ዮሐንስ 18 – NASV & NIVUK

New Amharic Standard Version

ዮሐንስ 18:1-40

ኢየሱስ በተቃዋሚዎቹ መያዙ

18፥3-11 ተጓ ምብ – ማቴ 26፥47-56ማር 14፥43-50ሉቃ 22፥47-53

1ኢየሱስ ይህን ካለ በኋላ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ሆኖ የቄድሮንን ሸለቆ ተሻገረ፤ ማዶ ወደ ነበረውም የአትክልት ስፍራ ገቡ።

2ብዙውን ጊዜ ኢየሱስ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር በዚያ ስለሚገናኝ፣ አሳልፎ የሰጠው ይሁዳም ቦታውን ያውቅ ነበር። 3ይሁዳም ወታደሮችን እንዲሁም ከካህናት አለቆችና ከፈሪሳውያን የተላኩ ሎሌዎችን እየመራ ወደ አትክልቱ ስፍራ መጣ፤ እነርሱም ችቦ፣ ፋኖስና የጦር መሣሪያ ይዘው ነበር።

4ኢየሱስም የሚደርስበትን ሁሉ ዐውቆ ወጣና፣ “የምትፈልጉት ማንን ነው?” አላቸው።

5እነርሱም፣ “የናዝሬቱን ኢየሱስን” አሉት።

ኢየሱስም፣ “እርሱ እኔ ነኝ” አላቸው። አሳልፎ የሰጠውም ይሁዳ ከእነርሱ ጋር ቆሞ ነበር። 6ኢየሱስም፣ “እርሱ እኔ ነኝ” ባለ ጊዜ ወደ ኋላ አፈግፍገው መሬት ላይ ወደቁ።

7እንደ ገናም፣ “የምትፈልጉት ማንን ነው?” ሲል ጠየቃቸው።

እነርሱም፣ “የናዝሬቱን ኢየሱስን” አሉት።

8ኢየሱስም መልሶ፣ “ ‘እርሱ እኔ ነኝ’ ብያችኋለሁ እኮ፤ እኔን የምትፈልጉ ከሆነ፣ እነዚህ ይሂዱ ተዉአቸው” አለ፤ 9ይህ የሆነው፣ “ከሰጠኸኝ ከእነዚህ አንድም አልጠፋብኝም” ብሎ የተናገረው ቃል እንዲፈጸም ነው።

10ሰይፍ ይዞ የነበረው ስምዖን ጴጥሮስም፣ ሰይፉን መዝዞ የሊቀ ካህናቱን አገልጋይ ቀኝ ጆሮ ቈረጠ፤ የአገልጋዩም ስም ማልኮስ ይባል ነበር።

11ኢየሱስም ጴጥሮስን፣ “ሰይፍህን ወደ ሰገባው መልስ! አብ የሰጠኝን ጽዋ አልጠጣምን?” አለው።

ኢየሱስ በሊቀ ካህናቱ በሐና ፊት ቀረበ

18፥1213 ተጓ ምብ – ማቴ 26፥57

12ወታደሮቹም ከአዛዣቸውና ከአይሁድ ሎሌዎች ጋር በመሆን ኢየሱስን ያዙት፤ አስረውም፣ 13በመጀመሪያ የቀያፋ አማት ወደ ነበረው ወደ ሐና አመጡት፤ ቀያፋም የዓመቱ ሊቀ ካህናት ነበር። 14ቀያፋም ለሕዝቡ ሲባል አንድ ሰው ቢሞት ይሻላል ብሎ አይሁድን የመከረ ነበር።

የጴጥሮስ ክሕደት

18፥16-18 ተጓ ምብ – ማቴ 26፥6970ማር 14፥66-68ሉቃ 22፥55-57

15ስምዖን ጴጥሮስና አንድ ሌላ ደቀ መዝሙር ኢየሱስን ተከተሉት። ይህም ደቀ መዝሙር በሊቀ ካህናቱ ይታወቅ ስለ ነበር፣ ከኢየሱስ ጋር ወደ ሊቀ ካህናቱ ግቢ ገባ፤ 16ጴጥሮስ ግን ከበሩ ውጭ ቀረ። በሊቀ ካህናቱ የታወቀው ሌላው ደቀ መዝሙርም ተመለሰና በር ጠባቂዋን አነጋግሮ ጴጥሮስን ይዞት ገባ።

