ዮሐንስ 14 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

ዮሐንስ 14:1-31

ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን አበረታታ

1“ልባችሁ አይጨነቅ፤ በእግዚአብሔር እመኑ14፥1 ወይም እናንተ በእግዚአብሔር ታምናላችሁ፤ በእኔም ደግሞ እመኑ። 2በአባቴ ቤት ብዙ መኖሪያ አለ፤ ይህ ባይሆንማ ኖሮ እነግራችሁ ነበር፤ የምሄደውም ስፍራ ላዘጋጅላችሁ ነው። 3ሄጄም ስፍራ ካዘጋጀሁላችሁ በኋላ፣ እኔ ባለሁበት እናንተም ከእኔ ጋር እንድትሆኑ ልወስዳችሁ ዳግመኛ እመጣለሁ። 4እኔ ወደምሄድበትም ስፍራ የሚያደርሰውን መንገድ ታውቃላችሁ።”

ወደ አብ የሚያደርሰው መንገድ

5ቶማስም፣ “ጌታ ሆይ፤ ወዴት እንደምትሄድ አናውቅም፤ ታዲያ፣ መንገዱን እንዴት ማወቅ እንችላለን?” አለው።

6ኢየሱስም እንዲህ አለው፤ “መንገዱ እኔ ነኝ፤ እውነትና ሕይወትም እኔው ነኝ፤ በእኔ በኩል ካልሆነ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም። 7እኔን ብታውቁኝ ኖሮ አባቴንም ባወቃችሁት ነበር።14፥7 አንዳንድ የጥንት ቅጆች በርግጥ እኔን ብታውቁ አባቴንም ታውቃላችሁ ይላሉ። ከአሁን ጀምሮ ግን ታውቁታላችሁ፤ አይታችሁታልም።”

8ፊልጶስም፣ “ጌታ ሆይ፤ አብን አሳየንና ይበቃናል” አለው።

9ኢየሱስም እንዲህ አለው፤ “አንተ ፊልጶስ! ይህን ያህል ጊዜ ከእናንተ ጋር ስኖር አታውቀኝምን? እኔን ያየ አብን አይቷል፤ እንዴትስ፣ ‘አብን አሳየን’ ትላለህ? 10እኔ በአብ እንዳለሁ፣ አብም በእኔ እንዳለ አታምንምን? የምነግራችሁ ቃል ከራሴ አይደለም፤ ነገር ግን ሥራውን የሚሠራው በእኔ የሚኖረው አብ ነው። 11እኔ በአብ እንዳለሁ አብም በእኔ እንዳለ ስነግራችሁ እመኑኝ፤ ሌላው ቢቀር ስለ ድንቅ ሥራዎቹ እንኳ እመኑ። 12እውነት እላችኋለሁ፤ በእኔ የሚያምን እኔ የማደርገውን ሥራ ይሠራል፤ እንዲያውም እኔ ወደ አብ ስለምሄድ፣ ከእነዚህም የሚበልጥ ያደርጋል። 13አብ በወልድ እንዲከብር፣ በስሜ የምትለምኑትን ሁሉ አደርገዋለሁ፤ 14ማንኛውንም ነገር በስሜ ብትለምኑኝ፣ እኔ አደርገዋለሁ።

ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጠ ተስፋ

15“ብትወድዱኝ ትእዛዜን ትጠብቃላችሁ። 16እኔ አብን እለምናለሁ፤ እርሱም ከእናንተ ጋር ለዘላለም የሚኖር ሌላ አጽናኝ ይሰጣችኋል፤ 17እርሱም የእውነት መንፈስ ነው፤ ዓለም ስለማያየውና ስለማያውቀው ሊቀበለው አይችልም። እናንተ ግን፣ አብሯችሁ ስለሚኖርና በውስጣችሁ ስለሚሆን14፥17 አንዳንድ የጥንት ቅጆች በውስጣችሁ ስላለ ይላሉ። ታውቁታላችሁ። 18ወላጅ እንደሌላቸው ልጆች አልተዋችሁም፤ ወደ እናንተ እመጣለሁ። 19ከጥቂት ጊዜ በኋላ፣ ዓለም ከቶ አያየኝም፤ እናንተ ግን ታዩኛላችሁ። እኔ ሕያው ስለሆንሁ እናንተም ሕያዋን ትሆናላችሁ። 20እኔ በአባቴ እንዳለሁ፣ እናንተም በእኔ እንዳላችሁ፣ እኔም ደግሞ በእናንተ እንዳለሁ በዚያ ቀን ትረዳላችሁ። 21የሚወድደኝ ትእዛዜን ተቀብሎ የሚጠብቅ ነው፤ የሚወድደኝንም አባቴ ይወድደዋል፤ እኔም እወድደዋለሁ፤ ራሴንም እገልጥለታለሁ።”

22ከዚያም የአስቆሮቱ ያልሆነው ይሁዳ፣ “ጌታ ሆይ፤ ታዲያ፣ ለዓለም ሳይሆን ራስህን ለእኛ የምትገልጠው እንዴት ነው?” አለው።

23ኢየሱስም እንዲህ አለው፤ “የሚወድደኝ ቢኖር ቃሌን ይጠብቃል፤ አባቴም ይወድደዋል፤ ወደ እርሱ እንመጣለን፤ ከእርሱም ጋር እንኖራለን። 24የማይወድደኝ ቃሌን አይጠብቅም። ይህ የምትሰሙት ቃል የላከኝ የአብ ነው እንጂ የእኔ አይደለም።

