ያዕቆብ 4 – NASV & NIVUK

New Amharic Standard Version

ያዕቆብ 4:1-17

ራሳችሁን ለእግዚአብሔር አስገዙ

1በእናንተ መካከል ያለው ጦርነትና ጠብ ከየት የመጣ ነው? በውስጣችሁ ከሚዋጉት ከምኞቶቻችሁ አይደለምን? 2ትመኛላችሁ፤ ነገር ግን አታገኙም። ትገድላላችሁ፤ በብርቱም ትመኛላችሁ፤ ልታገኙም አትችሉም። ትጣላላችሁ፤ ትዋጋላችሁ፤ አትለምኑምና ለእናንተ አይሆንም። 3ትለምናላችሁ ግን አትቀበሉም፣ ለራሳችሁ ሥጋዊ ደስታ በማሰብ በክፉ ምኞት ትለምናላችሁና።

4አመንዝሮች ሆይ፤ ከዓለም ጋር ወዳጅነት ከእግዚአብሔር ጋር ጠላትነት መሆኑን አታውቁምን? ስለዚህ የዓለም ወዳጅ መሆን የሚፈልግ ሁሉ የእግዚአብሔር ጠላት ሆኗል። 5ወይስ በውስጣችን ያሳደረው መንፈስ አብዝቶ ይቀናል4፥5 ወይም፣ እግዚአብሔር በውስጣችን እንዲኖር ስላደረገው መንፈስ በቅናት ይመኛል፤ ወይም በውስጣችን እንዲኖር ያደረገው መንፈስ በቅናት ይመኛል ማለት ነው በማለት መጽሐፍ የተናገረው በከንቱ ይመስላችኋልን? 6ነገር ግን ጸጋን አብዝቶ ይሰጠናል፤ መጽሐፍም፣

“እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን ይቃወማል፤

ለትሑታን ግን ጸጋን ይሰጣል”

ያለው ስለዚህ ነው።

7እንግዲህ ራሳችሁን ለእግዚአብሔር አስገዙ፤ ዲያብሎስን ተቃወሙት፤ ከእናንተም ይሸሻል። 8ወደ እግዚአብሔር ቅረቡ፤ እርሱም ወደ እናንተ ይቀርባል። እናንተ ኀጢአተኞች እጃችሁን አንጹ፤ እናንተ በሁለት ሐሳብ የምትዋልሉ ልባችሁን አጥሩ። 9ተጨነቁ፤ ዕዘኑ፤ አልቅሱም። ሳቃችሁ ወደ ሐዘን፣ ደስታችሁም ወደ ትካዜ ይለወጥ። 10በጌታ ፊት ራሳችሁን አዋርዱ፣ እርሱም ከፍ ከፍ ያደርጋችኋል።

11ወንድሞች ሆይ፤ እርስ በርሳችሁ አትወነጃጀሉ፤ ወንድሙን የሚወነጅልና በወንድሙም ላይ የሚፈርድ በሕግ ላይ ክፉ ይናገራል፤ በሕግም ላይ ይፈርዳል። በሕግ ላይ ብትፈርድ ፈራጅ እንጂ ሕግን አድራጊ አይደለህም። 12ሕግን የሚሰጥና የሚፈርድ አንድ ብቻ ነው፤ እርሱም ሊያድንና ሊያጠፋ የሚችል ነው፤ ነገር ግን በባልንጀራህ ላይ የምትፈርድ አንተ ማን ነህ?

ስለ ነገ መመካት

13እናንተ፣ “ዛሬ ወይም ነገ ወደዚህች ወይም ወደዚያች ከተማ እንሄዳለን፤ በእርሷም አንድ ዓመት እንቈያለን፤ እንነግዳለን፤ እናተርፋለንም” የምትሉ እንግዲህ ስሙ። 14ነገ የሚሆነውን እንኳ አታውቁም። ሕይወታችሁ ምንድን ናት? ለጥቂት ጊዜ ታይቶ ኋላ እንደሚጠፋ እንፋሎት ናችሁ። 15ይልቁንም፣ “የጌታ ፈቃድ ቢሆን እንኖራለን፤ ይህን ወይም ያንን እናደርጋለን” ማለት ይገባችኋል። 16አሁን ግን በትዕቢታችሁ ትመካላችሁ፤ እንዲህ ያለው ትምክሕት ሁሉ ክፉ ነው። 17እንግዲህ መልካም የሆነውን ነገር ማድረግ እንዳለበት እያወቀ የማያደርግ ሰው ኀጢአት ያደርጋል።

New International Version – UK

James 4:1-17

Submit yourselves to God

1What causes fights and quarrels among you? Don’t they come from your desires that battle within you? 2You desire but do not have, so you kill. You covet but you cannot get what you want, so you quarrel and fight. You do not have because you do not ask God. 3When you ask, you do not receive, because you ask with wrong motives, that you may spend what you get on your pleasures.

4You adulterous people,4:4 An allusion to covenant unfaithfulness; see Hosea 3:1. don’t you know that friendship with the world means enmity against God? Therefore, anyone who chooses to be a friend of the world becomes an enemy of God. 5Or do you think Scripture says without reason that he jealously longs for the spirit he has caused to dwell in us4:5 Or that the spirit he caused to dwell in us envies intensely; or that the Spirit he caused to dwell in us longs jealously? 6But he gives us more grace. That is why Scripture says:

‘God opposes the proud

but shows favour to the humble.’4:6 Prov. 3:34

7Submit yourselves, then, to God. Resist the devil, and he will flee from you. 8Come near to God and he will come near to you. Wash your hands, you sinners, and purify your hearts, you double-minded. 9Grieve, mourn and wail. Change your laughter to mourning and your joy to gloom. 10Humble yourselves before the Lord, and he will lift you up.

11Brothers and sisters, do not slander one another. Anyone who speaks against a brother or sister4:11 The Greek word for brother or sister (adelphos) refers here to a believer, whether man or woman, as part of God’s family. or judges them speaks against the law and judges it. When you judge the law, you are not keeping it, but sitting in judgment on it. 12There is only one Lawgiver and Judge, the one who is able to save and destroy. But you – who are you to judge your neighbour?

Boasting about tomorrow

13Now listen, you who say, ‘Today or tomorrow we will go to this or that city, spend a year there, carry on business and make money.’ 14Why, you do not even know what will happen tomorrow. What is your life? You are a mist that appears for a little while and then vanishes. 15Instead, you ought to say, ‘If it is the Lord’s will, we will live and do this or that.’ 16As it is, you boast in your arrogant schemes. All such boasting is evil. 17If anyone, then, knows the good they ought to do and doesn’t do it, it is sin for them.