน้าข้าพเจ้า สวมเสื้อผ้าลินินเนื้อละเอียด คาดเข็มขัดทองคำเนื้อดี 6กายของเขาสุกใสเหมือนบุษราคัม ใบหน้าเจิดจ้าเหมือนแสงฟ้าแลบ นัยน์ตาเหมือนเปลวไฟลุกโชน แขนขาเป็นมันปลาบเหมือนทองสัมฤทธิ์ขัดเงา และเสียงของเขาดังเหมือนเสียงคนหมู่ใหญ่

7ข้าพเจ้าดาเนียลเพียงคนเดียวที่เห็นนิมิตนั้น ผู้คนที่อยู่กับข้าพเจ้าไม่เห็นอะไร แต่พวกเขาก็หวาดกลัวจนหนีไปหลบซ่อน 8ข้าพเจ้าจึงถูกทิ้งไว้ตามลำพัง ข้าพเจ้าเพ่งดูนิมิตยิ่งใหญ่นี้ แล้วก็หมดเรี่ยวแรง หน้าซีดเผือดเหมือนคนตายและทำอะไรไม่ถูก 9จากนั้นข้าพเจ้าได้ยินผู้นั้นพูด ขณะที่ฟังอยู่ข้าพเจ้าก็หมดสติล้มซบลงกับดิน

10มีมือมาแตะต้องข้าพเจ้า แล้วพยุงข้าพเจ้าให้ค่อยๆ ลุกขึ้นด้วยมือและเข่าที่สั่นเทา 11เขากล่าวว่า “ดาเนียลเอ๋ย ท่านผู้เป็นที่ทรงรักยิ่ง จงใส่ใจฟังถ้อยคำที่เราจะบอกอยู่นี้และยืนขึ้นเถิด เพราะพระเจ้าทรงใช้เรามาหาท่าน” เมื่อเขากล่าวอย่างนี้ ข้าพเจ้าก็ยืนขึ้นและตัวยังสั่นอยู่

12แล้วเขากล่าวต่อไปว่า “ดาเนียลเอ๋ย อย่ากลัวเลย ตั้งแต่วันแรกที่ท่านตั้งใจแน่วแน่จะหาความเข้าใจ และถ่อมใจลงต่อหน้าพระเจ้าของท่าน พระองค์ก็ทรงสดับคำอธิษฐานของท่าน และเรามาเพื่อตอบท่าน 13แต่เทพแห่งอาณาจักรเปอร์เซียขัดขวางเราอยู่ถึง 21 วัน และมีคาเอลหัวหน้าทูตสวรรค์องค์หนึ่งมาช่วยเรา เพราะเราถูกเทพแห่งเปอร์เซียหน่วงเหนี่ยวไว้ที่นั่น 14บัดนี้เรามาเพื่ออธิบายให้ท่านทราบถึงสิ่งที่จะเกิดขึ้นกับพี่น้องร่วมชาติของท่านในอนาคต เพราะนิมิตนั้นเกี่ยวกับกาลภายหน้า”

15ขณะที่เขากล่าวอยู่นั้นข้าพเจ้าก็หมอบซบหน้ากับดินนิ่งเงียบอยู่ 16แล้วผู้ที่ดูเหมือนมนุษย์10:16 สำเนา MT. ฉบับหนึ่ง และฉบับ DSS. และ LXX. ว่าแล้วบางสิ่งที่ดูเหมือนมือมนุษย์ยื่นมือมาแตะริมฝีปากของข้าพเจ้า ข้าพเจ้าจึงเปิดปากพูด ข้าพเจ้ากล่าวกับเขาที่อยู่ตรงหน้าว่า “ท่านเจ้าข้า ข้าพเจ้าทุกข์ใจยิ่งนักเนื่องด้วยนิมิตนั้นและทำอะไรไม่ได้ 17นายเจ้าข้า ข้าพเจ้าผู้รับใช้ของท่านจะกล่าวแก่ท่านได้อย่างไร ข้าพเจ้าหมดเรี่ยวแรง แม้แต่หายใจยังแทบจะไม่ไหว”

18แล้วผู้ที่ดูเหมือนมนุษย์ก็แตะต้องข้าพเจ้า ทำให้ข้าพเจ้ามีกำลังวังชาขึ้น 19เขากล่าวว่า “ท่านผู้เป็นที่ทรงรักยิ่ง อย่ากลัวเลย สันติสุขจงมีแก่เจ้า! จงเข้มแข็งในบัดนี้ จงเข้มแข็งเถิด”

เมื่อเขากล่าวดังนั้นแล้ว ข้าพเจ้าก็เข้มแข็งขึ้น จึงพูดว่า “ท่านโปรดกล่าวต่อไปเถิด เพราะท่านได้ให้กำลังแก่ข้าพเจ้าแล้ว”

20เขาจึงกล่าวว่า “ท่านรู้หรือไม่ว่าเหตุใดเราจึงมาหาท่าน แล้วเราจะกลับไปต่อสู้กับเทพแห่งเปอร์เซีย เมื่อเราไปแล้ว เทพแห่งกรีซจะมา 21แต่อย่างไรก็ตามเรามาก็เพื่อจะบอกท่านถึงสิ่งที่เขียนไว้ในหนังสือแห่งสัจธรรมเสียก่อน (ไม่มีใครช่วยเราต่อสู้กับเทพทั้งสองนั้น ยกเว้นมีคาเอลทูตสวรรค์ของท่าน