ዮሐንስ 16 – NASV & HHH

New Amharic Standard Version

ዮሐንስ 16:1-33

1“ይህን ሁሉ የነገርኋችሁ እንዳትሰናከሉ ነው። 2ከምኵራብ ያስወጧችኋል፤ እንዲያውም የሚገድላችሁ ሁሉ እግዚአብሔርን እንዳገለገለ የሚቈጥርበት ጊዜ ይመጣል። 3ይህን ሁሉ የሚያደርጉባችሁ፣ አብን ወይም እኔን ስላላወቁ ነው። 4አስቀድሜ ይህን የነገርኋችሁ ጊዜው ሲደርስ እንድታስታውሱ ነው፤ ከእናንተ ጋር ስለ ነበርሁ፣ ይህን ከመጀመሪያው አልነገርኋችሁም።

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ

5“እንግዲህ ወደ ላከኝ እሄዳለሁ፤ ይሁን እንጂ ከእናንተ፣ ‘የምትሄደው የት ነው?’ ብሎ የሚጠይቀኝ የለም። 6ይህን በመናገሬም ልባችሁ በሐዘን ተሞልቷል፤ 7ነገር ግን፣ እውነት እላችኋለሁ፤ መሄዴ ይበጃችኋል። እኔ ካልሄድሁ አጽናኙ ወደ እናንተ አይመጣም፤ ከሄድሁ ግን እርሱን ወደ እናንተ እልካለሁ፤ 8በሚመጣበትም ጊዜ ዓለምን ስለ ኀጢአት16፥8 ወይም የዓለምን ኀጢአት ይገልጣል፣ ስለ ጽድቅና ስለ ፍርድ ይወቅሣል። 9ስለ ኀጢአት ሲባል፣ ሰዎች በእኔ ስለማያምኑ ነው፤ 10ስለ ጽድቅ፣ ወደ አብ ስለምሄድና ከእንግዲህ ስለማታዩኝ ነው፤ 11ስለ ፍርድም፣ የዚህ ዓለም ገዥ ስለ ተፈረደበት ነው።

12“ብዙ የምነግራችሁ ነበረኝ፤ አሁን ግን ልትሸከሙት አትችሉም። 13የእውነት መንፈስ በመጣ ጊዜ ወደ እውነት ሁሉ ይመራችኋል። እርሱ ከራሱ አይናገርም፤ የሚሰማውን ብቻ ይናገራል፤ እንዲሁም ወደ ፊት ስለሚሆነው ይነግራችኋል፤ 14የእኔ ከሆነው ወስዶ እንድታውቁ በማድረግ ያከብረኛል። 15የአብ የሆነው ሁሉ የእኔ ነው፤ እንግዲህ፣ ‘የእኔ ከሆነው ወስዶ እንድታውቁ ያደርጋል’ ያልኋችሁ ለዚሁ ነው።

16“ከጥቂት ጊዜ በኋላ አታዩኝም፤ ይሁን እንጂ ከጥቂት ጊዜ በኋላ ደግሞ ታዩኛላችሁ።”

የደቀ መዛሙርት ሐዘን ወደ ደስታ መለወጥ

17ከደቀ መዛሙርቱም አንዳንዶቹ፣ “ ‘ከጥቂት ጊዜ በኋላ አታዩኝም፤ ይሁን እንጂ ከጥቂት ጊዜ በኋላ ደግሞ ታዩኛላችሁ’ እንዲሁም፣ ‘ወደ አብ ስለምሄድ’ ሲል ምን ማለቱ ነው?” ተባባሉ፤ 18“ ‘ጥቂት ጊዜ’ ማለቱስ ምን ይሆን? የሚለውም ነገር አልገባንም” እያሉ ይጠያየቁ ነበር።

