ዮሐንስ 17 – NASV & HHH

New Amharic Standard Version

ዮሐንስ 17:1-26

ኢየሱስ ስለ ራሱ መጸለዩ

1ኢየሱስ ይህን ከተናገረ በኋላ፣ ወደ ሰማይ ቀና ብሎ እንዲህ ሲል ጸለየ፤

“አባት ሆይ፤ ጊዜው ደርሷል፤ ልጅህ ያከብርህ ዘንድ ልጅህን አክብረው፤ 2ከአንተ ለተቀበላቸው ሁሉ የዘላለምን ሕይወት እንዲሰጥ፣ በሰው ሁሉ ላይ ሥልጣን ሰጥተኸዋልና። 3እውነተኛ አምላክ የሆንኸውን አንተንና የላክኸውንም ኢየሱስ ክርስቶስን ያውቁ ዘንድ ይህች የዘላለም ሕይወት ናት። 4የሰጠኸኝን ሥራ በመፈጸም በምድር አከበርሁህ። 5እንግዲህ አባት ሆይ፤ ዓለም ሳይፈጠር ከአንተ ጋር በነበረኝ ክብር በአንተ ዘንድ አክብረኝ።

ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ ጸለየ

6“ለእነዚህ ከዓለም ለሰጠኸኝ ሰዎች ስምህን ገልጬላቸዋለሁ። የአንተ ነበሩ ለእኔ ሰጠኸኝ፤ እነርሱም ቃልህን ጠብቀዋል። 7የሰጠኸኝ ሁሉ ከአንተ እንደ ሆነ አሁን ዐውቀዋል፤ 8ምክንያቱም የሰጠኸኝን ቃል ሰጥቻቸው ተቀብለዋል፤ እኔም ከአንተ እንደ ወጣሁ በርግጥ ዐውቀዋል፤ አንተ እንደ ላክኸኝም አምነዋል፤ 9እነርሱ የአንተ ስለሆኑ እጸልይላቸዋለሁ፤ ለሰጠኸኝና የአንተ ለሆኑት እንጂ ለዓለም አልጸልይም። 10የእኔ የሆነው ሁሉ የአንተ ነው፤ የአንተ የሆነውም ሁሉ የእኔ ነው፤ በእነርሱም ከብሬአለሁ። 11ከእንግዲህ እኔ በዓለም አልቈይም፤ እነርሱ ግን በዓለም ውስጥ ናቸው፤ እኔም ወደ አንተ መምጣቴ ነው። ቅዱስ አባት ሆይ፤ እኛ አንድ እንደ ሆንን፣ እነርሱም አንድ እንዲሆኑ በሰጠኸኝ በስምህ ጠብቃቸው። 12እኔ ከእነርሱ ጋር ሳለሁ፣ በሰጠኸኝ ስም ከለልኋቸው፤ ጠበቅኋቸውም፤ የመጽሐፍ ቃል እንዲፈጸም ከአንዱ ከጥፋት ልጅ በቀር ከእነርሱ ማንም አልጠፋም።

13“አሁን ወደ አንተ መምጣቴ ነው፤ ነገር ግን ደስታዬ በእነርሱ ዘንድ የተሟላ እንዲሆን፣ አሁን በዓለም እያለሁ ይህን እናገራለሁ። 14ቃልህን ሰጥቻቸዋለሁ፤ እኔ ከዓለም እንዳይደለሁ፣ እነርሱም ከዓለም ባለመሆናቸው ዓለም ጠልቷቸዋል። 15የምለምንህም ከክፉው እንድትጠብቃቸው እንጂ፣ ከዓለም እንድታወጣቸው አይደለም። 16እኔ ከዓለም እንዳልሆንሁ ሁሉ፣ እነርሱም ከዓለም አይደሉም። 17ቃልህ እውነት ነው፤ በእውነትህ ቀድሳቸው17፥17 በግሪኩ ሀጊያዞ የሚለው ቅዱስ ለሆነ ተግባር መለየት ወይም መቀደስ ማለት ነው፤ 19 ይመ 18አንተ ወደ ዓለም እንደ ላክኸኝ እኔም ወደ ዓለም ልኬአቸዋለሁ። 19እነርሱ በእውነት የተቀደሱ እንዲሆኑ፣ ራሴን ስለ እነርሱ ቀድሻለሁ።”

ኢየሱስ ለአማኞች ሁሉ ጸለየ

20“የእነርሱን ትምህርት ተቀብለው በእኔ ለሚያምኑ ጭምር እንጂ ለእነዚህ ብቻ አልጸልይም፤ 21ይህም፣ አባት ሆይ፤ አንተ በእኔ፣ እኔም በአንተ እንዳለሁ ሁሉም አንድ እንዲሆኑ፣ እንዲሁም አንተ እኔን እንደ ላክኸኝ ዓለም ያምን ዘንድ፣ እነርሱም በእኛ እንዲሆኑ ነው። 22እኛ አንድ እንደ ሆንን እነርሱም አንድ እንዲሆኑ፣ የሰጠኸኝን ክብር ሰጥቻቸዋለሁ። 23ይህም እኔ በእነርሱ፣ አንተም በእኔ መሆንህ ነው። አንተ እንደ ላክኸኝና እኔን በወደድኸኝ መጠን እነርሱንም እንደ ወደድሃቸው ዓለም ያውቅ ዘንድ፣ አንድነታቸው ፍጹም ይሁን።

