ዮሐንስ 4 – NASV & NIRV

New Amharic Standard Version

ዮሐንስ 4:1-54

ኢየሱስ ከአንዲት ሳምራዊት ጋር ተነጋገረ

1ፈሪሳውያን ከዮሐንስ ይልቅ ኢየሱስ ብዙ ደቀ መዛሙርትን እንዳፈራና እንዳጠመቀ ሰሙ፤ 2ዳሩ ግን ያጠመቀው ኢየሱስ ሳይሆን ደቀ መዛሙርቱ ነበሩ። 3ጌታም ይህን እንዳወቀ ይሁዳን ለቅቆ ወደ ገሊላ ተመልሶ ሄደ።

4በሰማርያም በኩል ማለፍ ነበረበት። 5ስለዚህ በሰማርያ፣ ያዕቆብ ለልጁ ለዮሴፍ በሰጠው ቦታ አጠገብ ወደ ነበረች፣ ሲካር ወደምትባል ከተማ መጣ። 6በዚያም የያዕቆብ የውሃ ጕድጓድ ነበረ፤ ኢየሱስም ከጕዞው የተነሣ ደክሞት ስለ ነበር በውሃው ጕድጓድ አጠገብ ተቀመጠ፤ ጊዜውም ከቀኑ ስድስት ሰዓት አካባቢ ነበር።

7አንዲት ሳምራዊት ሴት ውሃ ለመቅዳት ስትመጣ ኢየሱስ፣ “እባክሽ የምጠጣው ስጪኝ” አላት፤ 8ደቀ መዛሙርቱ ምግብ ለመግዛት ወደ ከተማ ሄደው ነበር።

9ሳምራዊቷም፣ “አንተ አይሁዳዊ ሆነህ፣ እኔን ሳምራዊቷን እንዴት ውሃ አጠጪኝ ትላለህ?” አለችው፤ ይህን ማለቷ አይሁድ ከሳምራውያን ጋር ስለማይተባበሩ ነው።4፥9 ወይም ሳምራውያን በተጠቀሙበት ሳሕን ወይም ዕቃ አይጠቀሙም ነበር።

10ኢየሱስም፣ “የእግዚአብሔርን ስጦታ ብታውቂና ውሃ አጠጪኝ የሚልሽ ማን መሆኑን ብትረጂ ኖሮ፣ አንቺው በጠየቅሽው፣ እርሱም የሕይወትን ውሃ በሰጠሽ ነበር” ሲል መለሰላት።

11ሴትዮዋም እንዲህ አለችው፤ “ጌታዬ፣ መቅጃ የለህም፤ ጕድጓዱም ጥልቅ ነው፤ ታዲያ ይህን የሕይወት ውሃ ከየት ታገኛለህ? 12ለመሆኑ አንተ፣ ይህን ጕድጓድ ከሰጠን፣ ከአባታችን ከያዕቆብ ትበልጣለህን? እርሱ ራሱና ልጆቹ፣ እንስሳቱም ከዚሁ ጕድጓድ ጠጥተዋል።”

13ኢየሱስም እንዲህ ሲል መለሰላት፤ “ከዚህ ውሃ የሚጠጣ እንደ ገና ይጠማል፤ 14እኔ ከምሰጠው ውሃ የሚጠጣ ግን ከቶ አይጠማም፤ እኔ የምሰጠው ውሃ በውስጡ የሚፈልቅ የዘላለም ሕይወት ውሃ ምንጭ ይሆናል።”

15ሴትዮዋም፣ “ጌታዬ፤ እንዳልጠማና ውሃ ለመቅዳት እንዳልመላለስ፣ እባክህ ይህን ውሃ ስጠኝ” አለችው።

16እርሱም፣ “ሂጂና ባልሽን ጠርተሽ ወደዚህ ተመለሽ” አላት።

17ሴትዮዋም፣ “ባል የለኝም” ብላ መለሰች።

ኢየሱስም፣ እንዲህ አላት፤ “ባል የለኝም ማለትሽ ትክክል ነው፤ 18በርግጥ አምስት ባሎች ነበሩሽ፤ አሁን ከአንቺ ጋር ያለውም ባልሽ ስላልሆነ፣ የተናገርሽው እውነት ነው።”