19ኢየሱስም ሊጠይቁት እንደ ፈለጉ ባወቀ ጊዜ እንዲህ አላቸው፤ “እኔ፣ ‘ከጥቂት ጊዜ በኋላ አታዩኝም፤ ይሁን እንጂ ከጥቂት ጊዜ በኋላ ደግሞ ታዩኛላችሁ’ ስላልኋችሁ፣ ምን ማለቴ እንደ ሆነ እርስ በርሳችሁ ትጠያየቃላችሁ? 20እውነት እላችኋለሁ፤ እናንተ ታለቅሳላችሁ፤ ታዝናላችሁም፤ ዓለም ግን ሐሤት ያደርጋል፤ ይሁን እንጂ ሐዘናችሁ ወደ ደስታ ይለወጣል። 21ሴት ቀኗ ደርሶ ስትወልድ ትጨነቃለች፤ ከተገላገለች በኋላ ግን፣ ሰው ወደ ዓለም ስለ መጣ ጭንቋን ትረሳለች፤ 22ለእናንተም እንደዚሁ አሁን የሐዘን ጊዜ ነው፤ ሆኖም እንደ ገና ስለማያችሁ ደስ ይላችኋል፤ ደስታችሁንም የሚወስድባችሁ የለም። 23በዚያ ቀን ከእኔ ምንም አትለምኑም፤ እውነት እላችኋለሁ፤ አብ በስሜ የምትለምኑትን ሁሉ ይሰጣችኋል። 24እስከ አሁን በስሜ ምንም አልለመናችሁም፤ ለምኑ ትቀበላላችሁ፤ ደስታችሁም ሙሉ ይሆናል።

25“እስከ አሁን የነገርኋችሁ በምሳሌ ቢሆንም እንኳ፣ ከእንግዲህ ግን ስለ አብ በምሳሌ ሳይሆን በግልጽ የምናገርበት ጊዜ ይመጣል። 26በዚያ ቀን በስሜ ትለምናላችሁ፤ ይህም በእናንተ ፈንታ አብን እለምናለሁ ማለቴ አይደለም፤ 27ስለ ወደዳችሁኝና ከእግዚአብሔርም እንደ ወጣሁ ስላመናችሁ አብ ራሱ ይወድዳችኋል። 28ከአብ ወጥቼ ወደ ዓለም መጥቻለሁ፤ አሁን ግን ዓለምን ትቼ ወደ አብ እሄዳለሁ።”

29ከዚያም ደቀ መዛሙርቱ እንዲህ አሉ፤ “አሁንም እኮ ያለ ምሳሌ በግልጽ እየተናገርህ ነው። 30አሁን ሁሉን ነገር እንደምታውቅና ማንም ሊጠይቅህ እንደማያስፈልግ ተረድተናል፤ ይህም ከእግዚአብሔር እንደ ወጣህ እንድናምን አድርጎናል።”

31ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አላቸው፤ “አሁንስ አመናችሁ ማለት ነው?16፥31 ወይም በስተ መጨረሻው አመናችሁ! 32እነሆ፤ ሁላችሁም በየፊናችሁ የምትበታተኑበት ጊዜ ይመጣል፤ ያም ጊዜ አሁን ነው። እኔንም ብቻዬን ትተዉኛላችሁ፤ ይሁን እንጂ አባቴ ከእኔ ጋር ስለሆነ ብቻዬን አይደለሁም።

33“በእኔ ሰላም እንዲኖራችሁ፣ ይህን ነግሬአችኋለሁ። በዓለም ሳላችሁ መከራ አለባችሁ፤ ነገር ግን አይዟችሁ፤ እኔ ዓለምን አሸንፌዋለሁ።”

Habrit Hakhadasha/Haderekh

הבשורה על-פי יוחנן 16:1-33

1”סיפרתי לכם את כל הדברים האלה כדי שתדעו מה מצפה לכם ולא תופתעו או תיבהלו. 2יגרשו אתכם מבתי־הכנסת, ואף יגיע הזמן שהרוצחים אתכם יחשבו שהם עושים את רצון אלוהים! 3הם יעשו כל זאת מפני שאינם מכירים את אבי ואותי. 4אני מספר לכם את כל הדברים האלה כדי שבבוא העת תיזכרו שהזהרתי אתכם. לא סיפרתי לכם זאת מקודם, מפני שעדיין הייתי עמכם.