24“አባት ሆይ፤ እነዚህ የሰጠኸኝ፣ እኔ ባለሁበት እንዲሆኑ ዓለም ሳይፈጠር ስለ ወደድኸኝ የሰጠኸኝንም ክብሬን እንዲያዩ እፈልጋለሁ።

25“ጻድቅ አባት ሆይ፤ ዓለም ባያውቅህም፣ እኔ ዐውቅሃለሁ፤ እነዚህም አንተ እንደ ላክኸኝ ያውቃሉ። 26ለእኔ ያለህ ፍቅር በእነርሱ እንዲሆን፣ እኔም በእነርሱ እንድሆን፣ አንተን እንዲያውቁ17፥26 በግሪኩ ስምህን እንዲያወቁ ይላል። አድርጌአለሁ፤ እንዲያውቁህም አደርጋለሁ።”

Habrit Hakhadasha/Haderekh

הבשורה על-פי יוחנן 17:1-26

1בסיימו לדבר נשא ישוע את עיניו השמימה ואמר: ”אבי, הגיעה השעה; פאר את בנך כדי שבנך יפאר אותך. 2הרי נתת לו סמכות וכוח על כל בני־האדם, כדי שיעניק חיי עולם לכל מי שנתת לו. 3חיי עולם פירושם להכיר אותך, אלוהי האמת לבדו, ואת ישוע המשיח אשר שלחת. 4סיימתי את המשימה שהטלת עלי, וכך פארתי אותך על־פני הארץ. 5עתה, אבי, פאר אותי בכבוד שהיה לי איתך עוד לפני בריאת העולם.

6”סיפרתי על אודותיך לכל האנשים שנתת לי בעולם. למעשה הם היו שלך תמיד; אתה נתת לי אותם והם שמעו בקולך. 7עתה הם יודעים שכל מה שנתת לי ממך הוא, 8כי מסרתי להם את המצוות שמסרת לי. הם קיבלו אותן, והם יודעים בבטחון שבאתי לעולם מעמך ושאתה שלחת אותי.

9”איני מתפלל בעד העולם כולו, אלא בעד אלה שנתת לי, כי הם שייכים לך. 10אלה שהם שלי הם שלך, ושלך הם שלי, ולכן הם תפארתי. 11כעת אני עוזב את העולם ומשאיר אותם כאן. אבי הקדוש, אני בא אליך ומבקש ממך: שמור על כל אלה שנתת לי, כדי שיתאחדו ויהיו לאחד – כמונו. 12בהיותי כאן בעולם שמרתי על אלה שנתת לי אך אחד מהם לא אבד, מלבד בן־הגיהינום שבו נתקיימה הנבואה שבכתבי־הקודש.

13”עכשיו אני בא אליך. סיפרתי להם דברים רבים בהיותי עמם, כדי שיימלאו בשמחתי, 14ומסרתי להם את מצוותיך. העולם שונא אותם, כי אינם שייכים לו, כשם שאני איני שייך לעולם. 15אני לא מבקש ממך להוציא אותם מהעולם, אלא לשמרם מהרע. 16הם אינם שייכים לעולם הזה, כשם שאני איני שייך לעולם הזה. 17למד אותם את דבר האמת, כדי שיהיו קדושים וטהורים. 18כשם ששלחת אותי אל העולם כך גם אני שולח אותם אל העולם. 19אני מוסר את עצמי למענם, כדי שיגדלו באמת ובקדושה.

20”אינני מתפלל רק בעד אלה כאן, אלא גם בעד אלה שיאמינו בי בעתיד, לאחר שישמעו את עדויות המאמינים. 21אני מתפלל שהם יהיו מאוחדים כמונו; שהם יהיו בנו כשם שאתה בי ואני בך, כדי שהעולם יאמין שאתה שלחת אותי.

22”נתתי להם את הכבוד שנתת לי, כדי שיהיו מאוחדים כשם שאנחנו מאוחדים – 23אני בהם ואתה בי, כדי שאחדותם תהיה שלמה, וכדי שהעולם ידע שאתה שלחתני ושאתה אוהב אותם כמו שאתה אוהב אותי. 24אבי, אני רוצה שאלה אשר נתת לי יהיו במקום שבו אהיה, כדי שיוכלו לראות את התפארת והכבוד שהענקת לי על שום שאהבת אותי עוד לפני בריאת העולם.

25”הו, אבי הצדיק, העולם אינו מכיר אותך, אבל אני מכיר אותך, והתלמידים שנתת לי יודעים שאתה שלחתני. 26אני הודעתי להם את שמך, ואוסיף להודיע, כדי שהם יאהבו אותי כשם שאתה אוהב אותי וכדי שגם אני אהיה בהם.“