25“አሁን ከእናንተ ጋር እያለሁ ይህን ሁሉ ነግሬአችኋለሁ፤ 26አብ በስሜ የሚልከው አጽናኙ መንፈስ ቅዱስ ግን ሁሉን ነገር ያስተምራችኋል፤ እኔ የነገርኋችሁንም ሁሉ ያሳስባችኋል። 27ሰላምን እተውላችኋለሁ፤ ሰላሜን እሰጣችኋለሁ፤ እኔ የምሰጣችሁ ዓለም እንደሚሰጣችሁ አይደለም። ልባችሁ አይጨነቅ፤ አይፍራም።

28“ ‘እሄዳለሁ፤ ተመልሼም ወደ እናንተ እመጣለሁ’ ማለቴን ሰምታችኋል፤ ብትወድዱኝስ አብ ከእኔ ስለሚበልጥ ወደ አብ በመሄዴ ደስ ባላችሁ ነበር፤ 29የተናገርሁት ሲፈጸም እንድታምኑ፣ ከመሆኑ በፊት አሁን ነግሬአችኋለሁ። 30የዚህ ዓለም ገዥ ስለሚመጣ ከእንግዲህ ወዲህ ከእናንተ ጋር ብዙ አልናገርም። እርሱም በእኔ ላይ ሥልጣን የለውም፤ 31ነገር ግን እኔ አብን እንደምወድድ፣ አባቴ ያዘዘኝንም እንደማደርግ ዓለም እንዲያውቅ ነው።

“ተነሡ፤ ከዚህ እንሂድ።

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

約翰福音 14:1-31

耶穌是道路、真理、生命

1耶穌繼續說:「你們心裡不要憂愁,你們要信上帝,也要信我。 2我父的家裡有許多住處,不然我就不會說去為你們安排地方了。 3我安排好了以後,必定回來接你們到我那裡。我在哪裡,讓你們也在哪裡。 4你們知道通往我要去的地方的路。」

5多馬說:「主啊,你要去哪裡,我們還不知道,又怎麼會知道路呢?」

6耶穌說:「我就是道路、真理、生命,若不藉著我,沒有人能到父那裡。 7你們若認識我,也會認識我的父。從現在起,你們不但認識祂,而且也看見祂了。」

8腓力說:「主啊!求你讓我們看看父,我們就心滿意足了。」

9耶穌說:「腓力,我和你們相處了這麼久,你還不認識我嗎?人看見了我,就看見了父,你怎麼說『讓我們看看父』呢? 10難道你不相信我在父裡面,父也在我裡面嗎?我這些話不是憑自己講的,而是住在我裡面的父在做祂自己的工作。 11你們應當相信我在父裡面,父也在我裡面。即使你們不信,也應該因我所做的而信我。 12我實實在在地告訴你們,我所做的事,信我的人也要做,而且要做更大的事,因為我要回到父那裡。 13你們奉我的名無論求什麼,我必應允,好讓父在子身上得到榮耀。 14你們若奉我的名向我求什麼,我必應允。

應許賜下聖靈

15「你們若愛我,就必遵守我的命令。 16我要求父另外賜一位護慰者給你們,祂要永遠和你們同在。 17祂是真理的靈,世人不接受祂,因為他們看不見祂,也不認識祂;但你們卻認識祂,因祂常與你們同在,並且要住在你們裡面。 18我不會撇下你們為孤兒,我必到你們這裡來。 19不久,世人就看不見我了,而你們卻能看見我,因為我活著,你們也要活著。 20到了那一天,你們就知道我在父裡面,你們在我裡面,我也在你們裡面。 21接受我的命令又遵行的,就是愛我的人。愛我的,父必定愛他,我也要愛他,並且要親自向他顯現。」

22猶大,不是後來出賣耶穌的猶大,問耶穌:「主啊,你為什麼只向我們顯現而不向世人顯現呢?」

23耶穌回答說:「愛我的人必遵行我的道,我父也必愛他,並且我們要到他那裡與他同住。 24不愛我的人不會遵行我的道。你們所聽見的道不是出於我自己,而是出於差我來的父。 25我還與你們在一起的時候,將這些事情都告訴了你們。 26但護慰者,就是父為我的名而差來的聖靈,將教導你們一切的事,並使你們想起我對你們說的一切話。 27我把平安留給你們,把我的平安賜給你們,我賜給你們的平安不像世人給的平安。你們心裡不要憂愁,也不要害怕。

28「我對你們說過,我去了還要再回到你們這裡。如果你們真的愛我,就應當為我去父那裡而歡喜快樂,因為父比我大。 29現在事情還沒有發生,我便先告訴你們,到了事情發生的時候,你們就會相信。 30我不再跟你們多談,因為世界的王快要來了。他根本沒有力量勝過我, 31但這是為了讓世人知道我愛父,父怎麼吩咐我,我就怎麼做。起來,我們走吧!」