ዘፍጥረት 49 – NASV & NVI

New Amharic Standard Version

ዘፍጥረት 49:1-33

ያዕቆብ ልጆቹን ባረከ

49፥1-28 ተጓ ምብ – ዘዳ 33፥1-29

1ከዚህ በኋላ ያዕቆብ ልጆቹን ሁሉ አስጠርቶ እንዲህ አላቸው፤ “በኋለኛው ዘመን ምን እንደሚደርስባችሁ እነግራችሁ ዘንድ ተሰብሰቡ፤

2“እናንተ የያዕቆብ ልጆች ሆይ፤

ተሰብሰቡና ስሙ፤

አባታችሁ እስራኤልንም አድምጡ፤

3“ሮቤል፣ አንተ የበኵር ልጄ ነህ፤

ኀይሌና የጕብዝናዬም መጀመሪያ፤

በክብር ትልቃለህ፤ በኀይልም

ትበልጣለህ።

4እንደ ውሃ የዋለልህ ነህና እልቅና

አይኖርህም፤

የአባትህን መኝታ ደፍረሃል፤

ምንጣፌንም አርክሰሃል።

5“ስምዖንና ሌዊ ወንድማማቾች፣

ሰይፎቻቸው49፥5 በዕብራይስጥ የዚህ ቃል ትርጕም አይታወቅም። የዐመፅ መሣሪያዎች ናቸው።

6ወደ ሸንጓቸው አልግባ፤

ጉባኤያቸው ውስጥ አልገኝ፤

በቍጣ ተነሣሥተው ሰዎችን ገድለዋል፤

የበሬዎችንም ቋንጃ እንዳሻቸው ቈራርጠዋል።

7እጅግ አስፈሪ የሆነ ቍጣቸው፣

ጭከና የተሞላ ንዴታቸው የተረገመ ይሁን፤

በያዕቆብ እበትናቸዋለሁ፤

በመላው እስራኤልም አሠራጫቸዋለሁ።

8“ይሁዳ፣49፥8 ይሁዳ የሚለው ቃል ውዳሴ የሚል ትርጕም ካለው የዕብራይስጥ ቃል የመጣ ሲሆን፣ ከዚሁ ቃል ጋር አንድ ዐይነት ድምፅ አለው። ወንድሞችህ ይወድሱሃል፤

እጅህም የጠላቶችህን ዐንገት ዐንቆ ይይዛል፤

የአባትህ ልጆች በፊትህ ተደፍተው ይሰግዱልሃል።

9አንተ የአንበሳ ደቦል ይሁዳ፤

ከዐደንህ የምትመለስ ልጄ፣

እንደ አንበሳ ያደፍጣል፤ በምድርም ላይ ይተኛል፤

እንደ እንስት አንበሳም ያደባል፤

ታዲያ ማን ሊቀሰቅሰው ይደፍራል?

