ዮሐንስ 7 – NASV & HHH

New Amharic Standard Version

ዮሐንስ 7:1-53

ኢየሱስ የዳስ በዓል ወደሚከበርበት ሄደ

1ከዚህ በኋላ ኢየሱስ፣ በዚያ የነበሩት አይሁድ ሊገድሉት ስለ ፈለጉ፣ በይሁዳ አውራጃ መዘዋወር ትቶ በገሊላ ተዘዋወረ። 2የአይሁድ የዳስ በዓል በተቃረበ ጊዜ ግን፣ 3የኢየሱስ ወንድሞች እንዲህ አሉት፤ “ደቀ መዛሙርትህም ደግሞ የምታደርገውን ታምራት እንዲያዩ፣ ከዚህ ወደ ይሁዳ ሂድ፤ 4ራሱን ሊገልጥ እየፈለገ በስውር የሚሠራ ማንም የለምና። አንተም እነዚህን ነገሮች የምታደርግ ከሆነ፣ ራስህን ለዓለም ግለጥ።” 5የገዛ ወንድሞቹ እንኳ አላመኑበትም ነበር።

6ኢየሱስም እንዲህ አላቸው፤ “ለእኔ ትክክለኛው ጊዜ ገና አልደረሰም፤ ለእናንተ ግን ማንኛውም ጊዜ ምቹ ነው። 7ዓለም እናንተን ሊጠላ አይችልም፤ እኔ ግን፣ አድራጎቱ ክፉ መሆኑን ስለምመሰክርበት ይጠላኛል። 8እናንተ ወደ በዓሉ ሂዱ፤ ለእኔ ትክክለኛው ጊዜ ስላልደረሰ7፥8 አንዳንድ ቅጆች ገና ስላልደረሰ ይላሉ ወደ በዓሉ አልሄድም።” 9ይህን ብሏቸው በገሊላ ቈየ።

10ይሁን እንጂ፣ ወንድሞቹ ወደ በዓሉ ከሄዱ በኋላ፣ እርሱም በግልጥ ሳይሆን በስውር ወደ በዓሉ ሄደ። 11በበዓሉም ላይ አይሁድ፣ “ያ ሰው የት አለ?” እያሉ ይፈልጉት ነበር።

12ስለ እርሱ በሕዝቡ መካከል ብዙ ጕምጕምታ ነበር። አንዳንዶች፣ “ደግ ሰው ነው” አሉ።

ሌሎች ግን፣ “የለም፤ ሕዝቡን የሚያስት ነው” አሉ። 13ይሁን እንጂ አይሁድን ከመፍራት የተነሣ ስለ እርሱ በግልጽ የተናገረ ማንም አልነበረም።

ኢየሱስ በበዓሉ ላይ ተገኝቶ አስተማረ

14በበዓሉም አጋማሽ ኢየሱስ ወደ ቤተ መቅደስ ወጥቶ ያስተምር ጀመር። 15አይሁድም በመደነቅ፣ “ይህ ሰው ሳይማር መጻሕፍትን እንዴት ሊያውቅ ቻለ?” አሉ።

16ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አላቸው፤ “የማስተምረው ትምህርት ከራሴ ሳይሆን፣ ከላከኝ የመጣ ነው። 17ማንም የእግዚአብሔርን ፈቃድ ለማድረግ ቢፈልግ፣ የእኔ ትምህርት ከእግዚአብሔር ወይም ከራሴ የመጣ መሆኑን ለይቶ ያውቃል፤ 18ከራሱ የሚናገር፣ ያን የሚያደርገው ለራሱ ክብርን ስለሚሻ ነው፤ ስለ ላከው ክብር የሚሠራ ግን እርሱ እውነተኛ ነው፤ ሐሰትም አይገኝበትም። 19ሙሴ ሕግን አልሰጣችሁምን? ነገር ግን አንዳችሁም ሕጉን አልጠበቃችሁም። ለምን ልትገድሉኝ ትፈልጋላችሁ?”

20ሕዝቡም፣ “አንት ጋኔን ያደረብህ! ደግሞ አንተን ማን ሊገድል ይፈልጋል?” አሉት።

21ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አላቸው፤ “አንድ ሥራ ብሠራ፣ ሁላችሁም ተገረማችሁ። 22ግዝረት የመጣው ከአባቶች እንጂ ከሙሴ አይደለም፤ ሆኖም ሙሴ ግዝረትን ስለ ሰጣችሁ፣ በሰንበት እንኳ ሕፃን ትገርዛላችሁ። 23የሙሴ ሕግ እንዳይሻር ሕፃን በሰንበት የሚገረዝ ከሆነ፣ የሰውን ሁለንተና በሰንበት ስለ ፈወስሁ ለምን በእኔ ላይ ትቈጣላችሁ? 24የሰውን ፊት በማየት መፍረድ ትታችሁ ቅን ፍርድ ፍረዱ።”

