ዮሐንስ 1 – NASV & SNC

New Amharic Standard Version

ዮሐንስ 1:1-51

ቃል ሥጋ ሆነ

1በመጀመሪያ ቃል ነበረ፤ ቃልም ከእግዚአብሔር ጋር ነበረ፤ ቃልም እግዚአብሔር ነበረ። 2እርሱም በመጀመሪያ ከእግዚአብሔር ጋር ነበረ።

3ሁሉ ነገር በእርሱ ተፈጥሯል፤ ከተፈጠረው ሁሉ ያለ እርሱ የተፈጠረ ምንም የለም። 4ሕይወት በእርሱ ነበረች፤ ይህች ሕይወት የሰው ብርሃን ነበረች። 5ብርሃንም በጨለማ ያበራል፤ ጨለማውም አላሸነፈውም።1፥5 ወይም ጨለማው ግን አላወቀውም

6ከእግዚአብሔር የተላከ ዮሐንስ የተባለ አንድ ሰው ነበረ። 7ሰዎች ሁሉ በእርሱ በኩል እንዲያምኑ፣ ስለ ብርሃን ምስክር ሆኖ ለመቆም መጣ፤ 8ስለ ብርሃን ሊመሰክር መጣ እንጂ እርሱ ራሱ ብርሃን አልነበረም። 9ለሰው ሁሉ ብርሃን ሰጭ የሆነው እውነተኛው ብርሃን ወደ ዓለም እየመጣ ነበር።1፥9 ወይም ይህ ወደ ዓለም ለሚመጣ ሰው ብርሃን የሚሰጥ እውነተኛው ብርሃን ነበረ

10እርሱ በዓለም ውስጥ ነበረ፤ ዓለም የተፈጠረው በእርሱ ቢሆንም እንኳ፣ ዓለም አላወቀውም። 11ወደ ራሱ ወገኖች መጣ፤ የገዛ ወገኖቹ ግን አልተቀበሉትም፤ 12ለተቀበሉትና በስሙ ላመኑት ሁሉ ግን የእግዚአብሔር ልጆች የመሆን መብት ሰጣቸው። 13እነዚህም ከእግዚአብሔር ተወለዱ እንጂ፣ ከደም1፥13 ወይም ከሰው ውሳኔ ወይም ከሥጋ ፈቃድ ወይም ከወንድ ፈቃድ አልተወለዱም።

14ቃልም ሥጋ ሆነ፤ በመካከላችንም ዐደረ፤ እኛም ጸጋንና እውነትን ተሞልቶ ከአባቱ ዘንድ የመጣውን የአንድያ1፥14 ወይም አንድ ልጁ የሆነው ልጅን ክብር አየን።

15ዮሐንስም፣ “ ‘ከእኔ በኋላ የሚመጣው ከእኔ በፊት ስለ ነበረ ከእኔ ይልቃል’ ብዬ የመሰከርሁለት እርሱ ነው” በማለት ጮኾ ስለ እርሱ መሰከረ። 16ከእርሱ ሙላት ሁላችንም በጸጋ ላይ ጸጋ ተቀብለናል፤ 17ሕግ በሙሴ በኩል ተሰጥቶ ነበር፤ ጸጋና እውነት ግን በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል መጣ። 18ከቶውንም እግዚአብሔርን ያየ ማንም የለም፤ ነገር ግን በአብ ዕቅፍ ያለው አንድያ ልጁ1፥18 አንዳንድ ቅጆች አንድ ልጁ ይላሉ። የሆነው አምላክ እርሱ ገለጠው።

መጥምቁ ዮሐንስ ራሱ ክርስቶስ እንዳልሆነ ተናገረ

19አይሁድ፣ ማንነቱን እንዲጠይቁት ካህናትንና ሌዋውያንን ከኢየሩሳሌም ወደ እርሱ ሲልኩ፣ ዮሐንስ የሰጠው ምስክርነት ይህ ነበር።

20ከመመስከርም ወደ ኋላ አላለም፤ “እኔ ክርስቶስ1፥20 ወይም መሲሕ በግሪኩ፣ ክርስቶስ እና በዕብራይስጡ፣ መሲሕ፣ ሁለቱም የተቀባ የሚል ትርጕም አላቸው፤ 25 ይመ አይደለሁም፤” ብሎ በግልጽ መሰከረ።