17በር ጠባቂዋም ጴጥሮስን፣ “አንተ ከዚህ ሰው ደቀ መዛሙርት አንዱ አይደለህምን?” አለችው።

እርሱም፣ “አይደለሁም” አለ።

18ብርድ ስለ ነበር አገልጋዮቹና ሎሌዎቹ ባያያዙት የከሰል ፍም ዙሪያ ለመሞቅ ቆመው ሳሉ፣ ጴጥሮስም ከእነርሱ ጋር ቆሞ እሳት ይሞቅ ነበር።

ኢየሱስ በሊቀ ካህናቱ ፊት መቅረቡ

18፥19-24 ተጓ ምብ – ማቴ 26፥59-68ማር 14፥55-65ሉቃ 22፥63-71

19በዚያን ጊዜ ሊቀ ካህናቱ ኢየሱስን ስለ ደቀ መዛሙርቱና ስለ ትምህርቱ ጠየቀው።

20ኢየሱስም እንዲህ ሲል መለሰለት፤ “እኔ ለዓለም በግልጽ ተናግሬአለሁ፤ አይሁድ በተሰበሰቡበት ምኵራብ፣ በቤተ መቅደስም ሁልጊዜ አስተምሬአለሁ፤ በስውር የተናገርሁት የለም። 21ለምን እኔን ትጠይቀኛለህ? የሰሙኝን ጠይቃቸው፤ እነሆ፤ የተናገርሁትን እነርሱ ያውቃሉ።”

22ኢየሱስ ይህን በተናገረ ጊዜ፣ አጠገቡ ቆመው ከነበሩት ሎሌዎች አንዱ፣ “ለሊቀ ካህናቱ የምትመልሰው እንዲህ ነውን?” ብሎ በጥፊ መታው።

23ኢየሱስም፣ “ክፉ ተናግሬ ከሆነ ክፉ መናገሬን መስክር፤ እውነት ከተናገርሁ ግን ለምን ትመታኛለህ?” አለው። 24ሐናም ኢየሱስ ታስሮ እንዳለ ወደ ሊቀ ካህናቱ ወደ ቀያፋ ላከው።18፥24 ወይም ሐናም ወደ ቀያፋ እንደ ታሰረ ላከው

የጴጥሮስ ሁለተኛና ሦስተኛ ክሕደት

18፥25-27 ተጓ ምብ – ማቴ 26፥71-75ማር 14፥69-72ሉቃ 22፥58-62

25ስምዖን ጴጥሮስም ቆሞ እሳት ሲሞቅ፣ “አንተ ከእርሱ ደቀ መዛሙርት አንዱ አይደለህምን?” አሉት።

እርሱም፣ “አይደለሁም” ሲል ካደ።

26ከሊቀ ካህናቱ አገልጋዮች አንዱ ጴጥሮስ ጆሮውን የቈረጠው ሰው ዘመድ፣ “በአትክልቱ ስፍራ አንተን ከእርሱ ጋር አላየሁህም?” ሲል ጠየቀው። 27ጴጥሮስም እንደ ገና ካደ፤ ወዲያውም ዶሮ ጮኸ።

ኢየሱስ በጲላጦስ ፊት

18፥29-40 ተጓ ምብ – ማቴ 27፥11-1820-23ማር 15፥2-15ሉቃ 23፥2318-25

28አይሁድም ኢየሱስን ከቀያፋ ወደ ሮማዊው ገዥ ግቢ ይዘውት ሄዱ፤ ጊዜውም ማለዳ ነበር። አይሁድም ፋሲካን መብላት እንዲችሉ፣ ላለመርከስ ወደ ገዥው ግቢ አልገቡም። 29ስለዚህ ጲላጦስ ወደ እነርሱ ወጥቶ፣ “በዚህ ሰው ላይ የምታቀርቡት ክስ ምንድን ነው?” ብሎ ጠየቃቸው።