ኢየሱስ፣ እርሱ ክርስቶስ ስለ መሆኑ

25በዚህ ጊዜ በኢየሩሳሌም የነበሩ አንዳንድ ሰዎች እንዲህ አሉ፤ “ሊገድሉት የሚፈልጉት ሰው ይህ አይደለምን? 26ይኸው እርሱ በአደባባይ ይናገራል፤ አንድም ቃል አይናገሩትም፤ ክርስቶስ7፥26 ወይም መሲሑ፤ እንዲሁም 27፡31፡41 እና 42 ይመ ነው ብለው ባለሥልጣኖቹም ተቀብለውት ይሆን? 27ይህ ሰው ግን ከየት እንደ ሆነ እኛ እናውቃለን፤ ክርስቶስ ሲመጣ እኮ ከየት እንደ ሆነ ማንም አያውቅም።”

28ኢየሱስ በቤተ መቅደስ አደባባይ ሲያስተምር ድምፁን ከፍ አድርጎ እንዲህ አለ፤ “አዎን፣ እኔን ታውቁኛላችሁ፤ ከየት እንደ ሆንሁም ታውቃላችሁ። እኔ እዚህ ያለሁት በገዛ ራሴ አይደለም፤ ነገር ግን የላከኝ እርሱ እውነተኛ ነው። እናንተ አታውቁትም፤ 29እኔ ግን ከእርሱ ዘንድ ስለሆንሁ፣ እርሱም ስለ ላከኝ ዐውቀዋለሁ።”

30ስለዚህ ሊይዙት ፈለጉ፤ ነገር ግን ጊዜው ገና ስላልደረሰ ማንም እጁን አላሳረፈበትም፤ 31ሆኖም ከሕዝቡ ብዙዎች በእርሱ አምነው፣ “ታዲያ፣ ክርስቶስ ሲመጣ ይህ ሰው ከሚሠራቸው ታምራዊ ምልክቶች የበለጠ ያደርጋል?” አሉ።

32ፈሪሳውያን፣ ሕዝቡ ስለ እርሱ በጕምጕምታ የሚነጋገረውን ነገር ሰሙ፤ የካህናት አለቆችና ፈሪሳውያንም እንዲይዙት የቤተ መቅደስ ጠባቂዎችን ላኳቸው።

33ኢየሱስም እንዲህ አለ፤ “ከእናንተ ጋር የምቈየው ጥቂት ጊዜ ነው፤ ከዚያም ወደ ላከኝ እሄዳለሁ፤ 34ትፈልጉኛላችሁ፤ ግን አታገኙኝም፤ ወዳለሁበትም ልትመጡ አትችሉም።”

35አይሁድም እርስ በርሳቸው እንዲህ ተባባሉ፤ “ይህ ሰው፣ ልናገኘው የማንችለው ወዴት ለመሄድ ቢያስብ ነው? በግሪኮች መካከል ተበታትነው ወደሚኖሩት ወገኖቻችን ሄዶ ግሪኮችን ሊያስተምር ፈልጎ ይሆን? 36‘ትፈልጉኛላችሁ፤ ግን አታገኙኝም፤’ ደግሞም፣ ‘እኔ ወዳለሁበት ልትመጡ አትችሉም’ ሲል ምን ማለቱ ይሆን?”

37የበዓሉ መጨረሻ በሆነው በታላቁ ቀን፣ ኢየሱስ ቆሞ ከፍ ባለ ድምፅ እንዲህ አለ፤ “ማንም የተጠማ ቢኖር ወደ እኔ ይምጣና ይጠጣ፤ 38በእኔ የሚያምን፣ መጽሐፍ እንዳለ7፥37-38 ወይም ማንም የተጠማ ቢኖር ወደ እኔ ይምጣ፤ 38 በእኔ የሚያምን ይጠጣ የሕይወት ውሃ ምንጭ ከውስጡ ይፈልቃል።” 39ይህን ያለው በእርሱ የሚያምኑ ስለሚቀበሉት መንፈስ ነበር፤ ምክንያቱም ኢየሱስ ገና ስላልከበረ መንፈስ አልተሰጠም ነበር።