21እነርሱም፣ “ታዲያ አንተ ማን ነህ? ኤልያስ ነህ?” ብለው ጠየቁት።

እርሱም፣ “አይደለሁም” አለ።

እነርሱም፣ “ታዲያ ነቢዩ ነህ?” አሉት።

እርሱም፣ “አይደለሁም” ሲል መለሰ።

22በመጨረሻም፣ “እንግዲያስ ማን ነህ? ለላኩን ሰዎች መልስ እንድንሰጥ ስለ ራስህ ምን ትላለህ?” አሉት።

23ዮሐንስም በነቢዩ በኢሳይያስ እንደ ተነገረው፣ “ ‘ለጌታ መንገድ አቅኑለት’ እያለ በምድረ በዳ የሚጮኽ ድምፅ እኔ ነኝ” ሲል መለሰ።

24ከተላኩትም ፈሪሳውያን አንዳንዶቹ፣ 25“ታዲያ፣ ክርስቶስ ወይም ኤልያስ ወይም ነቢዩ ካልሆንህ፤ ለምን ታጠምቃለህ?” ብለው ጠየቁት።

26ዮሐንስም እንዲህ ብሎ መለሰላቸው፤ “እኔ በውሃ1፥26 ወይም በውሃ ውስጥ 31 እና 33 ይመ አጠምቃለሁ፤ እናንተ የማታውቁት ግን በመካከላችሁ ቆሟል፤ 27ከእኔ በኋላ የሚመጣው፣ የጫማውን ማሰሪያ ለመፍታት እንኳ የማልበቃ እርሱ ነው።”

28ይህ ሁሉ የሆነው ዮሐንስ ሲያጠምቅ በነበረበት ከዮርዳኖስ ማዶ በቢታንያ ነበር።

የእግዚአብሔር በግ

29ዮሐንስ በማግስቱም፣ ኢየሱስ ወደ እርሱ ሲመጣ አይቶ እንዲህ አለ፤ “እነሆ! የዓለምን ኀጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ፤ 30‘ከእኔ በኋላ የሚመጣው ከእኔ በፊት ስለ ነበር ከእኔ ይልቃል’ ያልሁት እርሱ ነው፤ 31እኔ ራሴ አላወቅሁትም ነበር፤ በውሃ እያጠመቅሁ የመጣሁትም እርሱ በእስራኤል ዘንድ እንዲገለጥ ነው።”

32ከዚያም ዮሐንስ እንዲህ ሲል ምስክርነቱን ሰጠ፤ “መንፈስ እንደ ርግብ ከሰማይ ወርዶ በእርሱ ላይ ሲያርፍ አየሁ፤ 33በውሃ እንዳጠምቅ የላከኝም፣ ‘በመንፈስ ቅዱስ የሚያጠምቀው፣ መንፈስ ሲወርድና በእርሱ ላይ ሲያርፍ የምታየው እርሱ ነው’ ብሎ እስከ ነገረኝ ድረስ እኔም አላወቅሁትም ነበር፤ 34አይቻለሁ፣ እርሱ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ እመሰክራለሁ።”

የመጀመሪያዎቹ የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት

1፥40-42 ተጓ ምብ – ማቴ 4፥18-22ማር 1፥16-20ሉቃ 5፥2-11

35በማግስቱም፣ ዮሐንስ ከሁለቱ ደቀ መዛሙርቱ ጋር እንደ ገና እዚያው ቦታ ነበር፤ 36ኢየሱስንም በዚያ ሲያልፍ አይቶ፣ “እነሆ፤ የእግዚአብሔር በግ!” አለ።

37ሁለቱ ደቀ መዛሙርትም ይህን ሲናገር ሰምተው ኢየሱስን ተከተሉት። 38ኢየሱስም ዘወር ብሎ ሲከተሉት አየና፣ “ምን ትፈልጋላችሁ?” ብሎ ጠየቃቸው።

እነርሱም፣ “ረቢ፣ የት ትኖራለህ?” አሉት፤ “ረቢ” ማለት መምህር ማለት ነው።

39እርሱም፣ “ኑና እዩ” አላቸው።

ስለዚህ ሄደው የት እንደሚኖር አዩ፤ በዚያም ዕለት አብረውት ዋሉ፤ ከቀኑም ዐሥር ሰዓት ያህል ነበር።

40ዮሐንስ የተናገረውን ሰምተው፣ ኢየሱስን ከተከተሉት ከሁለቱ አንዱ የስምዖን ጴጥሮስ ወንድም እንድርያስ ነበር። 41እንድርያስ በመጀመሪያ ያደረገው ወንድሙን ስምዖንን ፈልጎ፣ “መሲሑን አገኘነው” ብሎ መንገር ነው፤ “መሲሕ” ማለት ክርስቶስ ማለት ነው። 42ወደ ኢየሱስም አመጣው።