19ሴትዮዋም እንዲህ አለችው፤ “ጌታዬ፣ አንተ ነቢይ እንደ ሆንህ አያለሁ፤ 20አባቶቻችን በዚህ ተራራ ላይ ሰገዱ፤ እናንተ አይሁድ ግን ሰው መስገድ ያለበት በኢየሩሳሌም ነው ትላላችሁ” አለችው።

21ኢየሱስም እንዲህ አላት፤ “አንቺ ሴት፤ በዚህ ተራራም ሆነ በኢየሩሳሌም ለአብ የማትሰግዱበት ጊዜ እንደሚመጣ እመኚኝ። 22እናንተ ሳምራውያን ለማታውቁት ትሰግዳላችሁ፤ እኛ ግን ድነት ከአይሁድ ስለሆነ ለምናውቀው እንሰግዳለን። 23በእውነት የሚሰግዱ ለአብ በመንፈስና በእውነት የሚሰግዱበት ጊዜ ይመጣል፤ አሁንም መጥቷል፤ አብም እንደዚህ በእውነት የሚሰግዱለትን ይፈልጋል። 24እግዚአብሔር መንፈስ ነው፤ የሚሰግዱለትም በመንፈስና በእውነት ሊሰግዱለት ይገባል።”

25ሴትዮዋም፣ “ክርስቶስ የተባለ መሲሕ እንደሚመጣ ዐውቃለሁ፤ እርሱ ሲመጣ ሁሉን ነገር ይነግረናል” አለችው።

26ኢየሱስም፣ “የማነጋግርሽ እኮ እኔ እርሱ ነኝ” ሲል ገልጦ ነገራት።

ደቀ መዛሙርቱ ተመልሰው መጡ

27በዚህ ጊዜ ደቀ መዛሙርቱ ተመልሰው መጡ፤ ከሴት ጋር ሲነጋገር በማግኘታቸው ተደነቁ፤ ሆኖም ግን፤ “ምን ፈለግህ?” ወይም፣ “ከእርሷ ጋር የምትነጋገረው ለምንድን ነው?” ብሎ የጠየቀው ማንም አልነበረም።

28ሴትዮዋም እንስራዋን ትታ ወደ ከተማ ተመለሰች፤ ለሕዝቡም፣ 29“ያደረግሁትን ሁሉ የነገረኝን ሰው ኑና እዩ፤ እርሱ ክርስቶስ4፥29 ወይም መሲሕ ይሆን እንዴ?” አለች፤ 30እነርሱም ከከተማ ወጥተው እርሱ ወዳለበት አመሩ።

31በዚህ ጊዜ ደቀ መዛሙርቱ፣ “ረቢ፣ እህል ቅመስ እንጂ” አሉት።

32እርሱ ግን፣ “እናንተ የማታውቁት፣ የምበላው ምግብ አለኝ” አላቸው።

33ደቀ መዛሙርቱም፣ “ሰው ምግብ አምጥቶለት ይሆን እንዴ?” ተባባሉ።

34ኢየሱስም እንዲህ አላቸው፤ “የእኔ ምግብ የላከኝን ፈቃድ ማድረግና ሥራውን መፈጸም ነው፤ 35እናንተ፣ ‘ከአራት ወር በኋላ መከር ይደርሳል’ ትሉ የለምን? እነሆ፣ አዝመራው ለመከር እንደ ደረሰ ቀና ብላችሁ ማሳውን ተመልከቱ እላችኋለሁ። 36ዐጫጁ አሁንም ቢሆን እንኳ ደመወዙን እየተቀበለ ነው፤ ለዘላለም ሕይወት ይሆን ዘንድ አዝመራውን ይሰበስባል፤ ይህም ዘሪውና ዐጫጁ በጋራ ደስ እንዲላቸው ነው። 37ስለዚህ፣ ‘አንዱ ይዘራል፤ ሌላውም ያጭዳል’ የተባለው ምሳሌ እውነት ነው። 38ያልደከማችሁበትን እንድታጭዱ ላክኋችሁ፤ አድካሚውን ሥራ ሌሎች ሠሩ፤ እናንተም የድካማቸውን ፍሬ ሰበሰባችሁ።”