30እነርሱም፣ “ይህ ሰው ወንጀለኛ ባይሆን ኖሮ፣ አንተ ፊት ባላቀረብነውም ነበር” ብለው መለሱለት።

31ጲላጦስም፣ “እናንተ ራሳችሁ ወስዳችሁ በሕጋችሁ መሠረት ፍረዱበት” አላቸው።

አይሁድም፣ “እኛማ በማንም ላይ የሞት ፍርድ ለመፍረድ መብት የለንም” አሉት። 32ይህ የሆነው በምን ዐይነት ሞት እንደሚሞት ለማመልከት ሲል ኢየሱስ የተናገረው ቃል እንዲፈጸም ነው።

33ጲላጦስም ወደ ግቢው ተመልሶ ኢየሱስን አስጠራና፣ “አንተ የአይሁድ ንጉሥ ነህን?” ብሎ ጠየቀው።

34ኢየሱስም፣ “ይህ ሐሳብ የራስህ ነው? ወይስ ሌሎች ስለ እኔ የነገሩህ?” ሲል መለሰለት።

35ጲላጦስም መልሶ፣ “እኔ አይሁዳዊ ነኝን? ወደ እኔ የላኩህ የራስህ ወገኖችና የካህናት አለቆች ናቸው፤ ለመሆኑ ምን አድርገህ ነው?” አለው።

36ኢየሱስም፣ “የእኔ መንግሥት ከዚህ ዓለም አይደለም፤ ቢሆንማ ኖሮ አይሁድ እንዳይዙኝ ሎሌዎቼ በተከላከሉልኝ ነበር፤ አሁን ግን መንግሥቴ ከዚህ አይደለም” አለው።

37ጲላጦስም፣ “ታዲያ፣ ንጉሥ ነህ ማለት ነዋ!” አለው።

ኢየሱስም፣ “እኔ ንጉሥ እንደ ሆንሁ መናገርህ ትክክል ነው፤ የተወለድሁት፣ ወደዚህም ዓለም የመጣሁት ስለ እውነት ለመመስከር ነው፤ ከእውነት የሆነ ሁሉ ይሰማኛል” አለው።

38ጲላጦስም፣ “እውነት ምንድን ነው?” አለው፤ ይህን ከተናገረ በኋላም እንደ ገና ወደ አይሁድ ወጥቶ እንዲህ አላቸው፤ “እኔ የሚያስከስስ በደል አላገኘሁበትም፤ 39ነገር ግን በፋሲካ አንድ እስረኛ እንድፈታላችሁ ልማድ አላችሁ፤ ስለዚህ፣ ‘የአይሁድን ንጉሥ’ እንድፈታላችሁ ትፈልጋላችሁን?”

40እነርሱም እንደ ገና በመጮኽ፣ “የለም፤ እርሱን አይደለም! በርባንን ፍታልን!” አሉ። በርባን ግን ወንበዴ ነበረ።

New International Version – UK

John 18:1-40

Jesus arrested

1When he had finished praying, Jesus left with his disciples and crossed the Kidron Valley. On the other side there was a garden, and he and his disciples went into it.

2Now Judas, who betrayed him, knew the place, because Jesus had often met there with his disciples. 3So Judas came to the garden, guiding a detachment of soldiers and some officials from the chief priests and the Pharisees. They were carrying torches, lanterns and weapons.

4Jesus, knowing all that was going to happen to him, went out and asked them, ‘Who is it you want?’

5‘Jesus of Nazareth,’ they replied.

‘I am he,’ Jesus said. (And Judas the traitor was standing there with them.) 6When Jesus said, ‘I am he,’ they drew back and fell to the ground.

7Again he asked them, ‘Who is it you want?’