10በትረ መንግሥት ከይሁዳ እጅ አይወጣም፤

የገዥነት ምርኵዝም ከእግሮቹ መካከል።

ገዥነት የሚገባው እስኪመጣ ድረስ፣49፥10 ወይም ሴሎ እስኪመጣ ድረስ ወይም ክብር የሚገባው እስኪመጣ ድረስ

ሕዝቦች ሁሉ ይታዘዙታል።

11አህያውን በወይን ግንድ፣

ውርንጫውንም በምርጡ የወይን ሐረግ

ቅርንጫፍ ላይ ያስራል፤

ልብሱን በወይን ጠጅ፣

መጐናጸፊያውንም በወይን ጭማቂ ያጥባል።

12ዐይኖቹ ከወይን ጠጅ የቀሉ፣

ጥርሶቹም ከወተት ይልቅ የነጡ ይሆናሉ።

13“ዛብሎን፣ በባሕር ዳር ይኖራል፤

የመርከቦች መጠጊያም ይሆናል፤

ወሰኑም እስከ ሲዶና ይደርሳል።

14“ይሳኮር፣ በጭነት49፥14 የመስክ ላይ እሳት መካከል የሚተኛ

ዐጥንተ ብርቱ አህያ ነው።

15ማረፊያ ቦታው መልካም፣

ምድሪቱም አስደሳች መሆኗን ሲያይ፣

ትከሻውን ለሸክም ያመቻቻል፤

ተገድዶም ያገለግላል።

16“ዳን፣49፥16 ዳን ማለት ፍትሕ ይሰጣል ማለት ነው። ከእስራኤል ነገዶች እንደ አንዱ ሆኖ፣

በራሱ ሕዝብ ላይ ይፈርዳል።

17ዳን የመንገድ ዳር እባብ፣

የመተላለፊያም መንገድ እፉኝት ነው፤

ጋላቢው የኋሊት እንዲወድቅ፣

የፈረሱን ሰኰና ይነክሳል።

18እግዚአብሔር ሆይ (ያህዌ)፤ ማዳንህን እጠባበቃለሁ።

19“ጋድን49፥19 ጋድ ማለት ማጥቃት እንዲሁም ወራሪ ሰራዊት ማለት ነው። ወራሪዎች አደጋ ይጥሉበታል፤

እርሱ ግን ዱካቸውን ተከታትሎ ብድሩን ይመልሳል።

20“አሴር ማእደ ሰፊ ይሆናል፤

ለነገሥታትም የሚስማማ ምግብ ያቀርባል።

21“ንፍታሌም ነጻ እንደ ተለቀቀች፣

የሚያማምሩም ግልገሎች49፥21 ወይም ነጻ፤ ውብ ቃሎችን የሚናገር

እንደምትወልድ ሚዳቋ ነው።

22“ዮሴፍ፤ ፍሬያማ የወይን ተክል፣

በምንጭ ዳር የተተከለ ወይን ነው።

ሐረጎቹ ቅጥርን ያለብሳሉ።49፥22 ወይም ዮሴፍ የዱር የፈረስ ግልገል፣ በምንጭ ዳር ያለ የፈረስ ግልገል፣ በባለ ዕርከን ኰረብታ ላይ የዱር አህያ ነው

23ቀስተኞች በጭካኔ አጠቁት፤

በጥላቻም ነደፉት።

24ነገር ግን በያዕቆብ ኀያል አምላክ ክንድ፣49፥23-24 ወይም ቀስተኞች ያጠቃሉ… ያስፈነጥራሉ… ይኖራሉ… ይቈያሉ

እረኛው በሆነው በእስራኤል ዐለት፣ ቀስቱ ጸና፤

ጠንካራ ክንዱም ቀለጠፈ።

25አንተን በሚረዳህ በአባትህ አምላክ፣

በሚባርክህ፣ ሁሉን ማድረግ በሚችል አምላክ፣49፥25 ዕብራይስጡ ሻዳይ ይለዋል

ከላይ ከሰማይ በሚገኝ ረድኤት፣

ከምድር ጥልቅ በሚገኝ በረከት፣

ከማሕፀንና ከጡት በሚገኝ ምርቃት ይባርክሃል።

26ከጥንት ተራሮች በረከት፣

ከዘላለም ኰረብቶች ምርቃት ይልቅ፣

የአባትህ በረከት ይበልጣል።49፥26 …ከአያት ቅድማያቶቼ… ታላቅ ነው

ይህ ሁሉ በዮሴፍ ራስ ላይ ይውረድ፤

በወንድሞቹ መካከል አለቃ በሆነውም ግንባር ላይ ይረፍ።49፥26 ወይም ከ… የተለየ

27“ብንያም፣ ነጣቂ ተኵላ ነው፤

ያደነውን ማለዳ ይበላል፤

የማረከውን ማታ ይከፋፈላል።”

28እነዚህ ሁሉ ዐሥራ ሁለቱ የእስራኤል ነገዶች ናቸው። ይህም እያንዳንዳቸውን ተገቢ በሆነው በረከት አባታቸው ሲባርካቸው የተናገረው ቃል ነው።

የያዕቆብ መሞት

29ከዚህ በኋላ ያዕቆብ እንዲህ ሲል አዘዛቸው፤ “እነሆ፤ ወደ ወገኖቼ የምሰበሰብበት ጊዜ ደርሷል፤ በኬጢያዊው በኤፍሮን ዕርሻ ውስጥ ባለችው ዋሻ ከአባቶቼ ዘንድ ቅበሩኝ፤ 30ይህ በከነዓን ምድር፣ በመምሬ አጠገብ፣ በማክፌላ ዕርሻ ውስጥ ያለው ዋሻ፣ የመቃብር ቦታ እንዲሆን አብርሃም ከኬጢያዊው ኤፍሮን ላይ ከነዕርሻ ቦታው የገዛው ነው። 31በዚያ አብርሃምና ሚስቱ ሣራ ተቀብረዋል፤ በዚያ ይስሐቅና ሚስቱ ርብቃ ተቀብረዋል፤ 32እኔም ልያን የቀበርኋት እዚያው ነው። ዕርሻውና ዋሻው የተገዙት ከኬጢያውያን49፥32 ወይም ከኬጢ ልጆች ላይ ነው።”

33ያዕቆብ እነዚህን ቃላት ለልጆቹ ተናግሮ እንዳበቃ፣ እግሮቹን በዐልጋው ላይ ሰብስቦ፣ የመጨረሻ ትንፋሹን ተነፈሰ፤ ወደ ወገኖቹም ተሰበሰበ።

Nueva Versión Internacional

Génesis 49:1-33

Jacob bendice a sus hijos

1Jacob llamó a sus hijos y dijo: «Reúnanse, que voy a declararles lo que les va a suceder en el futuro:

2»Hijos de Jacob: acérquense y escuchen;

presten atención a su padre Israel.

