ዮናስ 2 – NASV & NAV

New Amharic Standard Version

ዮናስ 2:1-10

የዮናስ ጸሎት

1ዮናስ በዓሣው ሆድ ውስጥ ሆኖ ወደ አምላኩ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ፤ 2እንዲህም አለ፤

“ተጨንቄ ሳለሁ ወደ እግዚአብሔር ተጣራሁ፤

እርሱም መለሰልኝ፤

ከመቃብሩም2፥2 የዕብራይስጡ ትርጕም ሲዖል ይላል። ጥልቅ ርዳታን ፈልጌ ተጣራሁ፤

አንተም ጩኸቴን ሰማህ።

3ጥልቅ ወደ ሆነው፣

ወደ ባሕሩ መካከል ጣልኸኝ፤

ፈሳሾችም ዙሪያዬን ከበቡኝ፤

ማዕበልህና ሞገድህ ሁሉ፣

በላዬ ዐለፉ።

4እኔም፣ ‘ከፊትህ ጠፋሁ፣

ነገር ግን እንደ ገና፣

ወደ ቅዱስ መቅደስህ፣

እመለከታለሁ’ አልሁ።

5ውሃ እስከ ዐንገቴ አጠለቀኝ2፥5 ወይም “ውሃ ከብቦ አስፈራራኝ”

ጥልቁም ከበበኝ፤

የባሕርም ዐረም በራሴ ላይ ተጠመጠመ።

6ወደ ተራሮች መሠረት ሰመጥሁ፤

የምድርም በር ለዘላለም ተዘጋብኝ፤

እግዚአብሔር አምላኬ ሆይ፤

አንተ ግን ሕይወቴን ከጕድጓድ አወጣህ።

7“ነፍሴ በዛለች ጊዜ፣

እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተን ዐሰብሁ፤

ጸሎቴም ወደ አንተ፣

ወደ ቅዱስ መቅደስህ ዐረገች።

8“ከንቱ በሆኑ ጣዖቶች ላይ የሚንጠለጠሉ፣

ሊያገኙ የሚገባቸውን ጸጋ ያጣሉ።

9እኔ ግን በምስጋና መዝሙር፣

መሥዋዕት እሠዋልሃለሁ፤

የተሳልሁትንም እሰጣለሁ፤

ድነት ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው።”

10እግዚአብሔርም ዓሣውን አዘዘው፤ ዮናስንም በደረቅ ምድር ላይ ተፋው።

Ketab El Hayat

يونان 2:1-10

صلاة يونان

1ثُمَّ صَلَّى يُونَانُ إِلَى الرَّبِّ إِلَهِهِ مِنْ جَوْفِ الْحُوتِ، 2قَائِلاً: «اسْتَغَثْتُ بِالرَّبِّ فِي ضِيقِي فَاسْتَجَابَ لِي، وَمِنْ جَوْفِ الْهَاوِيَةِ ابْتَهَلْتُ فَسَمِعْتَ صَوْتِي. 3لأَنَّكَ طَرَحْتَنِي إِلَى اللُّجَجِ الْعَمِيقَةِ فِي قَلْبِ الْبِحَارِ، فَاكْتَنَفَنِي الْغَمْرُ وَأَحَاطَتْ بِي تَيَّارَاتُكَ وَأَمْوَاجُكَ 4فَقُلْتُ: قَدْ طُرِدْتُ مِنْ حَضْرَتِكَ، وَلَنْ أَعُودَ أَتَفَرَّسُ فِي هَيْكَلِكَ الْمُقَدَّسِ. 5قَدْ غَمَرَتْنِي الْمِيَاهُ وَأَحْدَقَتْ بِيَ اللُّجَجُ، وَالْتَفَّ عُشْبُ الْبَحْرِ حَوْلَ رَأْسِي. 6انْحَدَرْتُ إِلَى أُسُسِ الْجِبَالِ وَهَبَطْتُ إِلَى أَعْمَاقِ الأَرْضِ حَيْثُ أُغْلِقَتْ عَلَيَّ مَزَالِيجُهَا إِلَى الأَبَدِ. وَلَكِنَّكَ تُصْعِدُ حَيَاتِي مِنَ الْهَاوِيَةِ أَيُّهَا الرَّبُّ إِلَهِي. 7عِنْدَمَا وَهَنَتْ نَفْسِي فِي دَاخِلِي، تَذَكَّرْتُ إِلَهِي، فَحَلَّقَتْ صَلاتِي إِلَيْكَ، إِلَى هَيْكَلِكَ الْمُقَدَّسِ. 8إِنَّ الَّذِينَ يُبَجِّلُونَ الأَصْنَامَ الْبَاطِلَةَ يَتَخَلَّوْنَ عَنْ مَصْدَرِ نِعْمَتِهِمْ. 9أَمَّا أَنَا فَبِهُتَافِ الْحَمْدِ أَذْبَحُ لَكَ، وَمَا نَذَرْتُهُ أُوفِي بِهِ، لأَنَّ لِلرَّبِّ الْخَلاصَ».

10فَأَمَرَ الرَّبُّ الْحُوتَ فَقَذَفَ بِيُونَانَ إِلَى الشَّاطِئِ.