ኢየሱስም ተመለከተውና፣ “አንተ የዮና ልጅ ስምዖን ነህ፤ ኬፋ ተብለህ ትጠራለህ” አለው፤ “ኬፋ” ማለት ጴጥሮስ ማለት ነው።1፥42 ኬፋ የሚለው የአራማይክ ቃልና ጴጥሮስ የሚለው የግሪኩ ቃል ትርጕም ዐለት ማለት ነው።

ኢየሱስ ፊልጶስንና ናትናኤልን ጠራቸው

43በማግስቱም፣ ኢየሱስ ወደ ገሊላ ለመሄድ ፈለገ፤ ፊልጶስንም አግኝቶ፣ “ተከተለኝ” አለው።

44ፊልጶስም እንደ እንድርያስና እንደ ጴጥሮስ ሁሉ የቤተ ሳይዳ ከተማ ሰው ነበረ። 45ፊልጶስ ናትናኤልን አግኝቶ፣ “ሙሴ በሕግ መጻሕፍት፣ ነቢያትም ስለ እርሱ የጻፉለትን የዮሴፍን ልጅ የናዝሬቱ ኢየሱስን አግኝተነዋል” አለው።

46ናትናኤልም፣ “ከናዝሬት በጎ ነገር ሊወጣ ይችላልን?” አለ።

ፊልጶስም፣ “መጥተህ እይ” አለው።

47ኢየሱስም፣ ናትናኤል ወደ እርሱ ሲመጣ አይቶ፣ “እነሆ፤ ተንኰል የሌለበት እውነተኛ እስራኤላዊ” አለ።

48ናትናኤልም “እንዴት ዐወቅኸኝ?” ሲል ጠየቀው።

ኢየሱስም፣ “ከበለስ ዛፍ ሥር ሳለህ፣ ገና ፊልጶስ ሳይጠራህ አየሁህ” ሲል መለሰለት።

49ናትናኤልም መልሶ፣ “ረቢ አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ነህ፤ አንተ የእስራኤል ንጉሥ ነህ” አለ።

50ኢየሱስም፣ “ያመንኸው ከበለስ ዛፍ ሥር አየሁህ ስላልሁህ ነውን?1፥50 ወይም ከበለስ ዛፍ ሥር አየሁህ ስላልሁህ አመንህ? ገና ከዚህ የሚበልጥ ነገር ታያለህ” አለው፤ 51ጨምሮም፣ “እውነት እላችኋለሁ፣ ሰማይ ተከፍቶ፣ የእግዚአብሔርም መላእክት በሰው ልጅ ላይ ሲወጡና ሲወርዱ ታያላችሁ” አለው።

Slovo na cestu

Jan 1:1-51

Bůh se stal člověkem

1-3Kristus existoval od věčnosti,

byl stále s Bohem Otcem

a byl to Bůh sám.

On byl tvořícím Božím Slovem,

kterým vše vzniklo a trvá.

4Je zdrojem všeho života

a pro lidi světlem na cestě k Bohu.

5To světlo přemáhá temnotu světa,

ale ta ho nikdy nepřekoná.

6Bůh pověřil muže, který se jmenoval Jan (zvaný Křtitel),

7aby svědčil o Ježíši a vedl lidi k víře,

že Ježíš je tím světlem.

8Jan nikdy ani nenaznačil,

že by jím byl on sám.

9Ježíš je to pravé světlo,

které září vstříc každému člověku.

10-11Přišel na zem, kterou stvořil

a k lidem, které miloval,

ale oni ho nepřijali.

12Těm však, kteří ho přece přijali

a uvěřili v něho,

otevřel přístup do Boží rodiny.

13Nestali se jejími členy rodem ani lidským úsilím,

ale Božím působením.

14A věčné Slovo se stalo člověkem,

který žil mezi námi.

Viděli jsme jeho vznešenost,

vznešenost vlastní jedinému Božímu Synu.

Poznali jsme jej plného lásky a pravdy.

15Také Jan Křtitel o něm vydával jasné svědectví: „To je ten, který jde sice za mnou, ale je mnohem významnější a byl dávno přede mnou.“ 16Z jeho bohatství jsme přijímali dar za darem. 17Mojžíšovým prostřednictvím nám Bůh sdělil požadavky svého zákona, ale v Ježíši Kristu jsme se setkali s Božím milosrdenstvím a pravdou. 18Boha nikdo z lidí neviděl; jenom ten, který má k němu blízko jako jediný Syn k Otci, nám o něm sdělil pravdu.