5”אולם עתה אני חוזר אל שולחי, ואיש מכם אינו מתעניין לדעת לאן אני הולך. 6דברי רק העציבו אתכם. 7האמת היא כי מוטב שאלך, אחרת לא יבוא המנחם. אם אלך הוא יבוא, מפני שאשלח אותו אליכם.

8”כאשר יבוא המנחם הוא ילמד את העולם מהי משמעות החטא, הצדק והמשפט. 9הוא יוציא לאור את חטא העולם, משום שלא האמינו בי. 10הוא יראה להם מהו הצדק האמתי, כי אני חוזר אל אבי ושוב לא תראו אותי. 11הוא ילמד אותם את משמעות המשפט, כי שליט העולם הזה (השטן) כבר נשפט ונדון.

12”הייתי רוצה לומר לכם עוד דברים רבים, אבל אינכם מסוגלים להבינם עדיין. 13כאשר יבוא אליכם רוח האמת הוא יוביל אתכם אל כל האמת, כי אין הוא מדבר על דעת עצמו; הוא יספר לכם את אשר שמע. הוא יספר לכם גם על העתיד. 14הוא יפאר אותי ויביא לי כבוד רב בהראותו לכם את תפארתי. 15כל תפארתו היא תפארתי, ומשום כך אמרתי לכם שהרוח יביא לי כבוד רב בהראותו לכם את תפארתי. 16בעוד זמן מה אלך ושוב לא תראו אותי, אך כעבור זמן מה תראו אותי בשנית, כי אני הולך אל אבי.“

17אחדים מתלמידיו לא הבינו את דבריו. ”למה הוא מתכוון באמרו שבעוד זמן מה נראה אותו בשנית, כי הוא הולך אל אביו?“ שאלו איש את רעהו. 18”למה הוא מתכוון באמרו ’זמן מה‘?“ תמהו.

19ישוע ידע מה הטריד אותם ולכן שאל: ”האם אתם תוהים למה התכוונתי? 20אני אומר לכם באמת וברצינות: העולם ישמח ויגיל על מה שיקרה לי, ואילו אתם תבכו. אבל צערכם יהפוך לשמחה נפלאה, כאשר תראו אותי שנית. 21שמחה זו תדמה לשמחתה של יולדת השוכחת את חבלי הלידה לאחר הולדת תינוקה, כי היא נמלאת שמחה וגיל על כך שאדם נולד לעולם. 22עכשיו אתם עצובים, אולם אשוב לראותכם, ואז תשמחו מאוד ואיש לא יוכל להשבית את שמחתכם. 23ביום ההוא לא יהיה עליכם לבקש ממני דבר, כי תוכלו לבקש את הדבר מאבי, והוא ייתן לכם כל מה שתבקשו ממנו בשמי. 24עד עתה לא ביקשתם דבר בשמי; בקשו ותקבלו, כדי שתימלאו שמחה רבה.

25”דיברתי אליכם במשלים וחידות, אולם יבוא יום שאדבר אליכם על אבי בבירור ולא עוד בחידות ובמשלים. 26ביום ההוא תוכלו לבקש בשמי כל דבר, ולא אצטרך יותר לבקש מאבי שיתן לכם אותו. 27כי אבי אוהב אתכם משום שאתם אוהבים אותי ומאמינים שיצאתי ממנו. 28כן, יצאתי מאבי ובאתי לעולם. כעת אני עוזב את העולם וחוזר לאבי.“

29”סוף סוף אתה מדבר דברים ברורים ולא בחידות ובמשלים“, קראו תלמידיו בהקלה. 30”עתה אנו יודעים שאתה יודע הכל, ואיננו צריכים לשאול אותך יותר שאלות. אנו מאמינים שבאת מאלוהים.“

31”אתם מאמינים לי לבסוף?“ שאל ישוע. 32”אולם יגיע הזמן – למעשה הוא כבר הגיע – שכולכם תתפזרו איש לביתו ותעזבוני לבדי. אך לא אהיה לבדי כי אבי עמדי. 33אמרתי לכם את כל הדברים האלה כדי שלבכם ישקוט ולא תדאגו. כאן בעולם יהיו לכם קשיים וצרות, אולם חיזקו ואימצו, כי אני ניצחתי את העולם!“