ዘፍጥረት 7 – NASV & BPH

New Amharic Standard Version

ዘፍጥረት 7:1-24

1እግዚአብሔር (ያህዌ) ኖኅን እንዲህ አለው፤ “በዚህ ትውልድ መካከል አንተን ጻድቅ ሆነህ አግኝቼሃለሁና ቤተ ሰብህን በሙሉ ይዘህ ወደ መርከቧ ግባ። 2ከንጹሕ እንስሳት ሁሉ ሰባት ሰባት7፥2 ወይም ሰባት ጥንድ፤ በ3 ም እንዲሁ፤ ተባዕትና እንስት፣ ንጹሕ ካልሆኑት እንስሳት ደግሞ ሁለት ሁለት ተባዕትና እንስት 3እንዲሁም ከወፎች ወገን ሁሉ ሰባት ተባዕትና ሰባት እንስት፣ በምድር ላይ ለዘር እንዲተርፉ ከአንተ ጋር ታስገባለህ። 4ከሰባት ቀን በኋላ አርባ ቀንና አርባ ሌሊት በምድር ላይ ዝናብ አዘንባለሁ፤ የፈጠርሁትንም ሕያው ፍጡር ሁሉ ከምድር ገጽ አጠፋለሁ።”

5ኖኅም እግዚአብሔር (ያህዌ) ያዘዘውን ሁሉ አደረገ።

6የጥፋት ውሃ በምድር ላይ በወረደ ጊዜ ኖኅ የ600 ዓመት ሰው ነበር። 7ኖኅና ወንዶች ልጆቹ፣ ሚስቱና የልጆቹ ሚስቶች ከጥፋት ውሃ ለመትረፍ ወደ መርከቧ ገቡ። 8ንጹሕ ከሆኑትና ንጹሕ ካልሆኑት እንስሳት፣ ከወፎችና በምድር ላይ ከሚሳቡ ፍጡራን ሁሉ ጥንድ ጥንድ፣ 9ተባዕትና እንስት ሆነው ወደ ኖኅ መጡ፤ እግዚአብሔር (ኤሎሂም) ኖኅን ባዘዘውም መሠረት ወደ መርከቧ ገቡ። 10ከሰባት ቀንም በኋላ የጥፋት ውሃ በምድር ላይ መጣ።

11ኖኅ በተወለደ በ 600 ኛው ዓመት፣ በሁለተኛው ወር፣ ከወሩም በዐሥራ ሰባተኛው ቀን፣ በዚያ ቀን የታላቁ ጥልቅ ምንጮች በሙሉ ተነደሉ፤ የሰማይ መስኮቶችም ተከፈቱ፤ 12አርባ ቀንና አርባ ሌሊት በምድር ላይ ዝናብ ዘነበ።

13በዚያኑ ዕለት ኖኅና ልጆቹ ሴም፣ ካምና ያፌት፣ እንዲሁም ሚስቱና ሦስቱ የልጆቹ ሚስቶች ወደ መርከቧ ገቡ። 14ከዱር እንስሳት ከየወገኑ፣ ከቤት እንስሳት ከየወገኑ፣ በምድር ላይ ከሚሳቡ ፍጡራን ከየወገናቸው፣ ከወፎችም ከየወገናቸውና ክንፍ ያላቸው ሁሉ አብረዋቸው ገቡ። 15የሕይወት እስትንፋስ ያለባቸው ፍጡራን በሙሉ ጥንድ ጥንድ እየሆኑ ወደ ኖኅ በመምጣት መርከቧ ውስጥ ገቡ። 16ከሕያዋንም ፍጡራን ሁሉ እግዚአብሔር (ኤሎሂም) ኖኅን ባዘዘው መሠረት ተባዕትና እንስት እየሆኑ ገቡ፤ ከዚያም እግዚአብሔር (ያህዌ) ከውጭ ዘጋበት።

17የጥፋት ውሃም ለአርባ ቀናት ያለ ማቋረጥ በምድር ላይ ዘነበ፤ ውሃው እየጨመረ በሄደ መጠን መርከቧን ከምድር ወደ ላይ አነሣት። 18ውሃው በምድር ላይ በጣም እየጨመረና ከፍ እያለ ሲሄድ፣ መርከቧ በውሃው ላይ ተንሳፈፈች። 19ውሃው በጣም ከፍ በማለቱ፣ ከሰማይ በታች ያሉትን ታላላቅ ተራሮች ሁሉ ሸፈናቸው። 20ውሃው ከተራሮቹ ጫፍ በላይ 7 ሜትር ያህል ከፍ አለ። 21በምድር ላይ የነበሩ ሕያዋን ፍጡራን ሁሉ፦ ወፎች፣ የቤት እንሰሳት፣ የዱር እንስሳት በምድር የሚርመሰመሱ ፍጡራን፣ ሰዎችም በሙሉ ጠፉ። 22በአፍንጫቸው የሕይወት እስትንፋስ ያላቸው በየብስ የነበሩ ፍጡራን ሁሉ ሞቱ። 23ሕይወት ያላቸው ፍጡራን ሁሉ ከምድር ገጽ ጠፉ፤ ሰዎችና እንስሳት በምድር ላይ የሚሳቡ ፍጡራንና የሰማይ ወፎች ከምድር ላይ ጠፉ፤ ኖኅና ከእርሱ ጋር በመርከቧ ውስጥ የነበሩት ብቻ ተረፉ።

24ውሃውም ምድርን ሸፍኖ መቶ አምሳ ቀን ቈየ።

Bibelen på hverdagsdansk

1. Mosebog 7:1-24

Ondskabens konsekvens

1Da Noa var færdig med at bygge arken, sagde Herren til ham: „Du og din familie skal gå om bord i arken, for du er den eneste, jeg kan acceptere blandt menneskene på jorden. 2-3Af alle slags fugle og de dyr, der bruges til ofringer og til mad, skal du tage syv par, en han og en hun, for at de siden hen kan formere sig på jorden. Af de øvrige dyr skal du kun tage ét par, en han og en hun. 4Om syv dage vil jeg sende regn, og det vil blive ved at regne uden ophør i 40 dage.7,4 På hebraisk 40 dage og 40 nætter, hvilket svarer til 40 dage og 39 nætter eller 39 døgn på dansk. Jeg vil udrydde alle levende væsener fra jordens overflade.”

5Noa gjorde, som Herren havde befalet ham: 6-11Han bad sin kone, sine sønner og deres koner om at gøre sig klar til at gå ind i arken, så de kunne blive reddet fra oversvømmelsen. Alle dyrearter kom parvis ind i arken, som Herren havde befalet. Syv dage efter at Gud havde talt, begyndte regnen. Jordens kilder og himlens sluser blev åbnet på den 17. dag i den anden måned i det år, hvor Noa blev 600, 12og det regnede uafbrudt i de næste 40 dage. 13På den dag, da regnen begyndte, gik Noa ind i arken sammen med sin kone og sine sønner, Sem, Kam og Jafet, og deres koner. 14Alle de forskellige dyr var allerede kommet ind i arken, både de tamme og vilde dyr og fuglene, 15ja, alt, hvad der kunne trække vejret, 16sådan som Gud havde befalet. Og Herren lukkede døren efter dem.

17I 40 dage blev vandet ved med at stige, og arken flød på vandet. 18Vandet steg og steg, 19indtil de højeste bjerge stod under vand. 20Vandet nåede mere end 7 meter over bjergtoppene. 21-22Alt levende på landjorden omkom—både dyr og mennesker. 23Kun Noa overlevede—og sammen med ham alle dem, som var i arken.

24I 150 dage var jorden i vandmassernes vold.