3»Tú, Rubén, eres mi primogénito,

primer fruto de mi vigor,

primero en honor y en poder.

4Impetuoso como un torrente,

ya no serás el primero:

te acostaste en mi cama;

profanaste la cama de tu propio padre.

5»Simeón y Leví son hermanos;

sus espadas son instrumentos de violencia.

6¡No quiero participar de sus reuniones

ni arriesgar mi honor en sus asambleas!,

porque en su furor mataron hombres,

y por capricho mutilaron toros.

7¡Malditas sean la violencia de su enojo

y la crueldad de su furor!

Los dispersaré en el país de Jacob,

los desparramaré en la tierra de Israel.

8»Tú, Judá, serás alabado49:8 En hebreo, Judá suena como el verbo que significa alabar. por tus hermanos;

dominarás a tus enemigos

y tus propios hermanos se postrarán ante ti.

9Mi hijo Judá es como un cachorro de león

que se ha nutrido de la presa.

Se agacha como un león,

se tiende como una leona:

¿quién se atreverá a despertarlo?

10El cetro no se apartará de Judá,

ni de entre sus pies el bastón de mando,

hasta que llegue el verdadero rey,49:10 el verdadero rey. Alt. el verdadero dueño o a quien le pertenece.

quien merece la obediencia de los pueblos.

11Judá amarra su asno a la vid

y la cría de su asno a la mejor cepa;

lava su ropa en vino;

su manto, en la sangre de las uvas.

12Sus ojos son más oscuros que el vino;

sus dientes, más blancos que la leche.49:12 Sus ojos … la leche. Alt. Sus ojos están oscurecidos por el vino; sus dientes, blanqueados por la leche.

13»Zabulón vivirá a la orilla del mar;

será puerto seguro para las naves

y sus fronteras llegarán hasta Sidón.

14»Isacar es un asno fuerte

echado entre dos alforjas.

15Al ver que el establo era bueno

y que la tierra era agradable,

agachó el hombro para llevar la carga

y se sometió a la esclavitud.

16»Dan hará justicia en su pueblo,

como una de las tribus de Israel.

17Dan es una serpiente junto al camino,

una víbora junto al sendero,

que muerde los talones del caballo

y hace caer de espaldas al jinete.

18»¡Señor, espero tu salvación!

19»Las hordas atacan a Gad,

pero él las atacará por la espalda.

20»Aser disfrutará de comidas deliciosas;

ofrecerá manjares de reyes.

21»Neftalí es una gacela libre,

que tiene hermosos cervatillos.49:21 que … cervatillos. Alt. que pronuncia hermosas palabras.

22»José es un retoño fértil,

fértil retoño junto al agua,

cuyas ramas trepan por el muro.

23Los arqueros lo atacaron sin piedad;

le tiraron flechas, lo hostigaron.

24Pero su arco se mantuvo firme

y sus brazos fueron ágiles.

¡Gracias al Poderoso de Jacob,

al Pastor y Roca de Israel!

25¡Gracias al Dios de tu padre, que te ayuda!

¡Gracias al Todopoderoso, que te bendice!

¡Con bendiciones de lo alto!

¡Con bendiciones del abismo!

¡Con bendiciones de los pechos y del seno materno!

26Son mejores las bendiciones de tu padre

que las de los montes de antaño,

que la abundancia de las colinas eternas.

¡Que descansen estas bendiciones

sobre la cabeza de José,

sobre la frente del escogido entre sus hermanos!

27»Benjamín es un lobo rapaz

que en la mañana devora la presa

y en la tarde reparte los despojos».

28Estas son las doce tribus de Israel y esto es lo que su padre dijo cuando impartió a cada una de ellas su bendición.

Muerte de Jacob

29Además, Jacob dio estas instrucciones: «Ya estoy a punto de reunirme con los míos. Entiérrenme junto a mis antepasados, en la cueva que está en el campo de Efrón el hitita. 30Se trata de la cueva de Macpela, frente a Mamré, en la tierra de Canaán. Está en el campo que Abraham compró a Efrón el hitita, para que fuera el sepulcro de la familia. 31Allí fueron sepultados Abraham y su esposa Sara, Isaac y su esposa Rebeca. Allí también enterré a Lea. 32Ese campo y su cueva se les compró a los hititas».

33Cuando Jacob terminó de dar estas instrucciones a sus hijos, volvió a acostarse; exhaló el último suspiro y fue a reunirse con sus antepasados.