ብዙ ሳምራውያን አመኑ

39ሴትየዋ፣ “ያደረግሁትን ሁሉ ነገረኝ” ብላ ስለ መሰከረች፣ ከዚያች ከተማ ብዙ ሳምራውያን በእርሱ አመኑ። 40ስለዚህ፣ ሳምራውያኑ ወደ እርሱ በመጡ ጊዜ አብሯቸው እንዲቈይ አጥብቀው ለመኑት፤ እዚያም ሁለት ቀን ቈየ። 41ከቃሉም የተነሣ ሌሎች ብዙዎች አመኑ።

42ሴትዮዋንም፣ “ከእንግዲህ የምናምነው አንቺ ስለ ነገርሽን ብቻ አይደለም፤ እኛ ራሳችን ሰምተነዋል፤ ይህ ሰው በእውነት የዓለም አዳኝ እንደ ሆነ እናውቃለን” አሏት።

ኢየሱስ የሹሙን ልጅ ፈወሰ

43ከሁለቱ ቀናት በኋላም ወደ ገሊላ ሄደ፤ 44ነቢይ በገዛ አገሩ እንደማይከበር ኢየሱስ ራሱ ተናግሮ ነበርና። 45ገሊላ እንደ ደረሰም የገሊላ ሰዎች በደስታ ተቀበሉት፤ ምክንያቱም፣ እነርሱም በፋሲካ በዓል ኢየሩሳሌም ስለ ነበሩና በዚያ ያደረገውን ሁሉ ስላዩ ነው።

46ኢየሱስም ውሃውን የወይን ጠጅ ወዳደረገበት፣ በገሊላ ወደምትገኘው ወደ ቃና ከተማ ዳግመኛ መጣ፤ በቅፍርናሆምም ልጁ የታመመበት አንድ የቤተ መንግሥት ሹም ነበረ፤ 47ይህም ሰው ኢየሱስ ከይሁዳ ወደ ገሊላ መምጣቱን በሰማ ጊዜ፣ ወደ እርሱ ሄደና በሞት አፋፍ ላይ የነበረውን ልጁን መጥቶ እንዲፈውስለት ለመነው።

48ኢየሱስም፣ “መቼውንም እናንተ ምልክቶችንና ድንቅ ነገሮችን ካላያችሁ አታምኑም” አለው።

49ሹሙም፣ “ጌታዬ፤ ልጄ ከመሞቱ በፊት እባክህ ድረስልኝ” አለው።

50ኢየሱስም፣ “ልጅህ በሕይወት ይኖራልና ሂድ” አለው።

ሰውየውም ኢየሱስ የተናገረውን ቃል አምኖ ሄደ፤ 51በመንገድ ላይ እንዳለም፣ አገልጋዮቹ አግኝተውት ልጁ በሕይወት መኖሩን ነገሩት። 52እርሱም ልጁ በስንት ሰዓት እንደ ተሻለው ሲጠይቃቸው፣ “ትኵሳቱ የለቀቀው ትናንት በሰባት ሰዓት ላይ ነው” አሉት።

53አባትየውም ሰዓቱ ኢየሱስ፣ “ልጅህ በሕይወት ይኖራል” ያለበት ሰዓት መሆኑን ተገነዘበ፤ እርሱና ቤተ ሰቡም ሁሉ አመኑ።

54ይህም፣ ኢየሱስ ከይሁዳ ወደ ገሊላ መጥቶ ያደረገው ሁለተኛው ታምራዊ ምልክት ነው።

New International Reader’s Version

John 4:1-54

Jesus Talks With a Woman From Samaria

1Now Jesus learned that the Pharisees had heard about him. They had heard that he was gaining and baptizing more disciples than John. 2But in fact Jesus was not baptizing. His disciples were. 3So Jesus left Judea and went back again to Galilee.

4Jesus had to go through Samaria. 5He came to a town in Samaria called Sychar. It was near the piece of land Jacob had given his son Joseph. 6Jacob’s well was there. Jesus was tired from the journey. So he sat down by the well. It was about noon.

7A woman from Samaria came to get some water. Jesus said to her, “Will you give me a drink?” 8His disciples had gone into the town to buy food.

9The Samaritan woman said to him, “You are a Jew. I am a Samaritan woman. How can you ask me for a drink?” She said this because Jews don’t have anything to do with Samaritans.

10Jesus answered her, “You do not know what God’s gift is. And you do not know who is asking you for a drink. If you did, you would have asked him. He would have given you living water.”