40ከሕዝቡ አንዳንዶቹ ቃሉን ሰምተው፣ “ይህ ሰው በርግጥ ነቢዩ ነው” አሉ።

41ሌሎችም፣ “እርሱ ክርስቶስ ነው” አሉ።

ሌሎች ደግሞ እንዲህ አሉ፤ “ክርስቶስ ከገሊላ እንዴት ሊመጣ ይችላል? 42መጽሐፍ፣ ክርስቶስ ከዳዊት ዘር7፥42 ወይም ከዳዊት ቤተ ሰብ፣ ዳዊትም ከኖረበት ከቤተ ልሔም እንደሚመጣ ይናገር የለምን?” 43ስለዚህም በኢየሱስ ምክንያት በሕዝቡ መካከል መለያየት ሆነ፤ 44አንዳንዶቹም ሊይዙት ፈለጉ፤ ነገር ግን ማንም እጁን አላሳረፈበትም።

የአይሁድ መሪዎች አለማመን

45በመጨረሻም የቤተ መቅደስ ጠባቂዎቹ፣ ወደ ካህናት አለቆችና ወደ ፈሪሳውያን ተመልሰው ሄዱ፤ እነርሱም ጠባቂዎቹን፣ “ለምን አላመጣችሁትም?” አሏቸው።

46ጠባቂዎቹም፣ “እንደዚህ ሰው፣ ከቶ ማንም ተናግሮ አያውቅም” ሲሉ መለሱ።

47ፈሪሳውያንም እንዲህ ሲሉ መለሱ፤ “እናንተም ተታላችኋል ማለት ነው? 48ለመሆኑ ከባለሥልጣኖችና ከፈሪሳውያን በእርሱ ያመነ አለ? 49ሕጉን የማያውቅ ይህ ሕዝብ ግን የተረገመ ነው።”

50ከዚህ ቀደም ወደ ኢየሱስ ሄዶ የነበረውና ከእነርሱ አንዱ የሆነው ኒቆዲሞስ እንዲህ አላቸው፤ 51“ሕጋችን፣ አስቀድሞ አንድን ሰው ሳይሰማና ምን እንዳደረገ ሳይረዳ ይፈርድበታልን?”

52እነርሱም፣ “አንተም ደግሞ ከገሊላ ነህን? ነቢይ7፥52 ሁለት የጥንት ቅጆች ነቢዩ ይላሉ። ከገሊላ እንደማይነሣ መርምር፤ ትደርስበታለህ” ብለው መለሱለት።

53ከዚህ በኋላ ሁሉም ወደየቤታቸው ሄዱ።

Habrit Hakhadasha/Haderekh

הבשורה על-פי יוחנן 7:1-53

1לאחר מכן חזר ישוע לגליל ועבר מכפר לכפר. הוא לא רצה לשוב ליהודה, כי מנהיגי היהודים שם רצו להרגו. 2בהתקרב חג הסוכות 3האיצו בו אחיו לעלות לירושלים לרגל החג. ”לך ליהודה, כדי שגם תלמידיך יראו את הנסים שאתה מחולל“, לעגו לו.

4”איך אתה רוצה להתפרסם בעודך מסתתר כאן? אם אתה מחולל ניסים ונפלאות, גלה את עצמך לעולם.“ 5גם אחיו לא האמינו בו. 6”עדיין לא הגיע הזמן שאלך, אולם אתם יכולים ללכת בכל זמן שתרצו“, השיב ישוע. 7”כי העולם אינו יכול לשנוא אתכם, אבל הוא שונא אותי, משום שאני מוכיח אותו במעשיו המושחתים. 8לכו אתם לחוג את החג בירושלים. איני הולך עתה, כי טרם הגיע זמני.“ 9וישוע נשאר בגליל.

10אולם לאחר שהלכו אחיו הלך גם ישוע לירושלים, אם כי בסתר, כדי שלא יכירו אותו. 11בינתיים חיפשוהו המנהיגים בין החוגגים וחקרו: ”היכן הוא?“ 12דעת הקהל הייתה חלוקה עליו; אחדים אמרו: ”הוא אדם נפלא!“ ואילו אחרים טענו: ”הוא רמאי!“ 13אך איש לא העז להשמיע את דעתו עליו ברבים, מפחד מנהיגי היהודים.

14בעיצומו של החג הלך ישוע לבית־המקדש ולימד את העם. 15”כיצד הוא יודע כל־כך הרבה?“ תמהו היהודים. ”הרי הוא לא למד אף פעם בבית מדרש!“

16”איני מלמד אתכם את תורתי, כי אם את תורת האלוהים אשר שלחני“, השיב ישוע. 17”מי שרוצה לעשות את רצון האלוהים יודע אם אני מדבר בשם אלוהים או בשם עצמי. 18מי שמשמיע את דעתו האישית מצפה לשבחים ותהילה, אולם מי שרוצה בכבוד שולחו הוא אדם ישר ונאמן. 19משה נתן לכם את התורה אבל איש מביניכם אינו מקיים את התורה. מדוע אתם רוצים להרוג אותי על הפרת התורה?“ 20”היצאת מדעתך“, קרא הקהל. ”מי רוצה להרוג אותך?“