Jan Křtitel objasňuje své poslání

19Z Jeruzaléma přišla za Janem Křtitelem delegace židovských kněží s otázkou, zda je očekávaný Mesiáš – Boží Syn, izraelský král.

20-21„Ne, nejsem Mesiáš,“ řekl jim Jan otevřeně.

„Kdo tedy jsi?“ zeptali se ho znovu. „Jsi prorok Elijáš?“

„Nejsem.“

22„Tak řekni, kdo jsi. Musíme o tobě podat zprávu těm, kteří nás poslali. Jsi tedy jiný Mesiášův předchůdce?“

23„Nedávejte mi žádný titul. Jsem hlas, který na poušti volá: Upravte cestu pro Pána. Tak to předpověděl prorok Izajáš.“ 24-25Protože Janovu odpověď nepochopili, ptali se dál: „Když tedy nejsi Mesiáš, ani jeho předchůdce, proč křtíš?“

26-27Jan odpověděl: „Divíte se, že křtím. Ale co budete říkat tomu muži, který přichází za mnou? Ještě ho neznáte, ale je už mezi vámi. Jemu nejsem hoden ani obuv rozvázat.“ 28To se stalo v Betanii u Jordánu, kde Jan křtil.

Jan Křtitel prohlašuje Ježíše Mesiášem

29Druhého dne spatřil Jan Ježíše, jak k němu přichází. Ukázal na něho a řekl: „Beránek Boží, který bere na sebe hříchy celého světa. 30To o něm jsem vám včera řekl, že za mnou jde mnohem významnější muž, který byl dávno přede mnou. 31Když jsem byl pověřen, abych křtil a připravoval izraelský lid na příchod Mesiáše, ještě jsem nevěděl, kdo to je. 32-34Bůh mi však řekl: ‚Dávej pozor, na koho při křtu sestoupí můj Duch a zůstane na něm. To je ten, kdo bude křtít Duchem svatým.‘ Pak jsem viděl, jak se Boží Duch v podobě holubice snáší z nebe na Ježíše. Do té chvíle jsem ho neznal, ale protože se to na něm vyplnilo, vydávám svědectví, že je Boží Syn.“

První učedníci následují Ježíše

35Příštího dne, asi ve čtyři hodiny odpoledne, stál Jan se dvěma svými učedníky. 36Opět spatřil Ježíše, jak jde okolo a zvolal: „Podívejte se, to je Boží Beránek!“

37Když to Janovi učedníci uslyšeli, vydali se za Ježíšem. 38Ten se po chvíli ohlédl a viděl, že ho oba následují. Zeptal se jich: „Přejete si něco?“

„Mistře,“ odpověděli, „kde bydlíš?“

39„Pojďte se mnou!“ řekl Ježíš. Přijali to pozvání a zůstali ten den u něho.

40Jeden z těch učedníků se jmenoval Ondřej a měl bratra Šimona. 41Po návštěvě u Ježíše vyhledal Ondřej svého bratra a řekl mu: „Nalezli jsme Mesiáše – Krista.“ 42Pak ho přivedl k Ježíšovi. Ten se na něj zahleděl a řekl: „Ty jsi Šimon, Janův syn. Ode dneška se však budeš jmenovat Petr.“

43Příštího dne se Ježíš rozhodl, že půjde do Galileje. Setkal se s Filipem a vyzval ho, aby ho následoval. 44Stejně jako Ondřej a Petr pocházel i Filip z Betsaidy.

45Filip pak vyhledal Natanaela a řekl mu: „Nalezli jsme toho, o kterém hovořil Mojžíš a kterého předpověděli proroci. Jmenuje se Ježíš a je to syn Josefa z Nazaretu.“

46„Může být z Nazaretu něco dobrého?“ zapochyboval Natanael.

„Pojď a přesvědč se sám!“ řekl Filip.

47Když Ježíš spatřil Natanaela, řekl: „To je pravý a bezelstný Izraelec.“

48„Odkud mne znáš?“ zeptal se ho překvapeně Natanael.

„Viděl jsem tě pod fíkovým stromem dříve, než tě našel Filip,“ odpověděl Ježíš.

49Natanael s údivem zvolal: „Mistře, ty jsi Boží Syn a izraelský král.“

50Ježíš mu na to řekl: „Ty mi věříš proto, že jsem ti pověděl, jak jsem tě viděl pod fíkovníkem. 51Uvidíš větší věci a uvěříš, že jsem v neustálém spojení s nebem.“