11“Sir,” the woman said, “you don’t have anything to get water with. The well is deep. Where can you get this living water? 12Our father Jacob gave us the well. He drank from it himself. So did his sons and his livestock. Are you more important than he is?”

13Jesus answered, “Everyone who drinks this water will be thirsty again. 14But anyone who drinks the water I give them will never be thirsty. In fact, the water I give them will become a spring of water in them. It will flow up into eternal life.”

15The woman said to him, “Sir, give me this water. Then I will never be thirsty. And I won’t have to keep coming here to get water.”

16He told her, “Go. Get your husband and come back.”

17“I have no husband,” she replied.

Jesus said to her, “You are right when you say you have no husband. 18The fact is, you have had five husbands. And the man you live with now is not your husband. What you have just said is very true.”

19“Sir,” the woman said, “I can see that you are a prophet. 20Our people have always worshiped on this mountain. But you Jews claim that the place where we must worship is in Jerusalem.”

21Jesus said, “Woman, believe me. A time is coming when you will not worship the Father on this mountain or in Jerusalem. 22You Samaritans worship what you do not know. We worship what we do know. Salvation comes from the Jews. 23But a new time is coming. In fact, it is already here. True worshipers will worship the Father in the Spirit and in truth. They are the kind of worshipers the Father is looking for. 24God is spirit. His worshipers must worship him in the Spirit and in truth.”

25The woman said, “I know that Messiah is coming.” Messiah means Christ. “When he comes, he will explain everything to us.”

26Then Jesus said, “The one you’re talking about is the one speaking to you. I am he.”

The Disciples Join Jesus Again

27Just then Jesus’ disciples returned. They were surprised to find him talking with a woman. But no one asked, “What do you want from her?” No one asked, “Why are you talking with her?”

28The woman left her water jar and went back to the town. She said to the people, 29“Come. See a man who told me everything I’ve ever done. Could this be the Messiah?” 30The people came out of the town and made their way toward Jesus.

31His disciples were saying to him, “Rabbi, eat something!”

32But he said to them, “I have food to eat that you know nothing about.”

33Then his disciples asked each other, “Did someone bring him food?”

34Jesus said, “My food is to do what my Father sent me to do. My food is to finish his work. 35Don’t you have a saying? You say, ‘It’s still four months until harvest time.’ But I tell you, open your eyes! Look at the fields! They are ripe for harvest right now. 36Even now the one who gathers the crop is getting paid. They are already harvesting the crop for eternal life. So the one who plants and the one who gathers can now be glad together. 37Here is a true saying. ‘One plants and another gathers.’ 38I sent you to gather what you have not worked for. Others have done the hard work. You have gathered the benefits of their work.”

Many Samaritans Believe in Jesus

39Many of the Samaritans from the town of Sychar believed in Jesus. They believed because of what the woman had said about him. She said, “He told me everything I’ve ever done.” 40Then the Samaritans came to him and tried to get him to stay with them. So he stayed two days. 41Because of what he said, many more people became believers.

42They said to the woman, “We no longer believe just because of what you said. We have now heard for ourselves. We know that this man really is the Savior of the world.”

Jesus Heals an Official’s Son

43After the two days, Jesus left for Galilee. 44He himself had pointed out that a prophet is not respected in his own country. 45When he arrived in Galilee, the people living there welcomed him. They had seen everything he had done in Jerusalem at the Passover Feast. That was because they had also been there.

46Once more, Jesus visited Cana in Galilee. Cana is where he had turned the water into wine. A royal official was there. His son was sick in bed at Capernaum. 47The official heard that Jesus had arrived in Galilee from Judea. So he went to Jesus and begged him to come and heal his son. The boy was close to death.

48Jesus told him, “You people will never believe unless you see signs and wonders.”

49The royal official said, “Sir, come down before my child dies.”

50“Go,” Jesus replied. “Your son will live.”

The man believed what Jesus said, and so he left. 51While he was still on his way home, his slaves met him. They gave him the news that his boy was living. 52He asked what time his son got better. They said to him, “Yesterday, at one o’clock in the afternoon, the fever left him.”

53Then the father realized what had happened. That was the exact time Jesus had said to him, “Your son will live.” So he and his whole family became believers.

54This was the second sign that Jesus did after coming from Judea to Galilee.