21”אני עשיתי נס אחד בשבת וכולכם התפלאתם והשתוממתם על כך“, אמר ישוע. 22”אבל גם אתם עובדים בשבת! הרי אתם עושים ברית־מילה לפי מצוות משה, מצוה שניתנה לנו למעשה מהאבות וקדמה לתורת משה, גם בשבת. 23אם אתם מתירים קיום ברית־מילה בשבת, כדי לא להפר את התורה, מדוע אתם מתרגזים על שריפאתי מישהו בשבת? 24אל תשפטו רק לפי מה שאתם רואים בעיניכם, אלא בחנו ושפטו בצדק!“

25אחדים מתושבי ירושלים שאלו: ”האם אין זה האיש שהם רוצים להרוג? 26הנה הוא מדבר בציבור ואיש אינו פוגע בו. אולי מנהיגינו הגיעו למסקנה שהוא באמת המשיח! 27אולם כיצד ייתכן הדבר? הרי אנחנו יודעים מאין בא, ואילו המשיח אמור לבוא מאי־שם, ממקום בלתי ידוע.“

28”ודאי שיודעים אתם מי אני ומאין באתי,“ קרא ישוע בקול בבית־המקדש, ”אבל דעו לכם שלא באתי אליכם על דעת עצמי, אלא נשלחתי על־ידי האלוהים שאותו אינכם מכירים. 29אולם אני מכיר אותו, כי אני בא ממנו והוא שלח אותי.“

30ההמון רצה לתפוס אותו, אך איש לא הרים עליו אצבע, כי טרם הגיע זמנו. 31אנשים רבים מן העם האמינו בישוע, ואמרו: ”לאילו ניסים מצפים אתם מהמשיח שאדם זה לא חולל?“

32כאשר נוכחו הפרושים כי העם נוטה להאמין בישוע, הם שלחו יחד עם ראשי הכוהנים סוכנים לתפוס אותו. 33אולם ישוע אמר להם: ”אני אהיה אתכם עוד זמן־מה, ואחר כך אחזור לשולחי. 34תחפשו אותי ולא תמצאוני, כי לא תוכלו לבוא אל המקום שאהיה בו.“

35היהודים נבוכו מדבריו. ”לאן הוא עומד ללכת?“ תמהו. ”אולי בכוונתו לעזוב את הארץ וללכת ללמד את היהודים בתפוצות או אף את הגויים! 36למה התכוון כשאמר כי נחפש אותו ולא נוכל למצוא אותו, ואף לא נוכל לבוא למקום הימצאו?“

37ביום האחרון והגדול של החג עמד ישוע וקרא בקול: ”כל הצמא שיבוא אלי וישתה! 38כי כמו שכתוב, המאמין בי, יזרמו מקרבו נהרות מים חיים.“ 39ישוע התכוון לרוח הקודש שהמאמינים בשמו היו עתידים לקבל. עד לאותו זמן לא ניתן רוח הקודש, כי ישוע עדיין לא נתפאר ולא חזר לשמים. 40אנשים רבים בהמון קראו לאחר ששמעו את דבריו: ”הוא באמת הנביא!“ 41אחרים קראו: ”זהו המשיח!“ היו שלגלגו: ”האם המשיח יבוא מהגליל? 42הלא כתוב כי המשיח יהיה מזרע דוד וכי יבוא מבית לחם, עיר דוד.“ 43דעת הקהל עליו הייתה חלוקה. 44אחדים מהם רצו לתפסו, אך איש לא שלח בו יד.

45אנשי החוק שנשלחו לאסרו חזרו אל שולחיהם בידיים ריקות. ”היכן הוא? מדוע לא הבאתם אותו?“ שאלו הפרושים וראשי הכוהנים.

46”הוא דיבר דברים נפלאים כל־כך; מעולם לא שמענו דברים כאלה!“ השיבו. 47”גם אתם הלכתם שולל?“ כעסו הפרושים. 48”האם ראיתם מישהו בינינו, המנהיגים או הפרושים, אשר מאמין כי הוא המשיח? 49רק ההמון מקרב העם הזה מאמין בו, כי הם אינם יודעים את התורה. ארורים הם!“

50נקדימון היה ביניהם; הוא זה שבא אל ישוע בלילה, וכששמע את דברי הפרושים אמר: 51”האם תורתנו מתירה לנו לשפוט אדם לפני ששמענו מה בפיו וידענו מה שהוא עושה?“

52”גם אתה מהגליל?“ שאלו בלעג. ”דרוש בכתובים וראה שאף נביא אינו בא מהגליל!“ 53בזאת הם נפרדו והלכו איש לביתו.