‘Jesus of Nazareth,’ they said.

8Jesus answered, ‘I told you that I am he. If you are looking for me, then let these men go.’ 9This happened so that the words he had spoken would be fulfilled: ‘I have not lost one of those you gave me.’18:9 John 6:39

10Then Simon Peter, who had a sword, drew it and struck the high priest’s servant, cutting off his right ear. (The servant’s name was Malchus.)

11Jesus commanded Peter, ‘Put your sword away! Shall I not drink the cup the Father has given me?’

12Then the detachment of soldiers with its commander and the Jewish officials arrested Jesus. They bound him 13and brought him first to Annas, who was the father-in-law of Caiaphas, the high priest that year. 14Caiaphas was the one who had advised the Jewish leaders that it would be good if one man died for the people.

Peter’s first denial

15Simon Peter and another disciple were following Jesus. Because this disciple was known to the high priest, he went with Jesus into the high priest’s courtyard, 16but Peter had to wait outside at the door. The other disciple, who was known to the high priest, came back, spoke to the servant-girl on duty there and brought Peter in.

17‘You aren’t one of this man’s disciples too, are you?’ she asked Peter.

He replied, ‘I am not.’

18It was cold, and the servants and officials stood round a fire they had made to keep warm. Peter also was standing with them, warming himself.

The high priest questions Jesus

19Meanwhile, the high priest questioned Jesus about his disciples and his teaching.

20‘I have spoken openly to the world,’ Jesus replied. ‘I always taught in synagogues or at the temple, where all the Jews come together. I said nothing in secret. 21Why question me? Ask those who heard me. Surely they know what I said.’

22When Jesus said this, one of the officials near by slapped him in the face. ‘Is this the way you answer the high priest?’ he demanded.

23‘If I said something wrong,’ Jesus replied, ‘testify as to what is wrong. But if I spoke the truth, why did you strike me?’ 24Then Annas sent him bound to Caiaphas the high priest.

Peter’s second and third denials

25Meanwhile, Simon Peter was still standing there warming himself. So they asked him, ‘You aren’t one of his disciples too, are you?’

He denied it, saying, ‘I am not.’

26One of the high priest’s servants, a relative of the man whose ear Peter had cut off, challenged him, ‘Didn’t I see you with him in the garden?’ 27Again Peter denied it, and at that moment a cock began to crow.

Jesus before Pilate

28Then the Jewish leaders took Jesus from Caiaphas to the palace of the Roman governor. By now it was early morning, and to avoid ceremonial uncleanness they did not enter the palace, because they wanted to be able to eat the Passover. 29So Pilate came out to them and asked, ‘What charges are you bringing against this man?’

30‘If he were not a criminal,’ they replied, ‘we would not have handed him over to you.’

31Pilate said, ‘Take him yourselves and judge him by your own law.’

‘But we have no right to execute anyone,’ they objected. 32This took place to fulfil what Jesus had said about the kind of death he was going to die.

33Pilate then went back inside the palace, summoned Jesus and asked him, ‘Are you the king of the Jews?’

34‘Is that your own idea,’ Jesus asked, ‘or did others talk to you about me?’

35‘Am I a Jew?’ Pilate replied. ‘Your own people and chief priests handed you over to me. What is it you have done?’

36Jesus said, ‘My kingdom is not of this world. If it were, my servants would fight to prevent my arrest by the Jewish leaders. But now my kingdom is from another place.’

37‘You are a king, then!’ said Pilate.

Jesus answered, ‘You say that I am a king. In fact, the reason I was born and came into the world is to testify to the truth. Everyone on the side of truth listens to me.’

38‘What is truth?’ retorted Pilate. With this he went out again to the Jews gathered there and said, ‘I find no basis for a charge against him. 39But it is your custom for me to release to you one prisoner at the time of the Passover. Do you want me to release “the king of the Jews”?’

40They shouted back, ‘No, not him! Give us Barabbas!’ Now Barabbas had taken part in an uprising.